TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላችኋል " - በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት

በምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ፤ ትናንት ጥር 15/2017 ዓ.ም  " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠውን መግለጫ የሚቃወም መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም መግለጫው ፥ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት" የነሃሴው " ብሎ ሲጠራው ራሱን ደግሞ " ነባር " በማለት ገልጿል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን "  በሚል ያወጡት መግለጫ የ " ነሃሴው ህወሓት ህዝቡን እና ሰራዊቱ ለመበታተነ የሰራው ክፋት ውጤት ነው " በማለት ገልፆታል።

" የነሃሴው ህወሓት ህዝብን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያልተቀበለው ጉባኤ  በማካሄድ ነባሩን ህወሓት እንዲዳከም ሰርቷል " ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ፤ " ወታደራዊ አምባገንነት ታግሎ ዴሞክራሲያዊ እና ህዝባዊ መንግስት የጨበጠ ህዝብ ወደ ኋላ አይመለስም " ብሏል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን "  በሚል ስም የወጣውን መግለጫ " የጦርነት አዋጅ ነው ፤ በህዝብ ላይ አፋኝ አስተዳደር የሚጭን ተቀባይነት የሌለውና የውድቀት ጥሪ " ሲል ገልጾታል።

" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላቹሃል " ያለው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት " የጦርነት አዋጃችሁ የፕሪቶሪያ ስምምነት አፍርሶ ፤ ትግራይ ለአህጉራዊ ዓለምአቀፋዊ ተነጥሎ እና ውግዘት የሚዳርግ ህዝቡን ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ሲል አክሏል።

የአነ አቶ ጌታቸው ቡድን መግለጫውን መላ የትግራይ ኃይል አባላት እንዲያወግዙት ጠይቆ " ህዝብን እና መንግስታችሁ በሚስጡዋችሁ አቅጣጫ ብቻ እንድትንቀሳቀሱ ጥሪያችን እናቀርባለን " ሲል አሳስቧል።

ህዝቡ እና ወጣቱ በአደገኛ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም ገልጾ ይህንኑ በመገንዘብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትግሉ በማጠናከር ለመብቱ ለአንድነቱ እና ለህልውናው በመታገል የተደቀነበት አደጋ እንዲመከት ጥሪ አቅርቧል።

ለህዝቡ ፣ ለዳያስፓራ ፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ስም የወጣው መግለጫ እንዲያወግዙት ጠይቀዋል።

መግለጫውን ያወጡት አመራሮች ያለፈ ታሪካቸው ከሚያጎድፍ ተግባር በመውጣት አሁን የፈፀሙት ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርሙ እና ታሪካቸው እንዲያድሱ ጥሪ አቅርቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#ንጉስማልት
አፍ ላይ ቀለል ብሎ የሚጠጣ ፣ ልብን በደስታ የሚሞላ ፣ ልዩ ጣዕም!

ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.iss.one/Negus_Malt

#ደስደስበንጉስ #nonalcoholic #ከአልኮልነፃ
" ከእርዳታዎች ጋር በተያያዘ በአስቸኳይ የሥራ ማቆም ትዕዛዞችን አስተላልፉ " - ሾልኮ የወጣው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ደብዳቤ

የአሜሪካ መንግሥት የውጭ እርዳታ እንዲቆም መወሰኑን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ለባለስልጣናት እና ለውጭ አገራት ለሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች የላከው የውስጥ ማስታወሻ እንዳሳየ ቢቢሲ ዘግቧል።

ቢቢሲ ሾልኮ የወጣውን ይህ ማስታወሻ መመልከቱን ገልጿል።

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የውጭ ፖሊሲያቸው ውጤታማነት እና ወጥነት እስኪገመገም ድረስ ለ90 ቀናት የውጭ የልማት ድጋፍ እንዲቆም ባለፈው ሰኞ ዕለት የሥራ አስፈጻሚ ትዕዛዝ አስተላልፈው ነበር።

የእርዳታ ማቆም ውሳኔውም ይህንን የተከተለ ነው።

አሜሪካ ከዓለማችን ትልቁ ዓለም አቀፍ እርዳታ ለጋሽ ስትሆን በእኤአ 2023 ፤ 68 ቢሊዮን ዶላር ማውጣቷን ከመንግሥት የተገኘ መረጃ ያስረዳል።

የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ያስተላለፈው ትዕዛዝ ከልማት እርዳታ እስከ ወታደራዊ ድጋፍ ድረስ የሚሸፍን ሊሆን እንደሚችል የጠቆመ ነው።

ሾልኮ የወጣው የውስጥ ማስታወሻ ለድንገተኛ የምግብ ዕርዳታ እንዲሁም
#ለእስራኤል እና #ለግብጽ ወታደራዊ ድጋፍ በስተቀር ሁሉም የውጭ ልገሳዎች እንዲቆሙ የሚያዝ ነው።

በውጭ አገራት ላሉ የአሜሪካ ኤምባሲዎች የተላከው የውስጥ ማስታወሻ ፤ " እያንዳንዱ አዲስ የገንዘብ ድጋፍ ወይም ማራዘሚያ እስካልተገመገመ እና እስኪጸድቅ ድረስ አይለቀቅም " ይላል።

የአሜሪካ ባለስልጣናት " ከእርዳታዎች ጋር በተያያዘ በአስቸኳይ የሥራ ማቆም ትዕዛዞችን እንዲያስተላልፉ እና ይህም ግምገማውን ተከትሎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ እስኪወስንበት ጊዜ ድረስ የሚቆይ ይሆናል " ሲልም ያትታል።

በተጨማሪም እርዳታዎች የፕሬዚዳንት ትራምፕን የውጭ ፖሊሲ ግቦች የተከተሉ መሆናቸውን ለማረጋገጥ በሁሉም የውጭ እርዳታዎች ላይ ሰፋ ያለ ግምገማ በ85 ቀናት ውስጥ እንዲጠናቀቅ ያዛል።

አዲሱ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ፤ " አሜሪካ በውጭ አገራት ገንዘብ ማውጣት ያለባት አገራችንን ጠንካራ፣ ደኅንነቷ የተጠበቀ ወይም የምትበለጽግ  ካደረገ ብቻ ነው " ሲሉ ከዚህ ቀደም ተናግረው ነበር።

አንድ የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለስልጣን የእርዳታ ማቆም ውሳኔው በአሜሪካ ልገሳ በሚደረግላቸው የውጭ እርዳታ ፕሮግራሞች ላይ " ከበድ ያለ ተጽዕኖ " እንዳለው መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል የተሰጠው መግለጫ የሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃሳብ እና ውሳኔ እንዳልሆነ ለኢትዮጵያ መንግስት  እናሳውቃለን "  - የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ 

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው መግለጫ ተፈፃሚነት እንዳይኖረው (null and void እንዲሆን) ወስኗል። 

" በሰራዊቱ የኮር አመራር የሚል አደረጃጀት እውቅና የለውም " ሲል የወሰነው ካቢነኔው  " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ጥር 14/2017 ዓ.ም የተሰጠውን መግለጫ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጎታል።

ካቢኔው ዛሬ ቅዳሜ ጥር 17/2017 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ ፤ "የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው መግለጫ ፦
- ለአንድ ቡድን የወገነ
- መንግስት የሚፈርስ
- ሰራዊት የሚበትን
- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የሚያፈርስ እና መሰረታዊ ችግር ያለው በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲታረም እና ታች ወርዶ እንዳይተገበር ወስኗል። 

" የተሰጠው መግለጫ ከሰራዊት ተልእኮ ያፈነገጠ ፣ ተቋማዊ አሰራር የጣሰ " ነው "ሲል የገለፀው ካቢኔው ፥ " ' አመራር ነኝ ' በሚል በዚህ ሁኔታ ተሰብስቦ ውሳኔ ለማሳለፍ የሚያስችል ስልጣን የለውም " ብሏል።

" ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል በተሰጠው መግለጫ መንግስታዊ ማስተካከያ እንዲደረግ አስመልክቶ የቀረበው አቋም የአንዱ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት ሲባል የፕሪቶሪያ ውል የሚያፈርስ ሃላፊነት የጎደለው ውሳኔ ነው " አደገኛ ነው ' ሲል ገልጾ በአስቸኳይ የሚታረምበት አቅጣጫ ማስቀመጡን አሳውቋል።
  
ካቢኔው ባወጣው የውሳኔ መግለጫ ለኢትዮጵያ መንግስት ባስተላለፈው መልእክት " ' የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን ' በሚል በተሰጠው መግለጫ የሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃሳብ እና ውሳኔ አይደለም በመሆኑም ወድቅ አድርጎታል ፤ ሰራዊቱ እና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር  አሁንም ለፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተገዢ በመሆን ጅምር ሰላሙ እንዲጎለብት የትግራይ ሉአላዊ ግዛት ተከብሮ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የጀመረውን ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል " ብሏል።

" የትግራይ ህዝብና ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፍላጎት ሰላም ነው " ሲል ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ መልእክት ያስተላለፈው ካቢኔው ፤ " የፕሪቶሪያ የሰላም ውል በአፈፃፀም ብዙ ችግሮች ቢኖሩትም በስምምነቱ አፈፃፀም የሚነሱ ችግሮች በሰላማዊ እና ፓለቲካዊ ትግል እንዲመለሱ የአለም አቀፍ ማህበረሰብ የተሟላ ድጋፍ እንዲያደርግ " ሲል ጥሪ አስተላልፏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
Are you a bold innovator with a vision to contribute to Africa's economic prosperity? 🌍
The Jasiri Talent Investor Program is seeking exceptional entrepreneurs from Ethiopia🇪🇹,Kenya🇰🇪, Rwanda🇷🇼. We're looking for individuals with the potential to build high-impact ventures that disrupt industries, open new markets, and redefine how we live and work.

Check out our ideal candidate profile to see if you have what it takes to join Cohort 8.

To apply visit, https://jasiri.org/jasiri-talent-investor/
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ ነው " - የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ

የህዝቡ ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦችላይ  የማያዳግም አርምጃ እንደሚወሰድ የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ በጥብቅ አስጠነቀቀ።

ቢሮው " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14
/2017 ዓ.ም ያወጡትን መግለጫ ተከትሎ " የማያሻማ የመግለጫውን ትርጉም ወደ ጎን በመተው ለራሳቸው የፓለቲካ ማራመጃ በማለም  ጉዳዩን እያወሳሰቡት ይገኛሉ ብሏል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14 / 2017 ዓ.ም ያወጡት መግለጫ የድጋፍ እና ተቃውሞ ሰልፍ የሚያስፈልገው እንዳልሆነ የጠቀሰው ቢሮው " መግለጫውን የተለያዩ ትርጉሞች በመሰጠት ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ እየተመለከትን ነው " ሲል ገልጿል።

በተለያዩ አደረጃጀቶች ስም ተሸፍኖ በአንዳንድ ግለሰቦች እየተሰጠ እና እየተሰራጨ ያለውንና  " የበላይ ወታደራዊ  ኃይል አመራሮች " የሰጡት መግለጫ አቋም የማይወክሉ መልእክቶች በአስቸኳይ መታረም አለባቸው ብለዋል ቢሮው።

በተሳሳቱ ቅስቀሳዎች ህዝቡን ወደ ሁከት እና ብጥብጥ የሚመሩ ብሎም ስርአት አለበኝነት እንዲነገስ የሚሯሯጡ አካላት ወደ ቀልባቸው እንዲመለሱ እና ከማንኛውም ህገ-ወጥ ተግባር እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

" ያለውን ሁኔታ የሌለውን መልክ በማስያዝ ፦
- ሰልፍ ማደራጀት ፣
- የመንግስት አገልግሎት ማስተጓጎል እና ማቋረጥ ፣
- መንገድ በመዝጋት እንቅስቃሴ ማወክ እና ማደናቀፍ፣
- ሃይል በመጠቀም የግል ፍላጎት ለማሳካት የሚደረግ እንቅስቃሴ ፍፁም የማይፈቅድ መሆኑ አጥብቆ አሳስቧል።

ህዝቡ ከዚህ መሰል ተግባር እንዲርቅ ወደ ህገ-ወጥ ተግባሩ የሚቀላቀሉ እንዲመክር እና እንዲገስፅ ፤ምክር እና ተግሳፁን በመጣስ ወደ ሁከት እና ግርግር የሚገቡት ደግሞ እንዲኮንን ጥሪ አቅርቧል።

ቢሮው የሚያቀርበው ምክር እና መረጃ ወደ ጎን በመተው በድጋፍ እና ተቃውሞ ስም ወደ ጥፍት በሚገቡትንና በአስተባባሪዎቻቸው ላይ ስርአት የማስከበር ስራ ይሰራል ብሏል።

የህዝቡን ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቀዋል።


@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ ነው " - የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ የህዝቡ ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦችላይ  የማያዳግም አርምጃ እንደሚወሰድ የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ በጥብቅ አስጠነቀቀ። ቢሮው " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14 /2017 ዓ.ም ያወጡትን መግለጫ ተከትሎ " የማያሻማ የመግለጫውን ትርጉም…
#Update

🚨 " ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የተፈቀደ የተጠራ ሰልፍ የለም " - የትግራይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት

🔵 " እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም መቐለ ጨምሮ በመላው ትግራይ የሚካሄደው ሰልፍ መግባባት የተደረሰበት እና የተሟላ ጥበቃ የሚደረገበት ነው " - በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት

🔴 " ህወሓት ለእሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በቂ ጥበቃ ለመስጠት ስለምንቸገር ቀን እንዲቀይር እናስታውቃለን " - የትግራይ ፓሊስ ኮሚሽን


እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም ጥር 14/2017 ዓ.ም " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚደግፍ እና የሚቃወም ሰልፍ መጠራቱን ተከትሎ ፓሊስ ሰልፉን መሸፈን የሚችል የሰው ሃይል ስለሚያንሰው እንዲቀየር ጠይቀዋል።

ይሁን እንጂ ጥር 17/2017 ዓ.ም ፓሊስ የሰጠው የሰልፍ ክልከላ ማሳሰብያ በመጣስ በትግራይ ደቡባዊ ዞን የተለያዩ ከተሞች " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂደዋል።

እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠው ውሳኔ የሚደግፍ ሰላማዊ ስልፍ እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል።

የክልሉ ፓሊስ " በቂ ጥበቃ ስለሌለኝ ሰላማዊ ስልፍ የሚካሄድበት ቀን እንዲቀየር " ቢያሳስብም በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ሰልፉ የተሟላ የፀጥታ ጥበቃ ያለውና ተፈፃሚ የሚሆን ሲል የፅሁፍ መግለጫ ሰጥቷል።

" እሁድ ጥር 18/2017 ዓ.ም መንግስት በመቐለ የጠራው ሰብሰባም ይሁን ሰልፍ የለም " ያለው የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ፤ " ሰልፍ ይካሄዳል " በማለት ቤት ለቤት እየተዘዋወሩ የሚያደናግሩት አካላት እና ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
' ልጄን ትተህ እኔን ብላኝ ! '

🙏" ከእግዚአብሔር በታች እኔና ልጄን የታደገችን ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ናት " - መምህርት ደንበሌ አስራት

➡️" እናትና ልጅን ለማዳን ከ10 ደቂቃ በላይ ከጅቡ ጋር ታግለናል" - ወ/ሮ መቅደስ ተካ


ከሰሞኑ መምህርት ደንበሌ አስራት የተባሉ እናት በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ 'ጃሎ ናራሞ ' ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ የ12 ዓመት ልጃቸዉን ሊበላ ከያዘ ጅብ ጋር በመታገል ልጇን ማዳኗን ሲዘገብ ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ወደ መምህርት ደንበሌ አስራት የእጅ ስልክ በመደወል ስለጉዳዩ ጠይቋቸዋል።

መምህርት ደንበሌ ስለ ጉዳዩ ሲያስረዱ" ጥር 11/2017 ዓ/ም ረፋድ 3 ሠዓት አከባቢ ዉሃ ለመቅዳት ከልጄ ጋር ሽላንሻ ወደተባለው ምንጭ በወረድንበት አጋጣሚ ነበር አፉ በደም የተለወሰ አንድ ጅብ ወደ እኛ በመምጣት በእኔና በጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ መሃል የነበረዉን የ12 ዓመት ሕፃን እግር ነክሶ በመያዝ ወደ ጫካ ዉስጥ መጎተት ሲጀምር ዐይኔ እያዬ ልጄን አይበላብኝም በማለት ቀኝ እጄን የጅቡ አፍ ዉስጥ በመክተት 'ኤ ሲቴ' ኤ ሲቴ'በሀዲየኛ (ልጄን ትተህ እኔን ብላኝ) እያልኩ መጮህ ጀመርኩ " ብለዋል።

" ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ተካ በጄርካንና በመዘፍዘፊያ ጅቡን እየመቱ መጯጯህ ቀጠልን ፤ በመሃል ትግልና ጩኸታችን ስለበዛ ጅቡ እኔንም ልጄንም ትቶ ወደ ወ/ሮ መቅደስ ሲዞር አፉ ደም በደም ሆኖ ነበር " ሲሉ አስረድተዋል።

መምህርት ደንበሌ አስራት " እየጮህን ስንታገል የሰሙ ሰዎች ደርሰዉ ጅቡን በመግደላቸዉ እኛ ወደ ሆስፒታል ተወሰድን " ብለዋል።

" ከፈጣሪ በታች እኔንና ልጄን የታደገችን ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ናቸዉ " የሚሉት መምህርት ደንበሌ አስራት ለተደረገላቸው እገዛ ምስጋና አቅርበዋል።

ወ/ሮ መቅደስ ተካ በበኩላቸው " ልጅና እናቱን ከጅቡ አፍ ለማስጣል ከ10 ደቂቃ በላይ ታግለናል " ያሉ ሲሆን " የናቲቱ ወ/ሮ ደንበሌ ለልጇ መስዋዕት ለመሆን መዘጋጀት እኔም እናት ነኝና ሆዴን አባብቶ ጅቡን በጋራ ታግለን የከፋ አደጋ እንዳይደርስ አድርገናል" ብለዋል።

ከዚህ ቀደም አንዲት እናት ተመሳሳይ አደጋ በራሳቸዉ ላይ መድረሱን የሚያስታውሱት ሁለቱ እናቶች ከአደጋዉ ባሻገር በሀዲያ ዞን ዋና ከተማ ሆሳዕና ዉስጥ ሆነን " ከጅቦች ጋር ታግለን የምንጠቀመዉ የዉሃ ችግር እልባት ሊሰጠዉ ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል።

@tikvahethiopia
#MPESASafaricom

እኛ ለወዳጅ ለመላክ እንዘጋጅ እንጂ ብሩን ፈጥኖ በማድረስ M-PESA አለልን ፤ ከM-PESA ወደ M-PESA ገንዘብ ስንልክ ያለምንም የአገልግሎት ክፍያ በነፃ እንስተናገዳለን!

#FurtherAheadTogether
ከፍርድ ውጭ ግድያ፣ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ !

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሩብ ዓመት ሪፖርት በኢትዮጵያ በግጭት ዐውድ ውስጥ ያሉ አካባቢዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በተመለከተ።

@tikvahethiopia