TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ስፖርት📌 በ2010 ሳይጠናቀቅ ወደ 2011 የተሻገረው የኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በዛሬው እለት ቀጥሎ ተካሂዷል። በዛሬው እለትም #በሀዋሳ የኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሲዳማ ቡና መካከል ቀጥሎ ተካሂዷል። በዛሬው እለት የተደረገው የቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡና ጨዋታም በመደበኛ ሰዓት ያለምንም ግብ 0ለ0 መጠናቀቁን ተከትሎ በመለያ ምት አሸናፊው ተለይቷል። በዚሀም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን በመለያ ምት 7ለ6 በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜውን መቀላቀል ችሏል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የኢህአዴግ ጠቅላላ ጉባኤ ከመስከረም 23 እስከ 25 #በሀዋሳ ከተማ ይደረጋል። ጉባኤው «በልማታዊ ዴሞክራሲ ማዕቀፍ የለውጥ እንቅስቃሴያችንን በማስቀጠል የኢትዮጵያን ሕዳሴ እናረጋግጥ» በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ ይሆናል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ለአራት ቀናት የሚቆየው የደኢህዴን 10ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት #በሀዋሳ ከተማ ጀምሯል፡፡ጉባዔው ከሌሎች ጊዜ በተለየ ሁኔታ በክብር የሚሰናበቱ አመራሮች እንደሚኖሩ ተገልጿል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የህገ ደንብ፣ #አርማና #ስያሜ ለውጥን የሚመለከቱ ውይይቶች ይካሄዳሉ ተብሏል፡፡ በ10ኛው የደኢህዴን ጉባዔ አዳዲስ አመራሮች ወደ ድርጅቱ የመሪነት እርከን ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia