TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ነጭ ሳር ብሄራዊ ፓርክ⬇️

በደቡብ ክልል ጋሞ ጎፋ ዞን ባለው የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ ማንነታቸው ያልታወቀ #ታጣቂዎች ትላንት ባደረሱት ጥቃት አራት ሰዎች #መገደላቸውን የዞን የጸጥታ እና አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ለማ ቦሎ ለDW አስታወቁ።

አራቱ ግለሰቦች የተገደሉት በጥይት ተደብድበው ነው ተብሏል። ሟቾቹ እንጨት ለቅመው እና ሳር አጭደው የሚተዳደሩ እንደነበሩ የገለጹት ኃላፊው ከዚያ በተጨማሪ የደረሰ ጉዳት መኖር አለመኖሩ በእርግጠኝነት መናገር እንደሚቸገሩ ተናግረዋል። #ግድያውን የፈጸሙት ታጣቂዎች ማንነት በግልጽ እንደማይታወቅ ነገር ግን ከዚህ ቀደም በአካባቢው እንደሚንቀሳቀሱ ዞኑ መረጃ እንደነበረው ኃላፊው አስረድተዋል። አስራ ስድስት አባላት ያለበት አንድ የተደራጀ ቡድን እና አምስት አባላት ያሉት ሌላ የታጠቀ ቡድን በፓርኩ ውስጥ እንደሚዘዋወሩ መረጃው አለን ብለዋል። ከጉጂ አቅጣጫ የመጡ ናቸው የሚባሉትን እነዚህን ታጣቂዎች ለመያዝ የጸጥታ ኃይሎች ወደ ስፍራው ሲያመሩ እንደሚሰወሩም ገልጸዋል።

ምንጭ፦ DW አማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia