#update ሀዋሳ⬇️
በሀዋሳ ከተማ ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው አልፎ መገኘታቸውን ነዋሪዎች ገለፁ። የመጀመሪያው የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ 4ኛ አመት ተማሪ የሆነው ተማሪ ደሳለኝ በናና በ23/12/2010 ገብርኤል አካባቢ ተገድሎ ተገኝቷል። ሌላኛው ወጣት ነኸምያ ጌታቸው ነሀሴ 24/2010 ዓ.ም በአላሞራ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አካባቢ ተገድሎ ተግኝቷል።
ወጣቶቹ በምን ምክንያት እንደተገደሉ አልታወቀም። እንዲሁም የወጣት ነኸምያ ግድያ ከተማሪ ደሳለኝ ጋር ግንኙነት እንዳለውም የታወቀ ነገር የለም። ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሰራሁ ነው ብሏል።
ለቻናላችን አስተያየታቸውን የላኩ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት ይህን ወንጀል ይፈፀሙ አካላት #በአስችኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል። የከተማው ፖሊስም የዜጎችን #ደህንነት የማስጠበቅ ስራውን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ብለዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሀዋሳ ከተማ ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው አልፎ መገኘታቸውን ነዋሪዎች ገለፁ። የመጀመሪያው የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ 4ኛ አመት ተማሪ የሆነው ተማሪ ደሳለኝ በናና በ23/12/2010 ገብርኤል አካባቢ ተገድሎ ተገኝቷል። ሌላኛው ወጣት ነኸምያ ጌታቸው ነሀሴ 24/2010 ዓ.ም በአላሞራ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አካባቢ ተገድሎ ተግኝቷል።
ወጣቶቹ በምን ምክንያት እንደተገደሉ አልታወቀም። እንዲሁም የወጣት ነኸምያ ግድያ ከተማሪ ደሳለኝ ጋር ግንኙነት እንዳለውም የታወቀ ነገር የለም። ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሰራሁ ነው ብሏል።
ለቻናላችን አስተያየታቸውን የላኩ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት ይህን ወንጀል ይፈፀሙ አካላት #በአስችኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል። የከተማው ፖሊስም የዜጎችን #ደህንነት የማስጠበቅ ስራውን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ብለዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️
የህዝቡን #ደህንነት እና #ሰላም ለመጠበቅ ሲል መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ እንደሚወስድ የፌደራል ፖሊስ ገለፀ።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸው ላይ የመንግስት ትእግስት #ገደብ እንዳለው በመግለፅ #ጉልበተኞችን እንደማይታገስ አስታውቀዋል።
አሁን ላይ እየተስተዋሉ ያሉት #ሁከቶች #በሁለት የፖለቲካ ድርጅቶች ስም የተቀነባበሩ መሆናቸውን ኮሚሽነር ጀነራሉ ጠቁመዋል።
ባለፉት ሦስት ቀናት በቡራዩና አካባቢው ብዛት ያላቸው ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን በመጠቆም፥ በተለያዩ ቦታዎች ተዘርፈው የነበሩ ንብረቶችን የማሰባሰብ ስራ መሰራቱንም ነው ያስታወቁት።
በአጠቃላይም በቡራዩ ከ300 አስከ 400 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች ሲያዙ በአዲስ አበባ ደግሞ ከ300 በላይ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ #ገንዘብ ተከፍሏቸው ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት እንዲሁም ብሄርን መሰረት ያደረጉ ስድቦችንም ጭምር በማሰራጨት #የተጠረጠሩ ግለሰቦች መያዛቸውንም አንስተዋል።
ይህ ድርጊት #በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባና በአርባ ምንጭ መታየቱን ጠቅሰዋል።
ኮሚሽነሩ በቡራዩና አካባቢው የተፈፀመውን ግድያ ለማውገዝ በርካታ ሰላማዊ ሰው መውጣቱን ጠቅሰው #የተወሰኑ ቡድኖች ግን አዝሚሚያቸው ሌላ ነበር ብለዋል።
ከእነዚህ የተወሰኑ ግለሰቦች መካከልም #ቦምብ ይዘው የነበሩ በህብረተሰቡ ትብብር መያዛቸውን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በፒያሳና በመርካቶ #ለዝርፊያ የሚቃጡ ግለሰቦች እንደነበሩ ነው የጠቀሱት።
የተወሰኑት የጸጥታ ኃይሎች ደግሞ ጠብመንጃ ለመንጠቅ ሙከራ ያደረጉ ሲሆን በዚህም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር #ግብግብ ገጥመው ነበር ብለዋል።
ይህንንም ተከትሎ የአምስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፥ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸውን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ይህ ግርግር ሆን ተብሎ የተጀመረውን ለውጥ #እንዳይሳካ #ታስቦበት የተከናወነ መሆኑን ነው ያነሱት።
©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህዝቡን #ደህንነት እና #ሰላም ለመጠበቅ ሲል መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ እንደሚወስድ የፌደራል ፖሊስ ገለፀ።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸው ላይ የመንግስት ትእግስት #ገደብ እንዳለው በመግለፅ #ጉልበተኞችን እንደማይታገስ አስታውቀዋል።
አሁን ላይ እየተስተዋሉ ያሉት #ሁከቶች #በሁለት የፖለቲካ ድርጅቶች ስም የተቀነባበሩ መሆናቸውን ኮሚሽነር ጀነራሉ ጠቁመዋል።
ባለፉት ሦስት ቀናት በቡራዩና አካባቢው ብዛት ያላቸው ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን በመጠቆም፥ በተለያዩ ቦታዎች ተዘርፈው የነበሩ ንብረቶችን የማሰባሰብ ስራ መሰራቱንም ነው ያስታወቁት።
በአጠቃላይም በቡራዩ ከ300 አስከ 400 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች ሲያዙ በአዲስ አበባ ደግሞ ከ300 በላይ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ #ገንዘብ ተከፍሏቸው ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት እንዲሁም ብሄርን መሰረት ያደረጉ ስድቦችንም ጭምር በማሰራጨት #የተጠረጠሩ ግለሰቦች መያዛቸውንም አንስተዋል።
ይህ ድርጊት #በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባና በአርባ ምንጭ መታየቱን ጠቅሰዋል።
ኮሚሽነሩ በቡራዩና አካባቢው የተፈፀመውን ግድያ ለማውገዝ በርካታ ሰላማዊ ሰው መውጣቱን ጠቅሰው #የተወሰኑ ቡድኖች ግን አዝሚሚያቸው ሌላ ነበር ብለዋል።
ከእነዚህ የተወሰኑ ግለሰቦች መካከልም #ቦምብ ይዘው የነበሩ በህብረተሰቡ ትብብር መያዛቸውን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በፒያሳና በመርካቶ #ለዝርፊያ የሚቃጡ ግለሰቦች እንደነበሩ ነው የጠቀሱት።
የተወሰኑት የጸጥታ ኃይሎች ደግሞ ጠብመንጃ ለመንጠቅ ሙከራ ያደረጉ ሲሆን በዚህም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር #ግብግብ ገጥመው ነበር ብለዋል።
ይህንንም ተከትሎ የአምስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፥ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸውን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ይህ ግርግር ሆን ተብሎ የተጀመረውን ለውጥ #እንዳይሳካ #ታስቦበት የተከናወነ መሆኑን ነው ያነሱት።
©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia