#አብን
አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን ታፍሰው #ታሰሩብን" ሲል የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ /አብን/ አቤቱታ አሰማ። ሃያ ስምንት እንደሚሆኑ አብን ያሳወቃቸው አባላትና ደጋፊዎቹ የታሠሩት የመሪዎቻቸውን ጉዳይ ለመከታተል አዲስ አበባ፤ አራዳ ምድብ ችሎት ተገኝተው በነበረ ጊዜ መሆኑንም አብን ገልጿል። “የታሠሩብን ‘አማራነት እና እውነት አይታሰርም’ የሚል ሸሚዝ የለበሱ ናቸው” ሲሉ የንቅናቄው የፅሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ በለጠ ካሣ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። የተያዙት ሰዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የሦስት ሺህ ብር ዋስ እንዲያቀርቡ መጠየቃቸውንም አቶ በለጠ አመልክተዋል።
ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን ታፍሰው #ታሰሩብን" ሲል የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ /አብን/ አቤቱታ አሰማ። ሃያ ስምንት እንደሚሆኑ አብን ያሳወቃቸው አባላትና ደጋፊዎቹ የታሠሩት የመሪዎቻቸውን ጉዳይ ለመከታተል አዲስ አበባ፤ አራዳ ምድብ ችሎት ተገኝተው በነበረ ጊዜ መሆኑንም አብን ገልጿል። “የታሠሩብን ‘አማራነት እና እውነት አይታሰርም’ የሚል ሸሚዝ የለበሱ ናቸው” ሲሉ የንቅናቄው የፅሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ በለጠ ካሣ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። የተያዙት ሰዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የሦስት ሺህ ብር ዋስ እንዲያቀርቡ መጠየቃቸውንም አቶ በለጠ አመልክተዋል።
ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አብን
በእነ አስጠራው ከበደ እና በእነ ሲያምር ጌቴ መዝገብ የተከሰሱት የአብን አባላትና አመራራሮች በብር ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ተፈቀደላቸው ሲል አብን በፌስቡክ ጉፁ አሳወቀ። ከታሰሩ ከ1 ወር በላይ የሆናቸውና በእነ አስጠራው ከበደ መዝገብ የተከሰሱት 26ቱ የአብን አመራሮችና አባላት ዛሬ ማለትም ሐምሌ 23/2011 ዓ.ም 8:00 ላይ ለ3ኛ ጊዜ አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው የነበረ ሲሆን እያንዳንዳቸው በ1ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወስኗል ብሏል ንቅናቄው። በሌላ በኩል በእነ ሲያምር ጌቴ መዝገብ የተከሰሱት ሲያምር ጌቴ በ3ሺህ ብር እንዲሁም ሌሎች እያንዳንዳቸው በ2 ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ መወሰኑን ንቅናቄው በፌስቡክ ገፁ ገልጿል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በእነ አስጠራው ከበደ እና በእነ ሲያምር ጌቴ መዝገብ የተከሰሱት የአብን አባላትና አመራራሮች በብር ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ተፈቀደላቸው ሲል አብን በፌስቡክ ጉፁ አሳወቀ። ከታሰሩ ከ1 ወር በላይ የሆናቸውና በእነ አስጠራው ከበደ መዝገብ የተከሰሱት 26ቱ የአብን አመራሮችና አባላት ዛሬ ማለትም ሐምሌ 23/2011 ዓ.ም 8:00 ላይ ለ3ኛ ጊዜ አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው የነበረ ሲሆን እያንዳንዳቸው በ1ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወስኗል ብሏል ንቅናቄው። በሌላ በኩል በእነ ሲያምር ጌቴ መዝገብ የተከሰሱት ሲያምር ጌቴ በ3ሺህ ብር እንዲሁም ሌሎች እያንዳንዳቸው በ2 ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ መወሰኑን ንቅናቄው በፌስቡክ ገፁ ገልጿል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia