TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላችኋል " - በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት

በምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ፤ ትናንት ጥር 15/2017 ዓ.ም  " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠውን መግለጫ የሚቃወም መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም መግለጫው ፥ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት" የነሃሴው " ብሎ ሲጠራው ራሱን ደግሞ " ነባር " በማለት ገልጿል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን "  በሚል ያወጡት መግለጫ የ " ነሃሴው ህወሓት ህዝቡን እና ሰራዊቱ ለመበታተነ የሰራው ክፋት ውጤት ነው " በማለት ገልፆታል።

" የነሃሴው ህወሓት ህዝብን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያልተቀበለው ጉባኤ  በማካሄድ ነባሩን ህወሓት እንዲዳከም ሰርቷል " ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ፤ " ወታደራዊ አምባገንነት ታግሎ ዴሞክራሲያዊ እና ህዝባዊ መንግስት የጨበጠ ህዝብ ወደ ኋላ አይመለስም " ብሏል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን "  በሚል ስም የወጣውን መግለጫ " የጦርነት አዋጅ ነው ፤ በህዝብ ላይ አፋኝ አስተዳደር የሚጭን ተቀባይነት የሌለውና የውድቀት ጥሪ " ሲል ገልጾታል።

" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላቹሃል " ያለው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት " የጦርነት አዋጃችሁ የፕሪቶሪያ ስምምነት አፍርሶ ፤ ትግራይ ለአህጉራዊ ዓለምአቀፋዊ ተነጥሎ እና ውግዘት የሚዳርግ ህዝቡን ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ሲል አክሏል።

የአነ አቶ ጌታቸው ቡድን መግለጫውን መላ የትግራይ ኃይል አባላት እንዲያወግዙት ጠይቆ " ህዝብን እና መንግስታችሁ በሚስጡዋችሁ አቅጣጫ ብቻ እንድትንቀሳቀሱ ጥሪያችን እናቀርባለን " ሲል አሳስቧል።

ህዝቡ እና ወጣቱ በአደገኛ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም ገልጾ ይህንኑ በመገንዘብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትግሉ በማጠናከር ለመብቱ ለአንድነቱ እና ለህልውናው በመታገል የተደቀነበት አደጋ እንዲመከት ጥሪ አቅርቧል።

ለህዝቡ ፣ ለዳያስፓራ ፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ስም የወጣው መግለጫ እንዲያወግዙት ጠይቀዋል።

መግለጫውን ያወጡት አመራሮች ያለፈ ታሪካቸው ከሚያጎድፍ ተግባር በመውጣት አሁን የፈፀሙት ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርሙ እና ታሪካቸው እንዲያድሱ ጥሪ አቅርቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል የተሰጠው መግለጫ የሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃሳብ እና ውሳኔ እንዳልሆነ ለኢትዮጵያ መንግስት  እናሳውቃለን "  - የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ 

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው መግለጫ ተፈፃሚነት እንዳይኖረው (null and void እንዲሆን) ወስኗል። 

" በሰራዊቱ የኮር አመራር የሚል አደረጃጀት እውቅና የለውም " ሲል የወሰነው ካቢነኔው  " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ጥር 14/2017 ዓ.ም የተሰጠውን መግለጫ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጎታል።

ካቢኔው ዛሬ ቅዳሜ ጥር 17/2017 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ ፤ "የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው መግለጫ ፦
- ለአንድ ቡድን የወገነ
- መንግስት የሚፈርስ
- ሰራዊት የሚበትን
- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የሚያፈርስ እና መሰረታዊ ችግር ያለው በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲታረም እና ታች ወርዶ እንዳይተገበር ወስኗል። 

" የተሰጠው መግለጫ ከሰራዊት ተልእኮ ያፈነገጠ ፣ ተቋማዊ አሰራር የጣሰ " ነው "ሲል የገለፀው ካቢኔው ፥ " ' አመራር ነኝ ' በሚል በዚህ ሁኔታ ተሰብስቦ ውሳኔ ለማሳለፍ የሚያስችል ስልጣን የለውም " ብሏል።

" ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል በተሰጠው መግለጫ መንግስታዊ ማስተካከያ እንዲደረግ አስመልክቶ የቀረበው አቋም የአንዱ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት ሲባል የፕሪቶሪያ ውል የሚያፈርስ ሃላፊነት የጎደለው ውሳኔ ነው " አደገኛ ነው ' ሲል ገልጾ በአስቸኳይ የሚታረምበት አቅጣጫ ማስቀመጡን አሳውቋል።
  
ካቢኔው ባወጣው የውሳኔ መግለጫ ለኢትዮጵያ መንግስት ባስተላለፈው መልእክት " ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል በተሰጠው መግለጫ የሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃሳብ እና ውሳኔ አይደለም በመሆኑም ወድቅ አድርጎታል ፤ ሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር  አሁንም ለፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተገዢ በመሆን ጅምር ሰላሙ እንዲጎለብት የትግራይ ሉአላዊ ግዛት ተከብሮ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የጀመረውን ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል " ብሏል።

" የትግራይ ህዝብና ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፍላጎት ሰላም ነው " ሲል ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ መልእክት ያስተላለፈው ካቢኔው ፤ " የፕሪቶሪያ የሰላም ውል በአፈፃፀም ብዙ ችግሮች ቢኖሩትም በስምምነቱ አፈፃፀም የሚነሱ ችግሮች በሰላማዊ እና ፓለቲካዊ ትግል እንዲመለሱ የአለም አቀፍ ማህበረሰብ የተሟላ ድጋፍ እንዲያደርግ " ሲል ጥሪ አስተላልፏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ ነው " - የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ የህዝቡ ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦችላይ  የማያዳግም አርምጃ እንደሚወሰድ የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ በጥብቅ አስጠነቀቀ። ቢሮው " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14 /2017 ዓ.ም ያወጡትን መግለጫ ተከትሎ " የማያሻማ የመግለጫውን ትርጉም…
#Update

🚨 " ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የተፈቀደ የተጠራ ሰልፍ የለም " - የትግራይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት

🔵 " እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም መቐለ ጨምሮ በመላው ትግራይ የሚካሄደው ሰልፍ መግባባት የተደረሰበት እና የተሟላ ጥበቃ የሚደረገበት ነው " - በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት

🔴 " ህወሓት ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በቂ ጥበቃ ለመስጠት ስለምንቸገር ቀን እንዲቀይር እናስታውቃለን " - የትግራይ ፓሊስ ኮሚሽን


እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም ጥር 14/2017 ዓ.ም " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚደግፍ እና የሚቃወም ሰልፍ መጠራቱን ተከትሎ ፓሊስ ሰልፉን መሸፈን የሚችል የሰው ሃይል ስለሚያንሰው እንዲቀየር ጠይቀዋል።

ይሁን እንጂ ጥር 17/2017 ዓ.ም ፓሊስ የሰጠው የሰልፍ ክልከላ ማሳሰብያ በመጣስ በትግራይ ደቡባዊ ዞን የተለያዩ ከተሞች " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂደዋል።

እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚደግፍ ሰላማዊ ስልፍ እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል።

የክልሉ ፓሊስ " በቂ ጥበቃ ስለሌለኝ ሰላማዊ ስልፍ የሚካሄድበት ቀን እንዲቀየር " ቢያሳስብም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ሰልፉ የተሟላ የፀጥታ ጥበቃ ያለውና ተፈፃሚ የሚሆን ሲል የፅሁፍ መግለጫ ሰጥቷል።

" እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም መንግስት በመቐለ የጠራው ሰብሰባም ይሁን ሰልፍ የለም " ያለው የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ፤ " ሰልፍ ይካሄዳል " በማለት ቤት ለቤት እየተዘዋወሩ የሚያደናግሩት አካላት እና ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🚨#Alert ከደቂቃዎች በፊት ከፍ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቷል። ንዝሩት በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ተሰምቷል። ቃላቸውን የላኩልን የቤተሰባች አባላት " ዛሬ በጣም የሚያስፈራ ነበር። ሰሞኑን ድግግሞሹ ቀንሶ ነበር። ዛሬ በድንገት በሚያስፈራ ሁኔታ ነው የተሰማን " ብለዋል። @tikvahethiopia
#Update

ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት (4:38 ላይ) ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 36 ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንደሆነ የጀርመኑ የጂኦሳይንስ ሪሰርች ማዕከል ገልጿል።

መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.9 መመዝገቡን አሳውቋል።

በርካታ ሰዎች የዛሬው ከወትሮው የተለየ ነበር ብለዋል።

የመሬት መንቀጥቀጡ የነበረበት አካባቢ ያሉ ወገኖች " አስፈሪ " ሲሉ ገልጸዋል።

ንዝረቱ የተሰማባቸው አካባቢዎች ደግሞ ከወትሮው የተለየ እንደነበር ታውቋል።

ለአብነት አዲስ አበባ ብዙ ሰዎች ህንጻ ላይ የነበሩ ተሰምቷቸው መደናገጣቸውን ገልጸውልናል። ለተወሰኑ ሰከንዶች የቆየ ቢሆንም የህንጻ ንቅናቄ ስሜት ፣ የመንስታወት መርገፍገፍ እንደተመለከቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አንድ የቤተሰባችን አባል " 4ኛ ፎቅ ላይ በተቀመጥኩበት መስታወቱ ፣ የቤት እቃዎች ሲነቃነቁ፣ እኔም በተቀመጥኩበት በወትሮ በተለየ ንዝረት ሲሰማኝ ነበር " ብሏል።

ሌላ 12ኛ ፎቅ ላይ የነበረ የቤተሰባችን አባል " ያስፈራ ነበር " ሲል ክስተቱን አስረድቷል።

ከዚህ ባለፈ ንዝረቱ ከተሰባቸው ቦታዎች አንዱ የጅሌ ጥሙጋ አካባቢ ሲሆን የወረዳ አስተዳደር ህንፃ ላይ የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች በድንጋጤ ከህንጻው መውረዳቸውን ከሰራተኞቹ ለመረዳት ተችሏል።

Photo Credit - Omer Al Faruq

@tikvahethiopa
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 " ዩኒቨርሲቲያችን እንደ ሁሉም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም ነዉ " - የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ➡️ " ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እንዳንገባ ተደርገናል በዚህም ምክንያት በሁለት መስጊዶች ተጠልለን እንገኛለን " - ሙስሊም ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት የእስልምና እምነት ተከታይ / ሙስሊም…
#Update

“ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡

ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር።

ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ?

ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል።

" በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል።

በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡

በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡

የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ?

" በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡

በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡

አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡

የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል
" ብሏል፡፡

የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት  ዕጩ ሆነው ቀረቡ። በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም  ፓርላማ ቀርበዋል። ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። አቶ…
#Update

አቶ ብርሃኑ አዴሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።

ለሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮምሽነር በመሆን የተመረጡት አቶ ብርሃኑ በህዝብ ተወካዮሽ ምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።

አቶ ብርሃኑ የቀድሞው የምክር ቤት አባል የነበሩ ሲሆን የአዕምሯዊ ንብረት ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር፣ በኢህአዴግ ዘመን የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።

ላለፉት 10 ዓመታት ደግሞ በጥብቅና በህግ ማማከር ስራ ላይ ቆይተዋል።

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር የነበሩት ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የስራ ዘመናቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ራኬብ መሰለ በተጠባባቂነት ተቋሙን ሲመሩ ነበር።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በመቐለ ኤፍ ኤም 104.4 ምንድነው የተፈጠረው ? " በመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ላይ የአፈና እና የስራ አመራር የማባረር ሙከራ " መደረጉን ጣቢያው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል። ሙከራው በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የመቐለ ከንቲባ እንዲሆኑ በተሾመቱ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ያስተባበሩት ነው ተብሏል። ዛሬ ጥር 21/2017 ዓ.ም የተካሄደው የአፈናና አመራር የመቀየር…
#Update

🔴" በ104.4 የመቐለ ኤፍኤም ያጋጠመው ችግር በመግባባት እንዲፈታ አድርጊያለሁ  ስልጣን መረከብ የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት ያክብር  " - የመቐለ ከተማ ፓሊስ 

" ሬድዮ ጣቢያችን ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ እንዲሆን አንፈቅድም " - የመቐለ FM አመራር

ጥሪ 21 / 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት 5 ታጣቂዎች አስከትሎ የመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያን ለመቆጣጠረ ሙከራ ያደረገው ሬድዮ ጣብያውን እንዲመራ የመቐለ አስተዳደር " ሹሞኛል " የሚል ግለሰብ እንደሆነ የሬድዮ ጣቢያው አመራሮች ተናግረዋል።

ታጣቂዎች አስከትሎ ሬድዮ ጣብያውን ለመረከብ ሲሞክር የተፃፈለት ደብዳቤ በቦታው ለነበሩ አመራሮች ማሳየት ባለመቻሉ ምክንያት ግርግር እንዲነሳ ምክንያት መሆኑ አመራሮቹ ያብራራሉ።

ዘግይቶ በተደረገው ማጣራት የሹመት ደብዳቤ ማቅረብ ያልቻለውና ሬድዮውን ለመምራት መመደቡ የጠቀሰው ግለሰብ  በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት የከተማዋ ከንቲባ እንዲሆኑ በተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) መመደቡ በቃል እንደጠቀሰላቸው አመራሮቹ ገልጸዋል።

ጉዳዩን ወደ መቐለ ፓሊስ በመውሰድ ጊዚያዊ መፍትሄ ማግኘት መቻላቸው ከምስጋና ጭምር አስታውቀዋል።

የጣቢያው አመራሮች " በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት በተሾመ ከንቲባ ሬድዮ ጣብያውን ለማስተዳደር መመደቡን የሚናገረው ግለሰብ የአገሪቱዋ የሚድያ ህግ በሚጥስ አካሄድ ከአንድ ክፍለ ከተማ ያሰባሰባቸው ታጣቂዎች በማስከተል የአፈና ተግባር ለመፈፀም መመኮሩ የህወሓት በሁለት መሰንጠቅ በክልሉ እያደረሰ ያለው ዘርፈ በዙ ችግር አንዱ ማሳያ ነው " ሲሉ አክለዋል።

" ከ15 ዓመት በላይ ያስቆጠረ እና ከ60 በላይ ሰራተኞች ያሉት የመንግስት የኤፍኤም ሬድዮ ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ አይሆንም " ያሉት አመራሮቹ በአገሪቱ የብሮድካስት ህግ የሚተዳደር ሚድያ መሆኑ በመግለፅ ተመሳሳይ አፈና እንዳይፈፀም በግለሰቡ እና በላከው አካል ላይ ክስ እና አገዳ እንዲጣል እንቅስቃሴ መጀመራቸው አስታውቀዋል።

የመቐለ ፓሊስ በፅሁፍ ባወጣው መግለጫ የአፈና ተግባሩን አውግዞ  ፤ ችግሩ በመግባባት መፍታቱን እና ወደ ሃላፊነት መምጣት የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት አክብሮ መሆን ይገባዋል ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ወደ ቀን መርሃግብር ተቀይረን እንድንማር ከመግባባት ላይ ተደርሷል " - ተማሪዎች

ሰሞኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) መረሃግብር በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በግል ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ አመልካቾች ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት " ተመዝግበንና አስፈላጊውን ክፊያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ዉስጥ ባለንበት ዩኒቨርሲቲው ' አናስተምራችሁም ' ብሎናል " ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ዩኒቨርሲቲዉ በበኩሉ ጉዳዩን ከትምህርት ሚንስቴር ጋር በመነጋገር ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፆልን ነበር።

ቅሬታ አቅርበዉ የነበሩ ተማሪዎችና ወላጆች በዛሬው ዕለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳስታወቁት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት መርሃግብሩን ከእረፍት ቀናት ወደ መደበኛ መርሃግብር በማዘዋወር ተማሪዎቹን ለማስተማር መወሰኑን አረጋግጠዋል።

" ዛሬ ተጠርተን ዉል ተፈራርመናል " ያሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) አመልካቾች " በዉሉ ላይ የተቀመጡ ጉዳዮች የመረሃግብሩ ከዕረፍት ቀናት (weekend) ወደ መደበኛ መቀየር ፣ አመልካቾች በግል ከፍለዉ የሚማሩ ስለመሆናቸው የሚገልፅ፣ ስለ ክፍያ አፈፃፀምና በዩኒቨርሲቲው እና በተማሪዎቹ መካከል ስለሚኖረዉ መብትና ግዴታ የሚደነግግ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የተማሪ ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ከከፍተኛ ጭንቅ ነዉ የገላገላችሁን፣ ምን እንደምናደርግ ጨንቆን ነበር ትምህርት ሚንስቴር እና የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲም ላሳያችሁን በጎ ምላሽ እናመሰግናለን " ብለዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በግል ከፍሎ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለሚወስዱ ተማሪዎች ያዘጋጀዉን ዉል በዚህ መረጃ ላይ ያካተትን ሲሆን የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት  ዶ/ር አክበር ጩፎ ስለጉዳዩ ትክክለኛነት ከመግለፅ ባለፈ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Update

" እስካሁን በህይወት የተገኘ የለም "

በአሜሪካ ፤ ዋሽንግቶን ዲሲ የመንገደኞች አውሮፕላን ከጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ በ " ፖቶማክ ወንዝ " ውስጥ ከተከሰከሰበት አደጋ የነፍስ አድን ሰራተኞች እስካሁን አንድም ሰው በህይወት አላገኙም።

የነፍስ አድን ስራው ግን መቀጠሉ ተነግሯል።

አውሮፕላኑ 60 መንገደኞችን እና 4 የበረራ ሰራተኞችን ይዞ ነው 3 ሰው ከያዘው የጦር ሂሊኮፕተር ጋር ተላትሞ የተከሰከሰው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በመቐለ ከተማ በከንቲባ ስም ማንኛውም ተግባር እንዳይፈፅም አስጠነቀቁ።

አቶ ጌታቸው በእፅንኦት ያስጠነቀቋቸው ባለፈው ጥቅምት 2017 ዓ.ም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት እጩ አቅራቢነት ከንቲባ በመሆን የተሾሙትን ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ነው።

ፕሬዜዳንቱ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ፅፈውት  ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም በተለያዩ የማህበራዊ የትስስር ገፆች ይፋ በሆነው የማስጠንቀቅያ ደብዳቤ ፤ በከተማዋ የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች በጊዚያዊ አስተዳደሩ ቅቡልነት ባጡ ከንቲባ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) በተፃፈ ደብዳቤ ማንኛውም ስራ መፈፀም የህግ ተጠያቂነት አንደሚያስከትልባቸው ያትታል።

ዶክተሩ ህገ-ወጥ ተግባራቸው እንዲያቆሙ የሚያሳስበው እና የሚያስጠነቅቀው ደብዳቤው ጊዚያዊ አስተዳደሩ የሚፃረር አቋም በመያዝ ከተማዋ መምራት አግባብነት የለውም ይላል። 

ስለሆነም በመቐለ ከተማ የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች በጊዚያዊ አስተዳደሩ ቅቡልነት በሌላቸው ከንቲባ የሚሰጣቸው ማንኛውም ዓይነት ትእዛዝ እንዳይቀበሉ የፕሬዜዳንቱ ደብዳቤ አስጠንቅቋል።

ህወሓት ለሁለት በመሰንጠቁ ምክንያት የመቐለ ከተማ ላለፉት 60 ቀናት ቢሮ ገብቶ የሚደራ ከንቲባ የላትም።

ህዳር 23/2017 ዓ.ም በጊዚያዊ አስተዳደሩ ደብዳቤ የተሾሙ ብርሃነ ገ/የሱስ አንድ ቀን ብቻ በአስተዳደሩ ግቢ ታይተው ለሁለተኛ ጊዙ አልተመለሱም።

በደብረፅዮኑ ህወሓት የተሾሙ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ከህዳር 23 /2017 ዓ.ም ጀምሮ ቢሮ አልገቡም።

የመቐለ ከንቲባ ቢሮ አሁንም ታሽጎ በፓሊሶች ይጠበቃል፤ የከተማዋ ነዋሪ ደግሞ ከከንቲባ ማግኘት የሚገባውን አገልግሎት አጥቶ አቤቱታውን ለማን ማቅረብ እንዳለበት ግራ ገብቶት ይገኛል። 

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#Update

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የአማካሪ ካውንስል ምክር ቤት በይፋ ተመሰረተ።

ምክር ቤቱ ሰብሳቢ እና ምክትል ሰብሳቢ የመረጠ ሲሆን የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ሊቀመንበር ደጀን በርሀ (ዶ/ር) በከፍተኛ ድምፅ ምክትል ሰብሳቢ ሆነው ተመርጠዋል። 

የአማካሪ ካውንስል ምክር ቤት የማቋቋም ሃሳብ የክልሉ ምክር ቤት የሚያፈርሰው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተከትሎ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ማቋቋምያ ሰነድ ጥር 2015 ዓ.ም ሲፀድቅ የተነሳ ሃሳብ ነው።  

ሃሳቡ በድጋፍ እና በተቃውሞ ለሁለት አመታት ያህል ሲናጥ ቆይቶ ዛሬ ጥር 25/2017 ዓ.ም በይፋ ተመስርቶ መሪዎቹ መርጠዋል። 

በምስረታ ካውንስሉ መልእክት ያስተላለፉት ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ፤ በክልሉ የሚገኙ የኢሮብ እና ኩናማ ብሄረሰቦች የተወከሉበት ካውንስሉ ዘግይቶም ቢሆንም መመስረቱ መልካም ሆኖ አቃፊ ፣ አሳታፊ እና የሃሳብ ብዙህነት የሚንሸራሸሩበት መድረክ መሆን ይገባዋል ብለዋል። 

የአማካሪ ካውንስል ምክር ቤቱ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የተቀመጡት የትግራይ ህዝብ ጥቅሞች በተሻለ እና በአስተማማኝ እንዲመለሱ አጋዥ ሃይል ለማሰባሰብ አልሞ መቋቋሙን የጠቆሙት ፕሬዜዳንቱ " ልዩነቶቻችን በማጠበብ ለተሻለ ነገ በጋራ መስራት ወቅታዊ የትግራይ ጥያቄ ነው "  ብለዋል። 

የካውንስሉ እድሜ የጊዚያዊ አስተዳደሩ የቆይታ ጊዜ መሆኑ ያስረዱት ፕሬዜዳንት ጌታቸው ይህንን ታሳቢ በማድረግ የትግራይ ፓለቲካዊ ምህዳር ማስፋት እና ለነገ ማመቻቸት ዋነኛ ስራው መሆን እንደሚገባ አክለዋል።   

ካውንስሉ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራዎች መሬት ላይ እንዲወርዱ አጋዥ ሚና ከመጫወት በተጨማሪ የትግራይ ተደማጭነት እና የመደራደር አቅም የሚያጠናክር አቅጣጫ መከተል ይገባዋል ብለዋል ፕሬዜዳንቱ። 

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አማካሪ ካውንስል ምክር ቤት ለመምራት ሰብሳቢ እና ምክትል ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡት ቃለ ማህላ ፈፅሟል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አማካሪ ካውንስል ምክር ቤት መመስረት በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት እና ሳልሳይ ወያነ ፓርቲ እና ሌሎች ተቃውሞውታል

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴" በ104.4 የመቐለ ኤፍኤም ያጋጠመው ችግር በመግባባት እንዲፈታ አድርጊያለሁ  ስልጣን መረከብ የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት ያክብር  " - የመቐለ ከተማ ፓሊስ  " ሬድዮ ጣቢያችን ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ እንዲሆን አንፈቅድም " - የመቐለ FM አመራር ጥሪ 21 / 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት 5 ታጣቂዎች አስከትሎ የመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያን…
#Update

" ህጋዊ ስራ አስኪያጅ እኔ ነኝ ወደ ስራ ቦታየ እንዳልገባ ፓሊስ ከልክሎኛል " - የ104.4 ኤፍ ኤም መቐለ ሹመኛ መሆናቸውን የሚናገሩት ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ

" ሹመኛ ነኝ " ያሉት በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በመቐለ ከተሾመው ከንቲባ በኋላ ህዳር 2017 ዓ.ም የኤፍ ኤም ሬድዮው ስራ አስኪያጅ ሆኖው መመደባቸው የገለጹት ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ የከተማዋ ፓሊስ ወደ ስራ ቦታቸው እንዳይገቡ መከልከሉ " አግባብ " አይደለም ብለዋል።

ለኤፍኤም ሬድዮ ጣብያው የከተማዋን ምክር ቤት እና አሰራር በጣሰ መልኩ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ወዲህ ሦስት ስራ አስኪያጆች መመደባቸው የገለፁት ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ ይህ አካሄድ እንዲታረምና ወደ ስራቸው እንዲገቡ ጠይቀዋል።

ከተመደቡበት ወርሃ ህዳር 2017 ዓ.ም ሦስቴ ወደ ስራ ገበታቸው ለመግባት ያደረጉት ጥረት በኤፍ ኤም ሬድዮው በሚገኙ አመራሮች መስተጓጉሉም አምርረው የነቀፉት ዘመንፈስቅዱስ ከጥር 22/2017 ዓ.ም በኋላ ወደ ስራ ገበታቸው ለመግባት ያደረጉት ጥረት ከዛ በፊት አይተዋቸው የማያውቁ ታጣቂዎች ተመድበው  እንደተደናቀፋባቸው በምሬት ተናግረዋል። 

104.4 የመቐለ ኤፍኤም ከተማዋ ባቋቋመው ቦርድ የሚመራ እንደሆነ የጠቀሱም ሱሆን " ቦርዱ እኔ ህጋዊ ስራ አስኪያጅ አድርጎ ሹመኛል ስለሆነም ስራዬን እንድሰራ በጣብያው ያሉ ህገ-ወጦች ስርዓት መያዝ አለባቸው " ብለዋል።

ጥር 22/2017 ዓ.ም በ104.4 ኤፍ ኤም መቐለ ቅጥር ግቢ " እኔን ነኝ ህጋዊ ሹመኛ ... እንተ አይደለህም " በሚል በተፈጠረ ግርግር ፓሊስ ደርሶ በውይይት መፍታቱ መዘገባችን ይታወሳል።

የወዝግቡ መነሻ ለሁለት ከተከፈሉት የህወሓት አመራሮች የሚያያዝ ሆኖ በጣብያው የሚገኙ አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ቅቡልነት ያላቸው ፤ አዲሱ ተሿሚ ደግሞ በድብረፅዮኑ ህወሓት ድጋፍ ያላቸው ናቸው።

በ2001 ዓ.ም የተቋቋመው 104.4 የመቐለ ኤፍ ኤም በአገሪቱዋ የሚድያ ህግ የተቋቋመ እና በየአመቱ ተገቢ ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት መሆኑ ይታወቃል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቐለ " ተጠርጣሪው ተይዞ ለክልሉ ፖሊስ ተላለልፎ ተሰጥቷል " - ፖሊስ የ19 ዓመትዋን ወጣት በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በፓሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል። የመቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጸው ፥ ጥቅምት 19 /2017 ዓ.ም ሓበን የማነ የተባለች ፍቅረኛውን በተከራዩት የሆቴል ክፍል በጬቤ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ ከቀናት ፍለጋ በኃላ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል። በአሰቃቂ…
#Update

የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል !

ሓበን የማነ የተባለች ወጣትን በጭካኔ በመግደል ክስ የተመሰረተበት ዳዊት ዘርኡ የተባለ ወንጀለኛ ዛሬ ጥር 28/2017 ዓ.ም በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተፈርዶበታል።

ፍርዱን ያሳለፈው የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ነው።

አሰቃቂ ግድያው በትግራይ ፣ መቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ዓዲሓ ተብሎ በሚጠራው ልዩ ሰፈር በሚገኝ የአንድ ሆቴል ክፍል ነበር የተፈፀመው።

ሓበን የማነ የ19 ዓመት ወጣት ስትሆን በሆቴል ክፍል በቢላዋ ተገድላ መገኘቷንና ጥቅምት 20 /2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ የቀብር ስነ-ሰርዓት መከናወኑ በወቅቱ መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።

ፓሊስ አሰቃቂ የግድያ ተግባሩ አስመልክቶ በወቅቱ በሰጠው መረጃ ፤ የነፍስሄር ወጣት ሓበን የማነ አስከሬን ከ2 ቀን በኋላ ነው በተገደለችበት የሆቴል ክፍል የተገኘው።

ገዳይ ወንጀለኛው አሰቃቂ ተግባሩ በመቐለ ከተማ ከፈፀመ በኋላ በአማራ ክልል በኩል በድብቅ ለውጣት ሲያሴር ደሴ ከተማ በአማራ ክልል ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውሎ ለትግራይ ክልል ፓሊስ ተላልፎ ተሰጥቷል።

በወቅቱም ለደሴ ህዝብና ለአማራ ክልል ፖሊስ ምስጋና ቀርቦ ነበር።

ፓሊስ ጉዳዩ  አጣርቶ አቃቤ ህግ ክሰ መስርቶ ሲከራከር ከቆየ በኋላ ዛሬ እሮብ ጥር 28/2017 ዓ.ም የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ባዋለው ችሎት ወንጀለኛው በዕድሜ ልክ ፅኑ አስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia