TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በክቡር የኢፌድሪ ጠ/ሚንስተር #አብይ_አህመድ(ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሊተገበር የታቀደው የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክትን ለመደገፍ የቻይና መንግስት #ፍላጎት እንዳለው ገለፀ፡፡ ለዚህም የቻይና መንግስት የባለሞያ ልዑካን ቡድን የከተማ አስተዳደሩ የጀመረውን የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክትን በገንዘብ እና የቴክኒክ ዕገዛ በሚደረግበት ሁኔታ ላይ ከኢ/ር #ታከለ_ኡማ ጋር በዛሬው ዕለት ተወያይተዋል፡፡ በዚህም የቴክኒክ ቡድኑ የቻይና መንግስት ፕሮጀክቱን የሚደግፍበት ሁኔታ ላይ ጥናት የሚያደርግ ይሆናል፡፡

Via @mayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ገበታ ለሸገር ከዶክተር አብይ ጋር...!

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ ለአዲስ አበባ ወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክት የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ምሽት አዘጋጁ።

ለእራት ምሽት ዲፕሎማቶች፣ የኩባንያ ስራ አስኪያጆች፣ የአለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች እና ሎሎች አካላት እንዲሳተፉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጥሪ አቅርበዋል።

የእራት ምሽቱ ለሸገር ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ጋር በሚል መሪ ቃል መዘጋጀቱ ነው የተነገረው።

ለተሳታፊዎቹ ባደረጉት ጥሪም አዲስ አበባን #ንፁህና #አረንጓዴ ለማድረግ ተሳትፏችሁ የተያዘውን ውጥን ለማሳካት ያስችላል ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድጋፋችሁ ይህን ታላቅ አላማ #ስኬታማ በማድረግ የመዲናዋን ነዋሪዎች አኗኗር ለመቀየር ወሳኝ ነው ብለዋል በመልዕክታቸው።

በአዲስ አበባ ወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ላይ የምታደርጉት ተሳትፎ ለቀጣይ ትውልድ ውብ ከተማን ለማስተላፍ በዋጋ የማይተመን ነው በማለት ገልፀዋል። በዚህ የእራት ምሽት አንድ እራትን 5 ሚሊየን ብር #ለመሸጥ ዋጋ ተቆርጦለታል።

የአዲስ አበባን ዋና ዋና ወንዞች ተፋሰስ #ለማልማት የሚያስችል ፕሮጀክት የ29 ቢሊየን ብር ፕሮጀክት ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡

አዲስ አበባን ለሁለት ከፍለው የሚፈሱ ወንዞች ላይ ያተኮረው ፕሮጀክቱ ከሰሜን አዲስ አበባ እንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ወንዝ ያለውን 56 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍንም ታውቋል፡፡ ፕሮጀክቱ በሶስት አመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት እና ፋና
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ እና ፕሬዚዳንት #ኢማኑኤል_ማክሮን የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን እየጎበኙ ነው፡፡

Via ETV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጌዴኦ ዞን

ክቡር ጠ/ሚ ዶክተር #አብይ_አህመድ እባኮት ወደጎዲቲ አምርተው ህዝቡ ያለበትን ሁኔታ ቢጎበኙ መልካም ነው። እጅግ በጣም የተጎዱ ወገኖች በብዛት የሚገኙበት ቦታ እንደሆነ አካባቢው በተደጋጋሚ የጎበኙ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።

በነገራችን ላይ ...

ክብርት የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ከሚል የጌድኦ ተፈናቃዮችን በጎበኙበት ወቅት በርካቶች የተጎዱበትን ቦታ ሳይጎበኙ ነው የተመለሱት፤ ይህን ያጫወተኝ በጌዴኦ ተፈናቃዮች ዙሪያ የሚሰራ የህክምና ባለሞያ ነው።

የትኛው አካል ነው ይህ እያደረገ ያለው
@tsegabwolde @tikvahethiopia