TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጄነራሎቹ⁉️

የቀድሞው የብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ሜቴክ ዋና ሃላፊ ሜጀር ጀነራል #ክንፈ_ዳኘው መያዛቸው ተነገረ። ሃላፊው ከትግራይ የተገኘ መረጃ እንዳመለከተው ጀነራሉ የተያዙት ትናንት ማምሻ ሁመራ ከተማ ውስጥ ነው።

#የትግራይ ልዩ ፖሊስ ጀነራሉን ከያዘ በኋላ ለፌደራል መንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች #ማስረከቡን ምንጮች አስታውቀዋል። ከጀነራል ክንፈ ዳኘው በተጨማሪ የቀድሞ ኢንሳ በሚል ምህጻረ ቃል የሚጠራው የመረጃ ቴክኖሎጂ መስሪያ ቤት የቀድሞ ሃላፊ ሜጀር ጀነራል #ተክለብርሃን_ወልደአረጋይም ከሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ጋር #መያዛቸውን የተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ዘግበው ነበር።

ይሁን እና ጀነራል ተክለብርሃን የፍርድ ቤት #የማሰሪያ ትዕዛዝ አልተሰጠባቸውም በሚል እንዳልተያዙ ምንጮቼ ገልጸዋል ብሏል የጀርመን ድምፅ ራድዮ የአማርኛው አገልግሎት ክፍል።

ጉዳዩን #ለማጣራት የተለያዩ መሥሪያ ቤቶችን እያነጋገረን ነው እንደደረሰን መረጃውን እናቀርባለን ብሏል የጀርመን ድምፅ።

ሁለቱን ጀነራሎች ጨምሮ በርካታ የቀድሞ ከፍተኛ የጦርና የመረጃ (ስለላ) ባለሥልጣናት እሥረኞችን በማሰቃየት እና በሙስና ወንጀል እንደሚጠረጠሩ የኢትዮጵያ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ትንንት አስታውቆ ነበር።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia