TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#InfinixEthiopia

የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን የኢንፊኒክስ ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 ሞባይል ስልኮችን እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ሲገበያዩ ኩፖን በመውሰድ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም እና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በመለጠፍ ብቻ ከላይ በተጠቀሱት ሽልማቶች ይንበሽበሹ፡፡

መመሪያ

1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡

Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
#AddisAbaba

የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አፈጸሚ አቶ ሰዒድ አሊ ያለመከሰስ መብት ተነሳ።

የአዲስ አበባ ምክር ቤት ዛሬ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤ እያካሄደ ነው።

በዚህም ጉባኤ የምክር ቤቱ አባል የሆኑትን የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰዒድ ዓሊን ያለመከሰስ መብትን ተነስቷል።

በፍትሕ ሚኒስቴር በቀረበ ጥያቄ መሠረት ነው ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው።

ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ የተደረገው ከሙስና ጋር በተያያዘ ነው።

ምክር ቤቱ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በሕግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ በሙሉ ድምፅ መወሰኑ ተሰምቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ በራስ ገዟ ሶማሌላድ ዛሬ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እየተካሄደ ነው። ህዝቡ ከጥዋት አንስቶ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመሄድ ድምጹን እየሰጠ ይገኛል። በምርጫው የአሁን ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ከአብዲራህማን ኢሮ እንዲሁም ከፋይሰል አሊ ዋርቤ ጋር ይፎካከራሉ። ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ተገንጥላ እራሷን እንደ ነጻ ሀገር የምትቆጥር ናት። ላለፉት በርካታ አመታት ከሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ጋር ምንም ግንኙነት…
#UPDATE

አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ " ኢሮ " የሶማሌላድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫን አሸነፉ።

የዋደኒ ፓርቲ እጩ ሆነው የቀረቡት አብዲራህማን ኢሮ ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እንዳሸነፉ የምርጫ ኮሚሽኑ ዛሬ አሳውቋል።

በምርጫው ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ እንዲሁም ፋይሰል አሊ ዋርቤ ተሳታፊ የነበሩ ቢሆንም ድል ሳይቀናቸው ቀርቷል።

የኢሮ ፓርቲ ምርጫውን 63.92 በመቶ ድምፅ በማግኘት ነው ያሸነፈው። የተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ ፤ ኩልሚዬ ፓርቲ 34.81% ነው ያገኘው።

ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ተገንጥላ እራሷን እንደ ነጻ ሀገር የምትቆጥር ናት። ላለፉት በርካታ አመታት ከሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ጋር ምንም ግንኙነት የላትም።

የራሷን መሪ / ፕሬዜዳንቶችን በምርጫ ስትመርጥ ኖራለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ " ህጋዊ ያልሆነ ጉባኤ ያካሄደው ህጋዊ ያልሆነው ቡድን የሚመድባቸው አስተዳዳሪዎች እና የስራ ሃላፊዎች የሚያስተዳድሩት ሃብት የለም " ሲል የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ። ጊዚያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው በፕሬዜዳንት ፅ/ቤት በኩል ባወጣው መግለጫ ነው። " ህጋዊ ያልሆነው ቡድን "  ሲል የገለፀው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ግልፅ የመንግስት ግልበጣ አካሂደዋል…
#Tigray

🔴 " ተኩስ ተከፍቶብኝ መኪናዬ ላይ ጉዳት ደርሷል " - አቶ ሰለሙን መዓሾ

🟠 " መረጃው ከእውነት የራቀ ነው። የተኮሰበት ሰው የለም " - አቶ ገብረ ተክለሃይማኖት

🔵 " ፓለቲከኞች የልዩነታችሁ ጣጣችሁን እዛው ጨርሱት ወደ ሰራዊቱ አታጋቡት " - ጀነራል ህንፃ ወ/ጊዮርጊስ

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራር ከተቃጣባቸው የግድያ ሙከራ ማምለጣቸውን ተሰምቷል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ የማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሰለሙን መዓሾ ባለፈው እሁድ ህዳር 8/2017 ዓ.ም ከስራ ባለደርቦቻቸው ጋር ከአክሱም ወደ መቐለ ሰጓዙ የግድያ ሙከራ እንደ ተቃጣባቸውና ከግድያ ሙከራው እንደተረፉ ተናግረዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ከአክሱም ወደ መቐለ ሲመለሱ ማይቅነጣል ፈላፍል በተባለ ቦታ ሲደርሱ መኪናቸው ላይ ተኩስ እንደተከፍተባቸው ገልጸዋል።

ለጊዜው እነማን እንደተኮሱባቸው ማንነታቸውን / የታጣቂዎችን ማንነት ማወቅ እንዳልቻሉ ገልጸው በተተኮሰባቸው ጥይቶች መኪናቸው ላይ ጉዳት መድረሱን አስረድተዋል።

በጥይት የተመታው መኪናቸውን የሚያሳይ ፎቶም ይፋ አድርገዋል።

በመኪናው ውስጥ ከእሳቸው በተጨማሪ ጥበቃቸው እና የመኪናው ሹፌር ነበሩ።

ዋና አስተዳዳሪው የደረሰባቸው አካላዊ ጉዳት እንደሌለ አረጋግጠዋል።

እሁድ ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም በዋና አስተዳዳሪ ሰለሙን መዓሾ የመግደል ሙከራ መደረጉ በማህበራዊ የትስስር ገፆች ላይ በስፋት ከተሰራጨ በኃላ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ወደ ማይቅነጣል ወረዳ ስልክ ቢደውልም ጉዳዩ የሚያረጋግጥ አካል አልተገኘም ነበር።

የዞኑ መቀመጫ ወደሆነችው አክሱም የሚገኝ ፓሊስ ማዘዣ ስልክ ቢደወልም የተጣራ መረጃ ማግኘት አልተቻለም።

ይህ በእንዲህ እያለ የመግደል መከራ ተቃጥቶበታል የተባለው ቦታ የሚያስተዳድረው የማይ ቅነጣል ወረዳ " ጉዳዩ አልተፈፀመም " የሚል መግለጫ አውጥቷል።

የማይቅነጣል ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ገብረ ተክለሃይማኖት ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ደግሞ ፣ ጉዳዩን ከወረዳው የጸጥታና ፖሊስ አባላት ማጣራታቸውን ገልፀው፣ " መረጃው ከእውነት የራቀ ነው። የተኮሰበት ሰው የለም " ብለዋል።

ከዚህ ባለፈ " በአከባቢው አለ ጉዳዩ ፈፅሞታል " ተብሎ በማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች ተደጋግሞ የተጠቀሰው የትግራይ ሰራዊት አርሚ 60 አዛዥ ጀነራል ህንፃ ወ/ጊዮርጊስ እሳቸው የሚያዙት በፀሃፊዎቹ የተገለፀው ሰራዊት በአከባቢው እንደሌለ በመግለፅ " ፓለቲከኞች የልዩነታችሁ ጣጣችሁን እዛው ጨርሱት ወደ ሰራዊቱ አታጋቡት " ሲሉ ተጠምደዋል።

ከአሁን በፊት በተለያዩ ጊዚያት መሰል የግደያ ሙከራዎች በጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ ሹማመንት በየነ መኩሩ ፣ ነጋ ኣሰፋ ፣ ሰሎሙን ትኩእ እንዲሁም በአክሱም ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራር መደረጋቸው የተነገረ ቢሆንም እስካሁን የድርጊቱ ፈፃሚዎች ተጣርተው የተወሰደ እርምጃ የለም።

#VOATigrigna #TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
ዶዳይ ማኑፋክቸሪንግ
ታላቅ ቅናሽ እስከ ህዳር 22 ብቻ የሚቆይ

በአንድ ጊዜ ቻርጅ እስከ 150ኪሜ መጓዝ የሚችሉ
•⁠ ⁠ለሙሉ ቻርጅ 10ብር ብቻ ሚጠይቁ
•⁠ ⁠⁠150ኪሎ ተሸክመው በሰአት እስከ 60ኪሜ የሚሄዱ
•⁠ ⁠ለእለት ተለት ጉዞ ቢሉ ፣ አልያም ለዲሊቨሪ ስራ የሚሆኑ

ይፍጠኑ
ይሂዱ > ይጎብኙ > ይግዙ!

ለበለጠ መረጃ
📍ሾው ሩም: ጎፋ ገብርኤል
📲 ስልክ: 0938022222
🌐 ethiopia.dodai.co

•⁠ ⁠TikTok Page: https://www.tiktok.com/@dodai_et?is_from_webapp=1&sender_device=pc
•⁠ ⁠Telegram Page: https://t.iss.one/+z09SxQgb6vsyNzU8
በተጨማሪ ስጦታዎች የታጀበውን ቴሌብር ሱፐርአፕ ይጠቀሙ!!

ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ሲጭኑ በ100ሜ.ባ የእንኳን ደኅና መጡ ስጦታ እንቀበልዎታለን!

🎁 የመጀመሪያውን ግብይት ሲፈጽሙ ደግሞ የ15 ብር ስጦታ ይበረከትልዎታል!

በተጨማሪም በቴሌብር 100 ብር እና ከዚያ በላይ የሞባይል አየር ሰዓት ሲሞሉ 25%፣ ከ100 ብር በታች ሲሞሉ 15% እንዲሁም ጥቅል ሲገዙ 10% ተጨማሪ ስጦታ ያገኛሉ፡፡

▶️ ለተጨማሪ፡ https://youtu.be/l7sSDPhPig4 ይመልከቱ!

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትኩረት🚨 " የጤና ተቋሙ ሳይፈርስ ከላይ ያሉ አካላት አስቸኳይ ድጋፍ ቢያደርጉ መልካም ነው "  - ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ስር የሚገኘው የዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል በክልሉ ተፈጥሮ ከነበረው ጦርነት በፊት ለመድሃኒትና ለላብራቶሪ ግብዓቶች ይመደብለት የነበረው በጀት ከ60 ሚሊየን ብር በላይ ነበር። በሆስፒታሉ የመድኃኒት እና የላብራቶሪ መመርመሪያ ግብዓቶች እጥረት ስለማጋጠሙ…
#Update

" መስሪያ ቤቱ መድኃኒት ለመግዛት ገንዘብ እያጠረው ነው " -የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት

የዓይደር ኮምፕረንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ካጋጠመው የመድኃኒትና የህክምና ግብዓቶች እጥረት ጋር በተያያዘ በሆስፒታሉ እና በታካሚዎች ዘንድ በርካታ ችግሮችን እያስከተለ የሚገኝ ሲሆን ተቋሙ ባሉበት ተደራራቢ እዳዎች ምክንያት ችግሩን መቅረፍ ተስኖታል።

ሆስፒታሉ ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጋር ባለበት ከፍተኛ ያልተከፈለ እዳ ምክንያት ውዝግብ ውስጥ ገብቷል።

በተቋሙ አጋጥሟል ለተባለ የመድኃኒቶች እጥረት ምክንያትም ያለው ውስን በጀት እና ያለበት ውዝፍ ተጠቃሽ ናቸው።

ካሉበት ችግሮች በተጨማሪ አንዳንድ መድኃኒቶች በመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በኩልም እያጡ መሆኑን ሆስፒታሉ ለቲክቫህ አሳውቋል። 

ሆስፒታሉ ላቀረበው ቅሬታ እና ስላልተከፈለው ከፍተኛ እዳ የአገልግሎቱን የመቀሌ ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ አለማየሁ ገብረማርያምን አነጋግረናል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/TikvahEthiopia-11-19

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ዛሬ ያለመከከስ መብታቸው የተነሳው የልደታ ክ/ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት የአ/አ ም/ቤት አባል ሰዒድ አሊ በምንድነው የተጠረጠሩት ?

ዛሬ የአዲስ አበባ ም/ቤት የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ሰዒድ አሊን ያለመከከስ መብት አንስቷል።

ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው በሙስና ተጠርጥረው እንደሆነ በም/ቤቱ የሰላም ፣ ፍትህ እና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገልጿል።

ኮሚቴው ምን አለ ?

" ከሜክሲኮ እስከ ቄራ ባለው የኮሪደር ስራ ያልተካተቱ እና በመንግሥት ይፈርሳሉ ተብለው ያልተያዙ የመንግሥት ቤቶችን ከባለሃብት እና ከሰራተኞች ጋር በመመሳጠር ግምታቸው ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ኮንዶሚኒየም ቤት እንዲሰጥ አድርገዋል።

የፈረሱት የመንግሥት ቤቶች ግለሰቦች ተከራይተውት የነበረ ነው።

እነዚህን ቤቶች እንዲፈርሱ አስደርገው ይዞታውን ከቤቶቹ አጠገብ ለተሰራው " ዋይልድ አፓርትመንት " ለተባለ ህንጻ ባለቤት  ምቹ በማድረግ ግንባታ እንዲገነባና የግሉ እንዲያደርገው ለማድረግ ተንቀሳቅሰዋል።

አጠቃላይ 6 መኖሪያ ቤቶች እና 1 ንግድ ቤት ፦
- ግለሰቦች እየኖሩበትና ንግድ እየተከናወነ ባለበት፤
- ካቢኔው ይፍረሱ ብሎ ባልወሠነበት
- ፕላን፣ ፎርማት እና የካቢኔ ውሳኔ ባልተያዘበት በ503 ካ/ሜ ላይ ያረፉትን ቤቶች እንዲፈርሱ ሰራተኞችን ሰብስበው በማስወሰንና ትዕዛዝ በመስጠት ፤ ቤቶቹ ያሉበት ቦታ በአካል ጭምር በመሄድ እንዲፈርስ መመሪያና ትዕዛዝ ሰጥተዋል።

የመንግሥት መኖሪያ ቤቶች ውስጥ በኪራይ ይኖሩ ለነበሩት ግለሰቦች አጠቃላይ 3,383,202 ብር ከ77 ሳንቲም የሆኑ 6 የጋራ መኖሪያ ኮንዶሚኒየም ቤቶች እንዲሰጣቸው አድርገዋል።

ይዞታውን ሀጂ በገን ኸይሩ ነጋሽ ለተባሉ  በአካባቢው አፓርትመንት ላላቸው ግለሰብ እንዲሰጥና ግንባታ እንዲገነባበት አድርገዋል።

ተጠርጣሪው ለዚህ ስራ ጉቦ መቀበሉ ማስረጃ አለን ብሏል።

በባለቤታቸው ስም ከባለሃብቱና ከድርጅቱ 6 ሚሊዮን ብር ጉቦ ተቀብለዋል። ይህን ብር ከሌላ ግለሰብ ካተላለፈው 8 ሚሊዮን ብር ጋር በመቀላቀል በባንክ ብድር ለገዙት 30,000,000 ብር ለሚያወጣ ቤት 14,000,000 ብር ለቤቱ ግዥ ብድር ክፍያ ከፍለዋል ፤ በዚህም የሙስናና ህገወጥ ገንዘቡን ህጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል መፈጸም ምርመራ እየታጣራ ይገኛል " ብሏል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ መምህራንን ፈተና ለመፈተን እየተዘጋጀ መሆኑ ተሰማ።

ትምህርት ሚኒስቴር፤ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚያስተምሩ መምህራንን ብቃት ለመመዘን ፈተና ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

በሚኒስቴሩ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት እዮብ አየነው(ዶ/ር ) ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ በሰጡት ቃል ፥ " የመምህራን ፈተና ከዚህ በፊት በአንደኛ ደረጃ በሚያስተምሩት ላይ ተሞክሮ ነበረ በመሆኑም አልተጀመረም ማለት አይቻልም " ብለዋል።

አሁን ግን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንን ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ አስረድተዋል።

ዝግጅቱ እንዳለቀ በዚህ ዓመት ወይም በቀጣዩ 2018 ዓመት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መመህራን ፈተና መሰጠት ይጀምራል ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
#InfinixEthiopia

የኢንፊኒክስ ስማርት ስልኮች የሆኑትን ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ሲገበያዩ የሽልማት ኩፖን ይውሰዱ፡፡ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ በመጠቀም የማህበራዊ ገጾት ላይ ይለጥፉ የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት ፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን ያሸንፉ፡፡

መመሪያ

1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡

Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
#እንድታውቁት

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙት 16 ቅርንጫፎች አገልግሎት ለማግኘት " ፋይዳ " ዲጂታል መታወቂያ ወይም የተመዘገቡበትን ማስረጃ ማቅረብ ግዴታ ተደርጎ እየተሰራበት ነው።

@tikvahethiopia
አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ከትላንት ጀምሮ መሾማቸው ተሰምቷል።

አምባሳደር ሽፈራው ወደ ህብረት ስራ ኮሚሽነርነት እስከ ተሾሙበት ጊዜ ድረስ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣንን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ ቆይተዋል።

የኢትዮጵያ ኅበረት ሥራ ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት ጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) ከወር በፊት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል።

አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ፤ ኢህአዴግ ከመፍረሱ በፊት በተለያዩ የክልልና የፌዴራል የስልጣን እርከኖች ላይ ኢህአዴግ ፈርሶ ብልፅግና ከመጣም በኃላ በተለያዩ የስልጣን እርከኖች ላይ ተሹመው እየሰሩ ናቸው።

በሌላ በኩል ፤ በአምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ምትክ አህመድ አብተው (ዶ/ር) የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ከትላንት ጀምሮ እንደ ተሾሙ ሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ዘግቧል።

@tikvahethiopia