#ኢትዮጵያ
" ' ወደ ውጪ እንልካችኋለን ' በሚል ምክንያት ' ተጭበርብረናል ፣ ተዘርፈናል ' እያሉ ቅሬታ የሚያቀርቡ ሰዎች ተበራክተዋል " - የአ/አ ፍትህ ቢሮ
አሁን አሁን በኢትዮጵያ በርካታ ሰዎች በተለይም ወጣቶች ወደ ውጭ ሀገራት የመሄድ ፍላጎታቸው እየተበራከተ መጥቷል።
እኚህ ወጣቶች ከሀገር ለመውጣት የተለያዩ ሙከራዎችንም ሲያደርጉ ይታያል።
የውጭ ጉዞ ለማድረግ ከሚሞክሩባቸው አንዱ መንገድ ደግሞ በደላሎች ፣ በጉዞ ወኪሎች እና በሌሎችም አማካኝነት ነው።
ወጣቶች በትምህርት ፣ በስራ እንዲሁም በጉብኝነት አማካኝነት ነው ከሀገር ለመውጣት የሚጥሩት።
የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ህይወት ለመቀየር ፣ አፍላ የሆነ የወጣትነት እድሜያቸው ሳያልፍ አንዳች ነገር አፍርተው ቤተሰብ መስርተው ጥሩ ኑሮ ለመኖር ፤ ከድህነት ለመላቀቅ ሲሉ በሚሞክሯቸው የውጭ ሀገር እድሎች ግን ምንም ርህራሄ በሌላቸው አጨበርባሪዎች ሲታለሉም ይታያል።
የወጣቶቹን ፍላጎት እያየ ገንዘባቸውን የሚበላቸው ፣ አውሮፓና አሜሪካ ብሎ ሌላ የወንጀልና ደህንነት የሌለው ቀጠና የሚልካቸው ደላላ፣ ወኪል እየበዛ መጥቷል።
በመዲናችን አዲስ አበባ ህገወጥ ስራን የሚሰሩ የጉዞ ወኪሎች መበራከት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፍትህ ቢሮ ለአሃዱ በሰጠው ቃል ፤ በየጊዜው የውጪ ሀገር የጉዞ ወኪልና አማካሪ ድርጅቶች እንዲሁም ደላሎች " ወደ ውጪ እንልካችኋለን " በሚል ምክንያት ' ተጭበርብረናል፣ ተዘርፈናል ' እያሉ ቅሬታ የሚያቀርቡ ሰዎች መበራከታቸውን አስታውቋል፡፡
እነዚህ ቅሬታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸው ተመላክቷል።
" እነዚህን ቅሬታዎች ተሰምተዉ ዝም የሚባልበት አግባብ የለም " ያለው ቢሮ በቀጥታ ለአዲስ አበባ እና ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በመላክ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየሰራሁ ነው ብሏል።
" በኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም ወደ አውሮፓ የሚሄዱ ሰዎች ፍላጎት መበራከቱን ተከትሎ፤ ዜጎች ከሕግ ውጪ በሚሰሩ ድርጅቶችና ደላሎች አማካኝነት ረብጣ ገንዘባቸውን መጭበርበራቸው እየተባባሰ ይገኛል " ነው ያለው።
በብዙዎች ጥቆማና ቅሬታ መሰረት፤ ከዚህ ቀደም ከ40 በላይ ሕገ-ወጥ ሥራን በመስራት የተሰማሩ የውጪ ሀገር የጉዞ ወኪሎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ቢሮው አመልክቷል።
ፍትህ ቢሮ ፤ " ህብረተሰቡ በተለያየ መንገድ ወደ ውጪ ለመውጣት ሲፈልግ፤ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሕጋዊ የሆኑ ወኪሎችን ለይቶ ስላሰራጨ፤ በተለያዩ ማህበራዊ ሚድያዎች ላይ ማግኘት ይችላል " ብሏል።
አልያም በአካል ቀርቦ መረጃ እንዲያገኝ ለአሃዱ በሰጠው ቃል አሳስቧል።
#ኢትዮጵያ #የውጭሀገራትጉዞ #ወጣቶች
@tikvahethiopia
" ' ወደ ውጪ እንልካችኋለን ' በሚል ምክንያት ' ተጭበርብረናል ፣ ተዘርፈናል ' እያሉ ቅሬታ የሚያቀርቡ ሰዎች ተበራክተዋል " - የአ/አ ፍትህ ቢሮ
አሁን አሁን በኢትዮጵያ በርካታ ሰዎች በተለይም ወጣቶች ወደ ውጭ ሀገራት የመሄድ ፍላጎታቸው እየተበራከተ መጥቷል።
እኚህ ወጣቶች ከሀገር ለመውጣት የተለያዩ ሙከራዎችንም ሲያደርጉ ይታያል።
የውጭ ጉዞ ለማድረግ ከሚሞክሩባቸው አንዱ መንገድ ደግሞ በደላሎች ፣ በጉዞ ወኪሎች እና በሌሎችም አማካኝነት ነው።
ወጣቶች በትምህርት ፣ በስራ እንዲሁም በጉብኝነት አማካኝነት ነው ከሀገር ለመውጣት የሚጥሩት።
የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ህይወት ለመቀየር ፣ አፍላ የሆነ የወጣትነት እድሜያቸው ሳያልፍ አንዳች ነገር አፍርተው ቤተሰብ መስርተው ጥሩ ኑሮ ለመኖር ፤ ከድህነት ለመላቀቅ ሲሉ በሚሞክሯቸው የውጭ ሀገር እድሎች ግን ምንም ርህራሄ በሌላቸው አጨበርባሪዎች ሲታለሉም ይታያል።
የወጣቶቹን ፍላጎት እያየ ገንዘባቸውን የሚበላቸው ፣ አውሮፓና አሜሪካ ብሎ ሌላ የወንጀልና ደህንነት የሌለው ቀጠና የሚልካቸው ደላላ፣ ወኪል እየበዛ መጥቷል።
በመዲናችን አዲስ አበባ ህገወጥ ስራን የሚሰሩ የጉዞ ወኪሎች መበራከት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፍትህ ቢሮ ለአሃዱ በሰጠው ቃል ፤ በየጊዜው የውጪ ሀገር የጉዞ ወኪልና አማካሪ ድርጅቶች እንዲሁም ደላሎች " ወደ ውጪ እንልካችኋለን " በሚል ምክንያት ' ተጭበርብረናል፣ ተዘርፈናል ' እያሉ ቅሬታ የሚያቀርቡ ሰዎች መበራከታቸውን አስታውቋል፡፡
እነዚህ ቅሬታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸው ተመላክቷል።
" እነዚህን ቅሬታዎች ተሰምተዉ ዝም የሚባልበት አግባብ የለም " ያለው ቢሮ በቀጥታ ለአዲስ አበባ እና ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በመላክ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየሰራሁ ነው ብሏል።
" በኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም ወደ አውሮፓ የሚሄዱ ሰዎች ፍላጎት መበራከቱን ተከትሎ፤ ዜጎች ከሕግ ውጪ በሚሰሩ ድርጅቶችና ደላሎች አማካኝነት ረብጣ ገንዘባቸውን መጭበርበራቸው እየተባባሰ ይገኛል " ነው ያለው።
በብዙዎች ጥቆማና ቅሬታ መሰረት፤ ከዚህ ቀደም ከ40 በላይ ሕገ-ወጥ ሥራን በመስራት የተሰማሩ የውጪ ሀገር የጉዞ ወኪሎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ቢሮው አመልክቷል።
ፍትህ ቢሮ ፤ " ህብረተሰቡ በተለያየ መንገድ ወደ ውጪ ለመውጣት ሲፈልግ፤ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሕጋዊ የሆኑ ወኪሎችን ለይቶ ስላሰራጨ፤ በተለያዩ ማህበራዊ ሚድያዎች ላይ ማግኘት ይችላል " ብሏል።
አልያም በአካል ቀርቦ መረጃ እንዲያገኝ ለአሃዱ በሰጠው ቃል አሳስቧል።
#ኢትዮጵያ #የውጭሀገራትጉዞ #ወጣቶች
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ንጉስማልት ምግብ ያለ ንጉስ በጭራሽ አይታሰብም! የንጉስ ጠርሙስን ያሽከርክሩ ከዛም ከደረስዎ ምግብ ጋር ንጉስን ይሞክሩት::
#nonalcoholic #ንጉስ #DesDesWithNegus #ደስደስበንጉስ #የጣዕምልኬት_የደስታስሜት
#nonalcoholic #ንጉስ #DesDesWithNegus #ደስደስበንጉስ #የጣዕምልኬት_የደስታስሜት
#ሴጅ_ማሰልጠኛ
በቅዳሜ ጠዋት የልጆች የኮምፒውተር ኮዲንግ እና ግራፊክ ዲዛይን ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።
👉ስልጠናው ዕድሜያቸው ከ 8-18 ዓመት ላሉ ልጆች የሚሰጥ
👉 ልጆች ፕሮጀክቶች እየሰሩ የሚሰለጥኑበት
👉ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://t.iss.one/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
በቅዳሜ ጠዋት የልጆች የኮምፒውተር ኮዲንግ እና ግራፊክ ዲዛይን ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።
👉ስልጠናው ዕድሜያቸው ከ 8-18 ዓመት ላሉ ልጆች የሚሰጥ
👉 ልጆች ፕሮጀክቶች እየሰሩ የሚሰለጥኑበት
👉ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://t.iss.one/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
#Bata
ፒላርሰ ትሬዲንግ ዓለም አቀፍ ብራንድ ከሆነው ' ባታ ጫማ ' ጋር ስምምነት በመፈረም ብቸኛ አከፋፋይ በመሆን ወደ ኢትዮጵያ ገቢያ በማሰገባት ለሺያጭ ለማቅረብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
እ.ኤ.አ በ1894 ዓ/ም የተመሰረተው ባታ ጫማ በ5 አህጉር ከ70 በላይ ሀገሮች ላይ 5300 የጫማ መደብሮች ያለው ሲሆን በ21 ሀገሮች ላይም የጫማ ማምረቻ አሉት።
በችርቻሮ መደብሮቹም ለድንበኞቹ በሁሉም የእድሜ ክልል ላሉ ወንድና ሴቶች እንዲሁም ህፃናት የተለያዪ አይነት የጫማ አማራጮች ያቀርባል።
ፒላርሰ ትሬዲንግ በአጭር ጊዜ እቅድ ምርቶችን በማስመጣት ለገበያ ለማቅረብ ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጿል።
በቀጣይ 5 አመታት ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ 100 ያህል የመሸጫ ሱቆችን የመክፈት እቅድ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሆነ አመልክቷል።
የመጀመሪያው ሱቅ ቦሌ ማተሚያ ፊት ለፊት የሺ ህንፃ ግራውንድ ላይ በቅርቡ ከፍቶ ስራውን እንደሚጀምር ገልጿል።
ተጨማሪ መረጃ ፥ በ +251 966 96 56 76 (ዳግማዊ መስፍን) / +251913 03 77 24 (ትህትና ፀጋዬ) ላይ ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
@tikvahethiopia
ፒላርሰ ትሬዲንግ ዓለም አቀፍ ብራንድ ከሆነው ' ባታ ጫማ ' ጋር ስምምነት በመፈረም ብቸኛ አከፋፋይ በመሆን ወደ ኢትዮጵያ ገቢያ በማሰገባት ለሺያጭ ለማቅረብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
እ.ኤ.አ በ1894 ዓ/ም የተመሰረተው ባታ ጫማ በ5 አህጉር ከ70 በላይ ሀገሮች ላይ 5300 የጫማ መደብሮች ያለው ሲሆን በ21 ሀገሮች ላይም የጫማ ማምረቻ አሉት።
በችርቻሮ መደብሮቹም ለድንበኞቹ በሁሉም የእድሜ ክልል ላሉ ወንድና ሴቶች እንዲሁም ህፃናት የተለያዪ አይነት የጫማ አማራጮች ያቀርባል።
ፒላርሰ ትሬዲንግ በአጭር ጊዜ እቅድ ምርቶችን በማስመጣት ለገበያ ለማቅረብ ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጿል።
በቀጣይ 5 አመታት ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ 100 ያህል የመሸጫ ሱቆችን የመክፈት እቅድ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሆነ አመልክቷል።
የመጀመሪያው ሱቅ ቦሌ ማተሚያ ፊት ለፊት የሺ ህንፃ ግራውንድ ላይ በቅርቡ ከፍቶ ስራውን እንደሚጀምር ገልጿል።
ተጨማሪ መረጃ ፥ በ +251 966 96 56 76 (ዳግማዊ መስፍን) / +251913 03 77 24 (ትህትና ፀጋዬ) ላይ ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update
“ የተደበደቡ ስድስት መምህራን ህክምና ተከልክለዋል። ከታሰሩት አንድም የተፈታ የለም ” - የዞኑ መምህራን ማኀበር
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን በሳርማሌ ወረዳ የሚገኙ ከ60 በላይ መምህራን ከደመወዛቸው ያለፈቃዳቸው የተቆረጠ ገንዘብ እንዲመለስላቸው በመጠየቃቸው መታሰራቸውን የዞኑ መምህራን ማኀበር ትላንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።
ዛሬ ደግሞ፣ መምህራኑ ከእስር እንዳልተፈቱ፣ እየታሰሩ በነበረበት ወቅት ድብደባ የተፈጸመባቸው መምህራን እንዳይታከሙ መከልከላቸውን ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
የማኀበሩ ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ጭበጮ ለበሰጡት ቃል፣ “ በሚያስሩበት ወቅት የተደበደቡ ስድስት መምህራን ህክምና ተከልክለዋል። ከታሰሩት ውስጥ አንድም የተፈታ የለም ” ብለዋል።
ተጎጂዎቹን እንዲያዩ የማኀበሩን ሰዎች ወደ እስራት ቦታው ልኮ እንደነበር የገለጹት አቶ ተስፋዬ፣ “ አሁን ባለው ሂደት ብዙዎቹ እንደተገጎዱ ናቸው። እንዲያውም የአንዱ በጆሮው ሁሉ መግል እየወጣ ነው ህክምና ተከልክለዋል ” ብለው፣ ለማሳከም ቢጠይቁም እንደከላከሏቸው ተናግረዋል።
መምህራኑ ከታሰሩ ስንት ቀናት አስቆጠሩ ? የተቆረጠባቸው ምን ያህል ገንዘብ ነው ? ለሚለው ቲክቫህ ጥያቄ የሰጡት ምላሽ ደግሞ፣ “ ረቡዕ ነው እስራቱ የተጀመረው ፤ ዛሬ አራተኛ ቀናቸው ነው። 25 በመቶ ነው የተቆረጠባቸው ” የሚል ነው።
የዞኑ ትምህርት መምሪያ፣ መምህራኑ ደመወዛቸው የተቆረጠው በፈቃዳቸው እንደሆነ፣ የታሰሩትም ገንዘብ እንዲመለስላቸው በመጠየቃቸው ሳይሆን፣ “ ድንጋይ ወርውረው ሌሎችን በመበጥበጣቸው ” መሆኑን ነው የገለጸው፣ እውነትም እንደዛ ነው የሆነው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን አሉ?
“ ይሄ ትልቅ ውሸት ነው። ቢነጋገሩ፣ ተስማምተው ቢሆን ኖሮ መምህራኑ ቅሬታ አያቀርቡም ነበር።
መምህራኑ ለትምህርት መምሪያው በፅሑፍ ያቀረቡት ‘አልተስማማንበትም፤ ባልተስማማንበት ጉዳይ የተቆረጠብን ገንዘብ ይመለስልን’ የሚል ነው።
‘ያልተስማማንበት ስለሆነ ገንዘቡ ይመለስ’ ብሎ እያንዳንዱ መምህር ትምህርት መምሪያውን ጠይቋል። መምሪያው ይሄን ሁሉ ክዶ ነው ለመሸፈን የሚሞክረው። ባወጣው መግለጫም እርምት ቢደረግ መልካም ነው።
ትምህርት መምሪያው መምህራኑ ‘ድንጋይ ወርውረዋል’ ማለቱ ውሸት ነው። አንድም የወረወረ የለም። አንድ መምህር ለስህተት ድንጋይ የሚባል ነገር አላነሳም። ይህን ወርዶ ማረጋገጥ ይቻላል ” ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር ፕሬዜዳንት አቶ አማኑኤል ጳውሎስ በበኩላቸው፣ “ ‘አንድ መፅሐፍ ለአንድ ተማሪ’ በሚል ነው መምህራኑን ሳያወያዩ ‘በዞን ደረጃ ተወስኗል’ በሚል ከደመወዛቸው እየቆረጡ ያሉት ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
“ ደመወዝ ያለስምምነት መቆረጥ እንደሌለበት አቅጣጫ ቢቀመጥም ይሄን የሚያደርጉ አካላት ምንም ሲያደርጉ አይታዩም ” ሲሉም ተችተዋል።
“ ከዚህ በፊት ሌላ ዞንና ወረዳ ላይ እንደዚህ አይነት ነገር ሲያደርጉ የነበሩ ሰዎች ተመልሰው የተሻለ ሹመት እንዲያገኙ ነው የሚደረገው እንጂ ‘ይሄን አጥፍተሃል’ ተብሎ የማጠየቅ አካል የለም ” ነው ያሉት።
ስለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ታምራት፣ ለጊዜው የማይመች ቦታ እንደሆኑ ገልጸው፣ ቀጠሮ ሰጥተው የነበረ ሲሆን፣ በቀጠሩት ሰዓት በተደጋጋሚ ቢደወልም ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
የዞኑ ትምህርት መምሪያ ትላንት በሰጠን ማብራሪያ፣ የመምህራኑ ደመወዝ የተቆረጠው በስምምነታቸው መሠረት እንደሆነ፣ የታሰሩትም፣ ድንጋይ ስለወረወሩ እንደሆነ፣ ቅሬታው እንዲፈታ እየሰራ ስለመሆኑ ገልጾ ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንድስትሪ አ.ማ. ለደንበኞቹ ካዘጋጃቸው ሽልማቶች ውስጥ ሁለተኛው ቮልስ ዋገንአይዲ4 (VW ID4) የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ፣ በመዲናችን አዲስ አበባ ለዕድለኛ ወጥቷል፡፡
ዕድለኛዋ አሸናፊ ወ/ሮ መቅደስ አስናቀ፣ ሽልማታቸውን ኅዳር 14 ቀን 2017ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ በተከናወነ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም ተረክበዋል፡፡
ከዚህ በፊት በሐዋሳ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ኤርሚያስ፣ የመጀመሪያውን ቮልስ ዋገን አይዲ4 (VWID4) የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡
አሁንም በርካታ ሽልማቶች ተረኛ ዕድለኛቸውን እየጠበቁ ነው፡፡ የፔፕሲን ምርቶች እያጣጣምን ዕድላችን እንሞክር - እናሸንፍ! ፔፕሲ፣ ሚሪንዳ እና ሰቨን አፕ ይጥማሉ - ያስሸልማሉ!
ሞሐ !
ዕድለኛዋ አሸናፊ ወ/ሮ መቅደስ አስናቀ፣ ሽልማታቸውን ኅዳር 14 ቀን 2017ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ በተከናወነ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም ተረክበዋል፡፡
ከዚህ በፊት በሐዋሳ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ኤርሚያስ፣ የመጀመሪያውን ቮልስ ዋገን አይዲ4 (VWID4) የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡
አሁንም በርካታ ሽልማቶች ተረኛ ዕድለኛቸውን እየጠበቁ ነው፡፡ የፔፕሲን ምርቶች እያጣጣምን ዕድላችን እንሞክር - እናሸንፍ! ፔፕሲ፣ ሚሪንዳ እና ሰቨን አፕ ይጥማሉ - ያስሸልማሉ!
ሞሐ !
#SafaricomEthiopia
በነፋሻማ ተፈጥሮ ተከባችሁ ፊልም ለመኮምኮም ዝግጁ ናችሁ? ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የAddis Open Air Cinemaን ስፖንሰር አድርጎ ይዞላችሁ መጥቷል! እንደ ባንድ ሙዚቃ እና ካሪኦኬ ያሉ ሌሎች መዝናኛዎችም በሽ ናቸው! ህዳር 15 በጊዮን ግሮቭ ጋርደን ዎክ አይቀርም!
ቲኬቱን በM-PESA Safaricom app ላይ ያገኙታል
#MPESASafaricom #1Wedefit #Furtheraheadtogether
በነፋሻማ ተፈጥሮ ተከባችሁ ፊልም ለመኮምኮም ዝግጁ ናችሁ? ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የAddis Open Air Cinemaን ስፖንሰር አድርጎ ይዞላችሁ መጥቷል! እንደ ባንድ ሙዚቃ እና ካሪኦኬ ያሉ ሌሎች መዝናኛዎችም በሽ ናቸው! ህዳር 15 በጊዮን ግሮቭ ጋርደን ዎክ አይቀርም!
ቲኬቱን በM-PESA Safaricom app ላይ ያገኙታል
#MPESASafaricom #1Wedefit #Furtheraheadtogether
🔴 " ደመወዛችን ተቆርጦ 15 ,000 ብር የሚከፈላቸው 5 ,000 ብር ነው የገባላቸው፡፡ ለ6 ወራት ደመወዛችን በስርዓት እየተከፈለን አይደለም " - ሠራተኞች
🔵 " ጥሩ ቅሬታ ነው። ድርጅቱ ደመወዝ የሚከፍለው ብር ሲኖር ነው " - የናሁ ቴሌቪዥን አስተዳደር
የናሁ ቴሌቪዥን ሠራተኞች የወር መወዛቸው በወቅቱ እንደማይፈጸም፣ ጊዜው ካፈ በኋላ ራሱ ከደመወዛቸው ከግማሽ በላይ ተቆርጦ እንደሚደርሳቸው፣ ደመወዛቸው ባለመከፈሉ ብድር ጭምር እንደገቡ፣ ድርጅቱ አጥጋቢ ምላሽ በመስጠት ፋንታ እያንጓጠጣቸው መሆኑን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ስሞታ አሰምተዋል፡፡
ሠራተኞቹ ያቀረቡት ዝርዝር እሮሮ ምንድን ነው?
" ደመወዛችን ተቆርጦ 15 ሺሕ ብር የሚከፈላቸው 5 ሺሕ ብር ነው የገባላቸው። ላለፉት ስድስት ወራት የሰራንበት ደመወዝ በትክክል እየተከፈለን አይደለም፡፡ አሁን ለምሳሌ የጥቅምት ወር ደመወዝ ዛሬ ነው የገባልን።
ወቅቱን ተላልፎ እንኳ 13 ሺሕ ብር የሚከፈለን ሰዎች ተቆርጦ 6,500 ብር ነው የገባልን፡፡ ወሩን ሥራ ገብተናል፡፡ ግን ‘ፊርማ አልፈረማችሁም’ ተብሎ ነው የተቆረጠው፡፡ ለዜናም፣ ለጥቆማም ልናናግር ወጥተን ያረፈድነው ሰዓት አይቆጠርልንም፡፡
የሐምሌን ደመወዝ ራሱ ‘ከባንክ ተበደሩና ውሰዱ እኛ እንከፍላን’ ነበር ያሉን፡፡ የሐምሌ ደመወዛችን ባለመፈጸሙ አቢሲኒያ ብድር ገብተናል፡ ግን እስካሁን እለተከፈለንም፡፡
የነሐሴ ወር ደመወዝ ደግሞ 20 ፐርሰንት ተቀንሶ ነው የገባው፡፡ ቀሪውን ራሱ እስካሁን አልሰጡንም፡፡ የመስከረም ደግሞ ጥቅምት 20 ነው የተከፈለን፡፡ ይህ ባለበት ሁኔታ አሁን ደግሞ ደመወዛችን ከግማሽ በታች ተቆርጦ ነው የገባው፡፡
ከ10 ሺሕ ብር እስከ 3,000 ብር ነው የተቆረጠብን፡፡ ይህ ሲደረግ ምንም አይነት ማስጠንቀቂያ አናውቅም፡፡ ብቻ ደመወዛችን ሲገባ ግን ተቆርጧል፡፡ ስንናገርም ‘ከፈለጋችሁ ውጡ ከፈለጋችሁ ተቀመጡ’ ነው የምንባለው።
ድርጊቱ ከአቅማችን በላይ ሆኗል። እስከ ሰባት ዓመት የሰሩ ጓደኞቻችንን ‘እንዳትመጡ’ ብለዋቸዋል። አንዷ ወር ሙሉ የሠራችበት ተቆርጦ 1,000 ሺሕ ብር ነው የገባላት ከ10 ሺሕ ብር ደመወዟ። ‘ምን ታመጣላችሁ ብትፈልጉ ውጡ’ ነው የሚሉት።
ሰው ለመቀነስ ፈልገው ከሆነ እንኳ በአግባቡ ምክንያቱ ተጠቅሶ፣ ደብዳቤ ተፅፎ፣ ለሠራተኛው የሚገባው ሁሉ ተሰጥቶ ነው የሚሆነው። ከዚህ ግን ማናጀሩ ‘ኑ’ ብሎ ‘ካሁን ወዲያ እንዳትመጡ’ ነው የሚለው " ብለዋል።
የሌሎች ደመወዝ በትክክል እየተፈጸመ ከሆነ የእናንተ ለብቻው ለምን በወቅቱና ሳይቆረጥ አልተፈጸመም? ምን የተለዬ ምክንያት ኖሮ ነው የእናንተ ብቻ እንዲህ የተደረገው? በሚል ላቀረብነው ጥያቄ ምላሻቸው፣ " እነርሱ የሚሉት ‘አቴንዳንስ በትክክል አልፈረማችሁም’ ነው፡፡ ግን ሰዓት አልፎም ቢሆን ፈርመናል " የሚል ነው።
“ ደመወዝ ሊቆረጥ የሚችለው በተሸረረፈው ሰዓት ነው፡፡ ሦስት ቀን ያልፈረመ የአንድ ቀን ይቆረጣል ነው የሚለው ሕጉ” ሲሉ አክለው፣ " እኛ ግን ለምሳሌ 4 ሰዓት ገብተን ቢሮ ውለን የሙሉ ቀን ደመዝ ነው የሚቆረጥብን " ብለዋል።
ቅሬታው ያላቸው 14 ሰዎች እንደሆኑ፣ ከድርጅቱ ደመወዝ ያልተቆረጠባቸው አራት ወይም አምስት ሰዎች እንደሆኑ አስረድተው፣ ድርጅቱ በአግባቡ እንዲያስተዳድራቸው ጠይቀዋል።
ሠራተኞቹ ያቀረቡትን ቅሬታ በመንገር እውነት ነው ? ከሆነ ለምን እንደህ ተደረገ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው የናሁ ቴሌቪዥን አስተዳደር አቶ ኢዶሳ ቀጀላ፣ " ጥሩ ቅሬታ ነው። ድርጅቱ ደመወዝ የሚከፍለው ብር ሲኖር ነው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የድርጅቱ አስተዳደር አክለው ምን አሉ ?
" ብዙ ነገሮች ኪሳራ ላይ ስለጣሉን ብዙ ክፍያ ውጪ ላይ ስለሚያዝብንና ከከስተመሮቻችን ጋር ያሉትን ሴልሶች ቶሎ ኮሌክት ለማድረግ ስለማንችል/ ስለምንቸገር ደመወዝ ቆይተን ልንከፍል እንችላለን።
አንደኛ ደመወዝ ይቆያል። ሁለተኛ ደግሞ በአግባቡ ሥራ ያልገቡ ሰዎችን አቴንዳንሳቸው ኮሌክት ተደርጎ ይገባና ስንት ቀን ሥራ ገብተዋል? ተብሎ ነው ደመወዝ የሚከፈለው።
አሁን ‘ደመወዝ በአግባቡ አልተከፈለንም፣ ተቆረጠ’ የሚሉ ሠራተኞች በወር ውስጥ ስንት ቀን ገብተው እንደፈረሙ አቴንዳንሳቸው ታይቶ ነው ደመወዝ የተከፈላቸው እንጂ ሠራተኞች ስለሆኑ ብቻ 30 ቀናት ታስቦ አይሰጥም።
ስለዚህ የተቆረጠባቸው ሰዎች አሉ። እነርሱም በአግባቡ ያልገቡና አቴንዳንስ ያልፈረሙ ለድርጅቱ ሥራ ያልሰሩ ሰዎች ናቸው " ሲሉ ተናግረዋል።
ደመወዝ ሊቆረጥባቸው የሚገባው በሸራረፉት ሰዓት ሆኖ እያለ ሰዓት አሳልፈው ቢሮ ቢገቡም የሙሉ ቀን መቆረጡ ቅር እንዳሰኛቸው ሠራተኞቹ ገልጸዋል፤ ይህን ማድረጉ አግባብ ነው? ስንል ላቀረበው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን አሉ ?
"አንድ ሠራተኛ ድርጅቱ በሚያውቀው መልክ ነው ገብቶ የሚወጣው እንጂ ሥራ ስለሌለ 4 ሰዓት መግባት የለም።
የቢሮ መግቢያ ሰዓት ከ2፡30 ይጀምራል። እስከ 3፡30 እኛ እዚያ እንቆያለን አቴንዳንስ ከዚያ በኋላ ይነሳል” ያሉት የድርጅቱ አሰሰተዳዳሪ፣ “እስከ 4 ሰዓት ያልገባ ሠራተኛ ገብቶ እንዲሰራ አንፈልግም፤ አንፈቅድም።
አጋጣሚ ሆኖ ችግር ካጋጠመ ደውሎ ማሳወቅ፣ ማስፈቀድ ይኖርበታል። እንደዚህ የሚያደርጉ ሠራተኞች በጥሩ ትራት ይደረጋሉ።
እንደፈለጉ ለሚገቡና ለሚወጡ ሠራተኞች ደመወዛቸውንም አንከፍልም፤ እሱም ብቻ ሳይሆን አስተዳደራዊ እርምጃም እንወስድባቸዋለን። ይህን ሕጉም ስርዓቱም ይፈቅዳል” በማለት ነው የመለሱት።
ድርጅቱ ሠራተኛ ለመቀነስ ፈልጎም ከሆነ በደብዳቤ እንጅ ‘ውጡ’ ተብሎ “ተጥላልተን” መሆን የለበትም የሚል ቅሬታ ሠራተኞቹ አላቸው፤ ይህን ማድረግስ ለምን አስፈለገ? በሚል ቲክቫህ ላቀረበው ጥየያቄ፣ “ይህን አላደረግነውም” የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የተሰጠ ውክልና የለም " - ሚኒስቴሩ
" ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፡፡ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል " በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች እየተላለፉ እንደሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አሳውቋል።
እየተለለፉ ባሉት ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች ህብረተሰቡ ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየተዳረገ መሆኑን አመልክቷል።
በመሆኑ " መሰል የማጭበርበር ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ እየሰራሁ ነው " ብሏል።
በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና የሌለ መሆኑን አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ፥ " ዜጎች በስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ካላስፈላጊ ወጪ፣ እንግልትና ሌሎች አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ በጥብቅ እናሳስባለን " ብሏል።
የሁለትየሽ ስምምነት የተፈረመባቸው መዳረሻ ሀገራት በ lmis.gov.et ላይ መመልከት እንደሚቻል ገልጿል።
@tikvahethiopia
" ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፡፡ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል " በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች እየተላለፉ እንደሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አሳውቋል።
እየተለለፉ ባሉት ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች ህብረተሰቡ ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየተዳረገ መሆኑን አመልክቷል።
በመሆኑ " መሰል የማጭበርበር ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ እየሰራሁ ነው " ብሏል።
በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና የሌለ መሆኑን አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ፥ " ዜጎች በስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ካላስፈላጊ ወጪ፣ እንግልትና ሌሎች አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ በጥብቅ እናሳስባለን " ብሏል።
የሁለትየሽ ስምምነት የተፈረመባቸው መዳረሻ ሀገራት በ lmis.gov.et ላይ መመልከት እንደሚቻል ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DDR " ትጥቅ መፍታት መሸነፍ ፣ መዋረድ ወይም ራስን ዝቅ ማድረግ ማለት አይደለም። ትጥቅ መፍታት ማለት የሀገር አንድነትና ሰላም በፅኑ መሰረት ላይ ከማቆም አንፃር መታየት አለበት " - የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር የመጀመሪያ ዙር የትግራይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞቢላይዝድ በማድረግ ወደ ተሃድሶ ስልጠና ማዕከላት የማስገባት ስራ በይፋዊ ስነስርዓት ተጀምሯል። ዛሬ…
#Update
" ተገደን እንጂ ወደን የገባነው ጦርነት የለም ፤ በDDR አሰራር ወደ ህዝባችን ለመቀላቀል ፍቃደኞች ነን ሁሌም ምርጫችን ሰላም ነው " - ተመላሽ ታጣቂዎች
የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የዲሞብላይዜሽን እና መልሶ ማቋቋምያ ስነ-ሰርዓት በትግራይ መቐለ በይፋ ተጀምሯል።
ቅዳሜ ህዳር 14/2017 ዓ.ም በይፋ በተከናወነው የዲሞብላይዜሽን እና መልሶ ማቋቋምያ የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓተ የክልሉ እና የፌደራል ከፍተኛ የስራ ኋላፊዎች ተገኝተው ነበር።
የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን በDDR የሚታቀፉ የትግራይን ጨምሮ በስድስት የሀገሪቱ ክልሎች የሚገኙ ከ600 ሺህ በላይ ታጣቂዎች በሁለት ዓመት ውስጥ ዴሞብላይዝ በማድረግ ወደ ህዝቡ እንዲቀላቀሉ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ተገልጿል።
የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን ምን አሉ ?
ትጥቅ መፍታትና ዴሞብላይዜሽን (DDR) ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነቶች ዋነኛ እና ጎልቶ የሚጠቀስ ነጥብ ቢሆንም በሃብት እጦት ምክንያት መዘግየቱ ተናግረዋል።
በትግራይ ጦርነት የተሳተፉ 274,800 ታጣቂዎች በDDR ዴሞብላይዝ ሆነው በሁለት ዓመት ውስጥ ወደ ህዝብ ይቀላቀላሉ ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፦
👉 በአንድኛ ዙር 75 ሺህ
👉 በሁለተኛ 100 ሺህ
👉 በሦስታና ዙር 53 ሺህ 800
👉 በአራተኛ ዙር 46 ሺህ እንደሆነ አብራርተዋል።
በተካሄደው እጅግ አሰቃቂ ደም አፋሳሽ ጦርነት " በርካታ ህይወት ተቀጥፈዋል ፣ አካል ጎድሏል የሀገር እና የህዝብ ሃብት ወድመዋል " ያሉት አቶ ተመስገን ይህ እንዳይደገም እንደ ሀገር እና ህዝብ በቁርጠኝነት መስራት አለብን ሲሉ በአፅንኦት ተናግረዋል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳን ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?
DDR ቀድሞ መደረግ የነበረበት ቢሆንም፤ ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚሆን ሃብት ለማሰባሰብ ነው የዘገየው ፤ የዘገየም ቢሆን ዛሬ መጀመሩ ለሰላም ያለው ትርጉም ትልቅ ነው ብለዋል።
ተፈናቃዮች ባልተለመለሱበት፣ የትግራይ ሉኣላዊ ግዛቶች ከፌደራል የሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ ባሉ የሀገር ውስጥና የውጭ ታጣቂዎች ተይዞ ባለበት ወቅት DDR መጀመሩ ከስጋት ወጪ ሆኖ እየተፈፀመ ባይሆንም ሁኔታዎች እየተስተካከሉ ይሄዳሉ ከሚል ተስፋ ድጋፋችን መስጠት እንቀጥላለን ሲሉ ገልጸዋል።
የDDR መተግበር የትግራይ ሰላም መቀጠል ከሀገር ሰላም መፅናት ተያይዞ መታየትና መፈፀም እንዳለበት የፌደራል መንግስት እና ለጋሾች ትኩረት አደርገው ደጋፋቸው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅብረዋል።
የተሰናባች ታጣቂዎች ተወካይ ነጋሽ ገ/ዮሃንሰ ምን አሉ ?
" ተገደን እንጂ ወደን የገባነው ጦርነት የለም ፤ ስለሆነም የነበረው ችግር በጠረጴዛ ውይይት መፍታት ከተቻለ ትጥቅ አንግበን የምንኖርበት ፍላጎት ስለሌለን በDDR አሰራር ወደ ህዝባችን ለመቀላቀል ፍቃደኞች ነን " ብለዋል።
ታጣቂዎች " የመጀመሪያ እና የመጨረሻ ምርጫችን ሰላም ነው የተሟላ ሰላም እንዲሰፍን አሁንም ከፌደራል የሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጪ በትግራይ መሬት ያሉ ታጣቂዎች ለቀው እንዲወጡ ለፌደራል መንግስት እና ለአደራዳሪዎች እንጠይቃለን " ሲሉ ተናግረዋል።
" ለቀድሞ ታጣቂዎች ለማቋቋምያ የተመደበው በቂ ስላልሆነ ቀጣይ የሆነ ድጋፍ እንሻለን " በማለትም ተናግረዋል።
በመርሃ ግብሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች ተገኝተው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
Photo Credit - DW
@tikvahethiopia
" ተገደን እንጂ ወደን የገባነው ጦርነት የለም ፤ በDDR አሰራር ወደ ህዝባችን ለመቀላቀል ፍቃደኞች ነን ሁሌም ምርጫችን ሰላም ነው " - ተመላሽ ታጣቂዎች
የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የዲሞብላይዜሽን እና መልሶ ማቋቋምያ ስነ-ሰርዓት በትግራይ መቐለ በይፋ ተጀምሯል።
ቅዳሜ ህዳር 14/2017 ዓ.ም በይፋ በተከናወነው የዲሞብላይዜሽን እና መልሶ ማቋቋምያ የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓተ የክልሉ እና የፌደራል ከፍተኛ የስራ ኋላፊዎች ተገኝተው ነበር።
የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን በDDR የሚታቀፉ የትግራይን ጨምሮ በስድስት የሀገሪቱ ክልሎች የሚገኙ ከ600 ሺህ በላይ ታጣቂዎች በሁለት ዓመት ውስጥ ዴሞብላይዝ በማድረግ ወደ ህዝቡ እንዲቀላቀሉ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ተገልጿል።
የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን ምን አሉ ?
ትጥቅ መፍታትና ዴሞብላይዜሽን (DDR) ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነቶች ዋነኛ እና ጎልቶ የሚጠቀስ ነጥብ ቢሆንም በሃብት እጦት ምክንያት መዘግየቱ ተናግረዋል።
በትግራይ ጦርነት የተሳተፉ 274,800 ታጣቂዎች በDDR ዴሞብላይዝ ሆነው በሁለት ዓመት ውስጥ ወደ ህዝብ ይቀላቀላሉ ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፦
👉 በአንድኛ ዙር 75 ሺህ
👉 በሁለተኛ 100 ሺህ
👉 በሦስታና ዙር 53 ሺህ 800
👉 በአራተኛ ዙር 46 ሺህ እንደሆነ አብራርተዋል።
በተካሄደው እጅግ አሰቃቂ ደም አፋሳሽ ጦርነት " በርካታ ህይወት ተቀጥፈዋል ፣ አካል ጎድሏል የሀገር እና የህዝብ ሃብት ወድመዋል " ያሉት አቶ ተመስገን ይህ እንዳይደገም እንደ ሀገር እና ህዝብ በቁርጠኝነት መስራት አለብን ሲሉ በአፅንኦት ተናግረዋል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳን ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?
DDR ቀድሞ መደረግ የነበረበት ቢሆንም፤ ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚሆን ሃብት ለማሰባሰብ ነው የዘገየው ፤ የዘገየም ቢሆን ዛሬ መጀመሩ ለሰላም ያለው ትርጉም ትልቅ ነው ብለዋል።
ተፈናቃዮች ባልተለመለሱበት፣ የትግራይ ሉኣላዊ ግዛቶች ከፌደራል የሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ ባሉ የሀገር ውስጥና የውጭ ታጣቂዎች ተይዞ ባለበት ወቅት DDR መጀመሩ ከስጋት ወጪ ሆኖ እየተፈፀመ ባይሆንም ሁኔታዎች እየተስተካከሉ ይሄዳሉ ከሚል ተስፋ ድጋፋችን መስጠት እንቀጥላለን ሲሉ ገልጸዋል።
የDDR መተግበር የትግራይ ሰላም መቀጠል ከሀገር ሰላም መፅናት ተያይዞ መታየትና መፈፀም እንዳለበት የፌደራል መንግስት እና ለጋሾች ትኩረት አደርገው ደጋፋቸው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅብረዋል።
የተሰናባች ታጣቂዎች ተወካይ ነጋሽ ገ/ዮሃንሰ ምን አሉ ?
" ተገደን እንጂ ወደን የገባነው ጦርነት የለም ፤ ስለሆነም የነበረው ችግር በጠረጴዛ ውይይት መፍታት ከተቻለ ትጥቅ አንግበን የምንኖርበት ፍላጎት ስለሌለን በDDR አሰራር ወደ ህዝባችን ለመቀላቀል ፍቃደኞች ነን " ብለዋል።
ታጣቂዎች " የመጀመሪያ እና የመጨረሻ ምርጫችን ሰላም ነው የተሟላ ሰላም እንዲሰፍን አሁንም ከፌደራል የሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጪ በትግራይ መሬት ያሉ ታጣቂዎች ለቀው እንዲወጡ ለፌደራል መንግስት እና ለአደራዳሪዎች እንጠይቃለን " ሲሉ ተናግረዋል።
" ለቀድሞ ታጣቂዎች ለማቋቋምያ የተመደበው በቂ ስላልሆነ ቀጣይ የሆነ ድጋፍ እንሻለን " በማለትም ተናግረዋል።
በመርሃ ግብሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች ተገኝተው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
Photo Credit - DW
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
ለማይቋረጥ የኢንተርኔት ጌም ወሳኙ የማይቋረጥ ኢንተርኔት ነው ፤ አሁኑኑ የሳፋሪኮምን የ4G ዋይ ፋይ ጥቅል ከM-PESA ሳፋሪኮም mini app በመግዛት በጌማችን እንፍታታ!
#MPESASafaricom #FurtherAheadTogether
ለማይቋረጥ የኢንተርኔት ጌም ወሳኙ የማይቋረጥ ኢንተርኔት ነው ፤ አሁኑኑ የሳፋሪኮምን የ4G ዋይ ፋይ ጥቅል ከM-PESA ሳፋሪኮም mini app በመግዛት በጌማችን እንፍታታ!
#MPESASafaricom #FurtherAheadTogether
#DStvEthiopia
⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን...
👉ከሕዳር 16 ጀምሮ ፈጥነው ወደ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ ከፍ ይበሉ! ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ129 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/48oVhj8
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #MedaSport
⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን...
👉ከሕዳር 16 ጀምሮ ፈጥነው ወደ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ ከፍ ይበሉ! ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ129 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/48oVhj8
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #MedaSport