ከወሊሶ🔝
"ፀግሽ ወሊሶ ከተማና ዲለላ ላይ ከጠዋት ጀምሮ ሰልፍ አለ መንገድ ዝግ ነው፡፡ የሰልፉ ምክንያት ጦላይ በሚገኘዉ ማሰልጠኛ የነበሩት 280 የቀድሞ የኦነግ ሰራዊት ላይ በደረሰዉ የምግብ መመረዝ ምክንያት ነዉ፡፡ ከሰራዊቱ አባላት የተወሰኑት አሁን በወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል ይገኛሉ፡፡ የሞተ ሰዉ ይኑር አይኑር አላወኩም፡፡"
ፎቶ: OMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ፀግሽ ወሊሶ ከተማና ዲለላ ላይ ከጠዋት ጀምሮ ሰልፍ አለ መንገድ ዝግ ነው፡፡ የሰልፉ ምክንያት ጦላይ በሚገኘዉ ማሰልጠኛ የነበሩት 280 የቀድሞ የኦነግ ሰራዊት ላይ በደረሰዉ የምግብ መመረዝ ምክንያት ነዉ፡፡ ከሰራዊቱ አባላት የተወሰኑት አሁን በወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል ይገኛሉ፡፡ የሞተ ሰዉ ይኑር አይኑር አላወኩም፡፡"
ፎቶ: OMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ከኖኖ ወረዳ እንዲሁም የድሬ ጎዶ ከተማ እና አካባቢዋ ነዋሪዎች ከምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች ለተፈናቀሉ ወገኖች 300 ኩንታል በቆሎ እና የቤት መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ። የድጋፉ አስተባባሪዎች በአካባቢያቸው ብቻ ተወስነው ዕርዳታውን ቢያሰባስቡም ያገኙት ምላሽ ቀላል እንዳልሆነ ገልጸዋል። ሁኔታው ባይከሰት መልካም ነበር ያሉት የነዋሪዎቹ ተወካዮች "አሁንም ተፈናቃዮች በፍጥነት መቋቋምና ወደ ቀደመ ሕይወታቸው መመለስ አለባቸው" ብለዋል። ድጋፉን የተረከቡት የአማራ ክልል አደጋ መከላከል ምግብ ዋስትና ፕሮግራምና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አማረ ክንዴ ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ድረስ ተጉዘው ድጋፍ ያደረጉትን ነዋሪዎች አመስግነዋል። ድጋፉ በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ለሚገኙ አስቸኳይ ዕርዳታ ፈላጊዎች ፍትሐዊ በሆነ መልኩ የሚዳረስ መሆኑንም ለነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
Via አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢትዮጵያን እየጎበኝ የሚገኙት #ኢቫንካ ትራምፕ #በቦይንግ አውሮፕላን አደጋ #ህይዎታቸውን ላጡ ዜጎች #የአበባ_ጉንጉን አስቀምጠዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወሊሶ🔝
"በወሊሶ ከተማ እየተካሄደ ባለው #ሰልፍ ምክንያት መንገድ ተዘግቶ ቆመናል። #ከአዲስ_አበባ እና #ከወልቂጤ ሚመጣ መኪና #ማለፍ አልቻለም።"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በወሊሶ ከተማ እየተካሄደ ባለው #ሰልፍ ምክንያት መንገድ ተዘግቶ ቆመናል። #ከአዲስ_አበባ እና #ከወልቂጤ ሚመጣ መኪና #ማለፍ አልቻለም።"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስጠንቀቂያ‼️
‹‹ከሸዋ ሮቢት እስከ ሃርቡ ከተማ ባለው ዋና መንገድ ግራና ቀኝ አምስት ኪሎ ሜትር ድረስ ከፌደራል እና ከክልል የፀጥታ ኃይል ውጭ መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ተከልክሏል፡፡››
.
.
በሰሜን ሽዋ ዞን እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ከሰሞኑ የተከሰተውን የሰላም እጦት በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከፌደራል ልዩ ኃይል እና ከአማራ ክልል ልዩ ኃይል የተውጣጣ ጥምር የፀጥታ ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ ትላንት #በከሚሴ ከተማ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ጥምር የፀጥታ ኃይሉ ዕቅድ አዘጋጅቶ እና በሁለቱም ዞኖች በሚገኙ እና የፀጥታ ስጋት ባለባቸው 10 ወረዳዎች ከሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አድርጎ ወደ ሥራ መግባቱን አስታውቋል፡፡
በኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የ11ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴል ጄኔራል ሰኢድ ትኩየ መግለጫውን በሰጡበት ወቅት እንዳስታወቁት የጥምር ፀጥታ ኃይሉ ዕቅድ ስኬታማ እንዲሆንና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን የመላ ሕዝቡ የጋራ ትብብር ያስፈልጋል፡፡ ‹‹ችግሩ ከተከሰተ በኋላ የተለያዩ የፀጥታ ኃይሎች በመግባታቸው በአካባቢው አንፃራዊ ሰላም ቢኖርም አሁንም ድረስ ግን ሕዝቡ ስጋቶች አሉበት›› ያሉት ብርጋዴል ጄኔራል ሰኢድ የፀጥታ ዕቅዱ ዓላማዎችም ሕዝቡን ወደነበረበት ሰላሙ መመለስ፣ ተጎጅዎችን ማቋቋም፣ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱን ማጠናከር እና አጥፊዎችን በመለየት ለሕግ ማቅረብ እንደሆኑም አስታውቀዋል፡፡
እንደ ብርጋዴል ጄኔራል ሰኢድ ገለፃ ጥምር የፀጥታ ኃይሉ መንገዶችን ሙሉ በሙሉ ክፍት ማድረግ፣ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቦታቸው መመለስ፣ የግጭቱን አስተባባሪዎች መለየትና ለሕግ ማቅረብ እና ጠንካራ የነበረውን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ወደ ነበረበት መመለስ ዕቅዱ የሚመልሳቸው ግቦች ናቸው፡፡ በዕቅዱ ከጥምር የፀጥታ ኃይሎች ውጭ መሣሪያ ይዞ የመንቀሳቀስ ክልከላም ተደርጓል፡፡ ‹‹ከሸዋ ሮቢት እስከ እስከ ሃርቡ ከተማ ድረስ ባለው ዋናው መንገድ ግራ እና ቀኝ 5 ኪሎ ሜትር ድረስ ከፀጥታ ኃይሉ ውጭ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል ነው›› ተብሏል፡፡ ይዞ በሚገኝ ማንኛም አካል ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድም ተገልጿል፡፡
ጥምር የፀጥታ ኃይሉ ለፀጥታ ስጋት ይሆናሉ ያላቸውን 12 የሚደርሱ ቦታዎች በሁለቱም ዞኖች ለይቷል፡፡ በነዚህ ኬላዎች ላይም ጊዜያዊ እና ቋሚ ፍተሻ ይደረጋል፡፡ ከክልል እና የፌደራል የፀጥታ ኃይሎች ውጭ በየትኛውም አካባቢ በግልም ሆነ በቡድን የሚደረግ ፍተሻ የተከለከለ መሆኑን ጥምር የፀጥታ ኃይሉ በመግለጫው አስታውቋል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹ከሸዋ ሮቢት እስከ ሃርቡ ከተማ ባለው ዋና መንገድ ግራና ቀኝ አምስት ኪሎ ሜትር ድረስ ከፌደራል እና ከክልል የፀጥታ ኃይል ውጭ መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ተከልክሏል፡፡››
.
.
በሰሜን ሽዋ ዞን እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ከሰሞኑ የተከሰተውን የሰላም እጦት በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከፌደራል ልዩ ኃይል እና ከአማራ ክልል ልዩ ኃይል የተውጣጣ ጥምር የፀጥታ ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ ትላንት #በከሚሴ ከተማ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ጥምር የፀጥታ ኃይሉ ዕቅድ አዘጋጅቶ እና በሁለቱም ዞኖች በሚገኙ እና የፀጥታ ስጋት ባለባቸው 10 ወረዳዎች ከሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አድርጎ ወደ ሥራ መግባቱን አስታውቋል፡፡
በኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የ11ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴል ጄኔራል ሰኢድ ትኩየ መግለጫውን በሰጡበት ወቅት እንዳስታወቁት የጥምር ፀጥታ ኃይሉ ዕቅድ ስኬታማ እንዲሆንና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን የመላ ሕዝቡ የጋራ ትብብር ያስፈልጋል፡፡ ‹‹ችግሩ ከተከሰተ በኋላ የተለያዩ የፀጥታ ኃይሎች በመግባታቸው በአካባቢው አንፃራዊ ሰላም ቢኖርም አሁንም ድረስ ግን ሕዝቡ ስጋቶች አሉበት›› ያሉት ብርጋዴል ጄኔራል ሰኢድ የፀጥታ ዕቅዱ ዓላማዎችም ሕዝቡን ወደነበረበት ሰላሙ መመለስ፣ ተጎጅዎችን ማቋቋም፣ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱን ማጠናከር እና አጥፊዎችን በመለየት ለሕግ ማቅረብ እንደሆኑም አስታውቀዋል፡፡
እንደ ብርጋዴል ጄኔራል ሰኢድ ገለፃ ጥምር የፀጥታ ኃይሉ መንገዶችን ሙሉ በሙሉ ክፍት ማድረግ፣ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቦታቸው መመለስ፣ የግጭቱን አስተባባሪዎች መለየትና ለሕግ ማቅረብ እና ጠንካራ የነበረውን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ወደ ነበረበት መመለስ ዕቅዱ የሚመልሳቸው ግቦች ናቸው፡፡ በዕቅዱ ከጥምር የፀጥታ ኃይሎች ውጭ መሣሪያ ይዞ የመንቀሳቀስ ክልከላም ተደርጓል፡፡ ‹‹ከሸዋ ሮቢት እስከ እስከ ሃርቡ ከተማ ድረስ ባለው ዋናው መንገድ ግራ እና ቀኝ 5 ኪሎ ሜትር ድረስ ከፀጥታ ኃይሉ ውጭ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል ነው›› ተብሏል፡፡ ይዞ በሚገኝ ማንኛም አካል ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድም ተገልጿል፡፡
ጥምር የፀጥታ ኃይሉ ለፀጥታ ስጋት ይሆናሉ ያላቸውን 12 የሚደርሱ ቦታዎች በሁለቱም ዞኖች ለይቷል፡፡ በነዚህ ኬላዎች ላይም ጊዜያዊ እና ቋሚ ፍተሻ ይደረጋል፡፡ ከክልል እና የፌደራል የፀጥታ ኃይሎች ውጭ በየትኛውም አካባቢ በግልም ሆነ በቡድን የሚደረግ ፍተሻ የተከለከለ መሆኑን ጥምር የፀጥታ ኃይሉ በመግለጫው አስታውቋል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መልካምነት ይፋፋም...🔝
"ፀግሽ በፈለገ ህይወት ት/ት ቤት ምክትል ር/መር ነኘ እናም በት/ቤታችን የሚማሩ ተማሪዎች #ለተፈናቀሉ ዜጎች የድርሻቸውን በመወጣት #ከጥላቻ_ይልቅ መረዳዳትን ባህል አድርገው ግምቱ ወደ 10000 ብር የሚጠጋ ድጋፍ በማድረጋቸው አመስግንልኘ!"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ፀግሽ በፈለገ ህይወት ት/ት ቤት ምክትል ር/መር ነኘ እናም በት/ቤታችን የሚማሩ ተማሪዎች #ለተፈናቀሉ ዜጎች የድርሻቸውን በመወጣት #ከጥላቻ_ይልቅ መረዳዳትን ባህል አድርገው ግምቱ ወደ 10000 ብር የሚጠጋ ድጋፍ በማድረጋቸው አመስግንልኘ!"
@tsegabwolde @tikvahethiopia