TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.5K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኮማንደር ዋለልኝ⬆️"እስካሁንም በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ ምንም አይነት የመገናኛ ሬዲዮም ሆነ ቦምብ የለም።”

#BahirDar #ባህር_ዳር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BAHIRDAR

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት በየአጥቢያዎቹ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ጸሎተ ምህላ አወጀ፡፡ ሀገረ ስብከቱ ለመስከረም 11 ቀን 2012 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ከፊታችን ሰኞ መስከረም 5 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ጸሎተ ምህላ አውጇል፤ ለመስከረም 11 ቀን 2012 ዓ.ም ደግሞ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ ሀገረ ስብከቱ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመላከተው የፀሎተ ምህላው ዓላማ በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ የሚደርሰውን መከራ፣ ግፍ እና መሰደድ አስመልክታ ለፈጣሪዋ መልዕክት ለማቅረብ ነው፡፡

ከጸሎተ ምህላው እና ከሰልፉ በኋላ በእለቱ 10፡00 ሰዓት ላይ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች እና የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ስለወቅታዊው የቤተ ክርስቲያን ጥያቄ ውይይት ይደረጋል ተብሏል በመግለጫው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia