TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ትኩረት🚨

" የጤና ተቋሙ ሳይፈርስ ከላይ ያሉ አካላት አስቸኳይ ድጋፍ ቢያደርጉ መልካም ነው "  - ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል

በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ስር የሚገኘው የዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል በክልሉ ተፈጥሮ ከነበረው ጦርነት በፊት ለመድሃኒትና ለላብራቶሪ ግብዓቶች ይመደብለት የነበረው በጀት ከ60 ሚሊየን ብር በላይ ነበር።

በሆስፒታሉ የመድኃኒት እና የላብራቶሪ መመርመሪያ ግብዓቶች እጥረት ስለማጋጠሙ በተደጋጋሚ ሲነገር ቢቆይም ችግሩን እስካሁን መቅረፍ እንዳልተቻለ ተነግሯል።

በሆስፒታሉ ላይ ላጋጠመው እጥረት ለዩኒቨርሲቲው ይመደብ የነበረው በጀት በግማሽ መቀነሱ እንደምክንያት ይነሳል።

ለሆስፒታሉ ለመድኃኒትና ለላብራቶሪ መመርመሪያ ግብዓቶች አቅርቦት በ2016 በጀት ዓመት ተመድቦለት የነበረው 18.9 ሚሊየን ብር ሲሆን ለ 2017 በጀት ዓመት የተመደበለት ደግሞ 30 ሚሊየን ብር ብቻ ነው።

በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዓይደር ኮምፕረንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስተዳደር እና ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ኃይለስላሴ በርኸ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት ሆስፒታሉ በ2016 በጀት ዓመት ከ ኢትዮጵያዊ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በብድር የወሰደው መድኃኒት ከ 60-70 ሚሊየን ብር ይደርሳል ብለዋል።

በብድር የወሰደውን የመድኃኒት ክፍያ ሆስፒታሉ መክፈል ባለመቻሉ 14.3 ሚሊየን ብር ከጤና ሚንስቴር ለመድኃኒት አቅራቢ ድርጅት እንዲከፈል ሆኗል።

ሆስፒታሉ የተወሰነ ክፍያ የከፈለ ቢሆንም ያልተከፈለ ከ 40 ሚሊየን ብር በላይ ክፍያ እዳ ከ 2016 ወደ 2017 በጀት ዓመት የተላለፈበት ሲሆን በዚህ ምክንያት ከዚህ በኋላ ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት መድኃኒቶችን በካሽ እንጂ በብድር እንደማያገኝ ተነግሮታል።

ሆስፒታሉ ከውስጥ ገቢው እዳውን መክፈል ለምን ተሳነው ?

ዶ/ር ኃይለስላሴ እንደሚሉት በዓይደር ሆስፒታል የሚታከሙ ታካሚዎች ከ 80-90 በመቶ የነጻ ታካሚዎች ናቸው።

" ከፍለው መታከም የማይችሉ ታካሚዎች የደሃ ደሃ መሆናቸውን ከወረዳቸው ያጽፋሉ ወረዳውም ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በሚገባው ውል መሰረት ጤና ቢሮው ከእኛ ጋር ውል ያስራል ያከምናቸውን ታካሚዎችም በ3 ወር ወይም በ6 ወር ለሆስፒታሉ ይከፍላል" ብለዋል።

ስለዚህ የምናክማቸው ታካሚዎች እነርሱ በቀጥታ ባይከፍሉም ከጤና ቢሮው ክፍያው እንዲፈጸም የሚደረግ በመሆኑ ነጻ ናቸው ማለት አይደለም ብለዋል።

ይሁን እንጂ ሆስፒታሉ በተጠቀሰው መንገድ ሲያክም ቆይቶ ክፍያው እንዲፈጸምለት ለጤና ቢሮው ጥያቄ ቢያቀርብም "በትግራይ የምዕራብ እና የደቡብ አካባቢዎች የሚገኙ አንዳንድ ወረዳዎች በትግራይ ስር ስላልሆኑ እና በርካታ መጠለያ ጣቢያዎች በመኖራቸው እንዲሁም ታካሚዎችም ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ በመሆናቸው ከየትም አምጥቼ ገንዘብ መሰብሰብ አልቻልኩም " የሚል ምላሽ መስጠቱን ተናግረዋል።

በዚህም ምክንያት ሆስፒታሉ ከጤና ቢሮው ሊከፈለው የሚገባ በርካታ ሚሊየን ብር ስለቀረበት መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ላይ ያለበትን የ40 ሚሊየን ብር በላይ እዳ መክፈል እንዳልቻለ ገልጸዋል።

በተጨማሪም በመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በኩልም የማይገኙ እንደ የስነ-ልቦና እና የካንሰር መድሃኒቶች ፣ ካቴተር ፣ ለመስፋት የሚያገለግሉ ስቲቾች (Stitches) እንዲሁም እንደ ማግኒዢየም ሰልፌት ያሉ መድኃኒቶችም መኖራቸውን ጠቁመዋል።

በአገልግሎቱ በኩል አይገኙም የተባሉትን መድኃኒቶች ለመግዛት ወደ ሌሎች አቅራቢዎች ለግዢ ጨረታ ይወጣል ፤ ከውጭ ሲገዛ በጣም ውድ በመሆኑ ሳቢያ ሆስፒታሉ ለመድኃኒት ካለው ትንሽ በጀት ጋር ተደምሮ ለገንዘብ እጥረት እንዳጋለጠው ጠቁመዋል።

አሁን ካለው የኑሮ ውድነት ጫና ጋር ተደምሮ ከዚህ በፊት ለዓመት ያስገዛ የነበረ ገንዘብ ለሁለት እና ሦስት ወርም አይቆይም ብለዋል።

ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች ሆስፒታሉ እዳውን መክፈል እንደተሳነው ገልጸዋል።

" በካሽ ካልሆነ በብድር ይሰጥ የነበረ መድኃኒት ከዚህ በኃላ እንደሌለ ከአገልግሎቱ ተነግሮናል " ብለዋል።

በዚህም ሳቢያ በሆስፒታሉ በተለይም የስነ አዕምሮ ፣ የማደንዘዣ እና ለመስፋት የሚያገለግሉ ግብዓቶች እጥረት በከፍተኛ ሁኔታ ማጋጠሙን ተሰምቷል።

በሆስፒታሉ የማይገኙ መድኃኒቶችን ታካሚዎች ከውጭ በውድ ዋጋ እንዲገዙ መገደዳቸውን ተናግረዋል።

እንደሆስፒታሉ መረጃ በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የስነ አዕምሮ መድኃኒቶች ፍላጎት እየጨመረ ነው።

ሆስፒታሉ ካለበት የበጀት እጥረት በተጨማሪ ከፍተኛ የሆነ የባለሞያዎች ፍልሰት እንዳጋጠመው የተሰማ ሲሆን ከህክምና ት/ቤቱ ብቻ ከ300 በላይ ሐኪሞች መሰደዳቸውን ተናግረዋል።

አብዛኛዎቹ ባለሞያዎች የተሰደዱት ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ ነው።

ዶክተር ፥ " አብዛኛው ሃኪም የሄደው ወደ ሶማሊያ፣ ፑንትላንድ እና ሶማሊላንድ ነው ለመኖር አስቸጋሪ ቢሆኑም የሚከፈላቸው ክፍያ ጥሩ ስለሆነ ለመኖር አዳጋች ወደ ሚባሉ ቦታዎች እየተሰደዱ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

በሆስፒታሉ ለህክምና ባለሞያዎች ያልተከፈለ የ17 ወር ደሞዝ እና የ22 ወር የትርፍ ሰዓት ክፍያ እስካሁን እንዲከፈል አልተደረገም።

በሆስፒታሉ ስላጋጠመው እዳ በቀጣይ ምን ታስቧል ? ለሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ " ምንም እንኳን በጽሁፍ ያቀረብነው ጥይቄ ባይኖርም ጤና ሚኒስቴር ድጋፍ እንዲያደርግልን ወይም የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የእዳ ስረዛ እንዲያደርግልን ለመጠየቅ እያሰብን ነው " ብለዋል።

" ሆስፒታሉ ከሚገኝበት ውስብስብ ችግር ምክንያት የጤና ተቋሙ ሳይፈርስ ከላይ ያሉ አካላት አስቸኳይ ድጋፍ ቢያደርጉ መልካም ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

በመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በኩል የማናገኛቸው መድኃኒቶች አሉ ስለሚለው ቅሬታ እና ሆስፒታሉ ስላለበት እዳ ምን ታስቧል ? የሚለውን በሚመለከት የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የመቀሌ ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ አለማየሁ ገብረማርያምን አነጋግረናል ምላሻቸው በቀጣይ ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ከሳቸው የተሻለ ሰው አይገኝም " - ትራምፕ

ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ በአሜሪካ የሚገኙ ህጋዊ ሰነድ የሌላቸውን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስደተኞችን እንደሚያባርሩ የገቡትን ቃል የሚያስፈጽሙላቸውን ቶም ሆማን የተባሉ ባለስልጣን ሾመዋል።

የአሜሪካ ድንበር ቁጥጥር ዋና ባለስልጣን " ቦርደር ዛር " ሆነው የተሾሙት በአንድ ወቅት የሀገሪቱ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ጉዳይ ዋና መሥሪያ ቤት ተጠባባቂ ዳይሬክተራቸው ነበሩ።

ትራምፕ " ለድንበሮቻችን ጥበቃ እና ቁጥጥር ከሳቸው የተሻለ ሰው አይገኝም " ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በስደተኞች ጉዳይ አክራሪ አቋም ያላቸውን ስቲቭን ሚለር የተባሉ ግለሰብን የጽህፈት ቤታቸው የፖሊሲ ጉዳዮች ምክትል ኅላፊ አድርገው እንደሚሾሟቸው ቪኦኤ ዘግቧል።

ትራምፕ ስራ ሲጀምሩ የመጀመሪያ ተግባራቸው ሀገሪቱ ውስጥ ይገኛሉ ያሏቸውን እጅግ በጣም በርካታ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች ከሀገር ማባረር እንደሆነ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከሳቸው የተሻለ ሰው አይገኝም " - ትራምፕ ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ በአሜሪካ የሚገኙ ህጋዊ ሰነድ የሌላቸውን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስደተኞችን እንደሚያባርሩ የገቡትን ቃል የሚያስፈጽሙላቸውን ቶም ሆማን የተባሉ ባለስልጣን ሾመዋል። የአሜሪካ ድንበር ቁጥጥር ዋና ባለስልጣን " ቦርደር ዛር " ሆነው የተሾሙት በአንድ ወቅት የሀገሪቱ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ጉዳይ ዋና መሥሪያ ቤት ተጠባባቂ…
#Canada

ካናዳ በስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንደሆነች ተሰምቷል።

ካናዳ ዶናልድ ትራምፕ ልክ ስራ ሲጀምሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞችን ከሀገር ለማባረር ከያዙት እቅድ ጋር በተያያዘ ሊከሰት ለሚችል ማንኛውም ነገር የራሷን ዝግጅት ማድረግ መጀመሯ ተሰምቷል።

በዶናልድ ትራምፕ እቅድ ምክንያት ወደ ሀገሪቱ ለመግባት የሚሞክሩ የስደተኞች ቁጥር ሊበዛ ይችላል በሚል ስጋት የራሷን ዝግጅት እያደረገች ነው።

የትራምፕ ትግበራ በካናዳ ድንበር የጥገኝነት ጠያቂዎችን (asylum) ቁጥር ያበዛዋል በሚል ስጋት ተደቅኗል።

ካናዳ ሂደቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ትገኛለች የተባለ ሲሆን ሊከሰት የሚችለውን ማንኛውም አይነት ሁኔታ ለመቆጣጠር ዝግጅት እያደረገች ነው።

የትራምፕ ጥብቅ የኢሚግሬሽን ፖሊሲ ሚሊዮኖችን ማባረር እና የዜግነት ህግን መቀየርን ያጠቃልላል። ይህም ብዙ ሰዎች በህገወጥ መንገድ ወደ ካናዳ ለመሻገር እንዲሞክሩ ሊያደርግ ይችላል።

የካናዳ ባለስልጣናት በድንበር ላይ ሊከሰት የሚችለውን ችግር ለመፍታት ከወዲሁ ዝግጅት እያደረጉ ነው።

ብዙዎች የትራምፕ እርምጃ ወደ ካናዳ ትልቅ የስደተኞች ማዕበል ይዞ ይመጣ ይሆን ? ብለው እያሰቡ ናቸው።

ባለስልጣናቱ ግን የደንበር ቁጥጥርን ለማጠናከር እንዲሁም በህገወጥ መንገድ ሰዎች እንዳይገቡ ፣ ድንበር ላይም ችግር እንዳይፈጠር ትኩረት አድርገው እየሰሩ ነው ተብሏል።

@tikvahethiopia
Rosewood Furniture
ሮዝዉድ ፈርኒቸር

ዉበት! ጥንካሬ! አገልግሎት!

የተሟላ አገልግሎት የሚሰጥ ፈርኒቸር ለእርሶ በሚሆን መልኩ!

ደረጃዉን የጠበቀ ዲዛይን በማዘጋጀት የምንሰራልዎት ፈርኒቸር ምን እንደሚመስል በቅድሚያ ሙሉ እይታ እንዲኖርዎት እናደርጋለን!

What you see is what you will actually  get 👌


ይደውሉልን🤙📲   0905848586
Text us 💬   @Rosew0od

ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ  👇
https://t.iss.one/R0seWood
https://t.iss.one/R0seWood
https://t.iss.one/R0seWood

#Rosewood #Furniture
#SafaricomEthiopia

💯 የድምጽ ጥቅሎችን እየገዛን በ100% ጉርሻ ደቂቃዎች እንንበሽበሽ!! ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት⚡️

🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details...
የቴሌግራም ቦታችንን https://t.iss.one/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
ፎቶ ፦ በራስ ገዟ ሶማሌላድ ዛሬ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እየተካሄደ ነው።

ህዝቡ ከጥዋት አንስቶ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመሄድ ድምጹን እየሰጠ ይገኛል።

በምርጫው የአሁን ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ከአብዲራህማን ኢሮ እንዲሁም ከፋይሰል አሊ ዋርቤ ጋር ይፎካከራሉ።

ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ተገንጥላ እራሷን እንደ ነጻ ሀገር የምትቆጥር ናት። ላለፉት በርካታ አመታት ከሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ጋር ምንም ግንኙነት የላትም።

የራሷን መሪ / ፕሬዜዳንቶችን በሰላማዊ መንገድ ስትመርጥ ኖራለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " ያለደረሰኝ አትሽጡ አልን እንጂ እቃ እንወርሳለን ያለ አካል የለም " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ " በከተማዋ በርካታ ነጋዴዎች በግብር ከፋይነት ተመዝግበው ደረሰኝ የማይሰጡ በመሆናቸው እና ችግሩም በጣም እየሰፋ በመሆኑ ወጥነት ባለው መንገድ ህጉን እንዲያከብሩ እና ወደስርዓት እንዲገቡ ለማድረግ እየሰራው ነው " ሲል ገልጿል። ቢሮው የታክስ ኢንተለጀንስ…
#Update

" ግለሰቦቹ ከአንዳንዶቹ ነጋዴዎች ባዘጋጁት ተሽከርካሪ እቃዎችን ጭነው ሄደዋል " - ቢሮው

ሰኞ ዕለት በመርካቶ ያሉ ነጋዴዎች " ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ነው የመጣነው " ያሉ ሰዎች ያለ ደረሰኝ ለምን ሸጣችሁ በሚል እቃችንን ወርሰውብናል ብለዋል።

በዚህና ተያያዥ ምክንያቶች በእለቱ በመርካቶ ያሉ በርከት ያሉ ሱቆች ዝግ ሆነው ውለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ፥ የተባለው ችግር በመርካቶ እንደተፈጠረ አምኖ ነገር ግን የነጋዴዎችን እቃ ወርሰዋል የተባሉት ግለሰቦች ከገቢዎች ቢሮም ይሁን ከየትኛውም የመንግስት አካል ያልተወከሉ ህገ ወጦች ናቸው ሲል ማመልከቱን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ዘግቧል።

የታክስ ኢንቴሌጀንስና ምርመራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተስፋዬ ነጋሽ " እኛ ምንም አይነት ንብረት የመውረስ መብት የለንም መወረስ ካለበትም ይህንን የሚሰራው የጉምሩክ ኮሚሽን ነው " ብለዋል፡፡

" ግለሰቦቹ ከአንዳንዶቹ ነጋዴዎች ባዘጋጁት ተሽከርካሪ እቃዎችን ጭነው ሄደዋል፤ ከአንዳንዶቹ ነጋዴዎች ደግሞ ገንዘብ ተቀብለው ተሰውረዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ነጋዴዎቹ ለፀጥታ አካላት መረጃዎችን በመስጠት ተባባሪ እንዲሆኑ ጠይቀዋል፡፡

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ " መንግስት ከመርካቶ ገበያ የነጋዴዎችን እቃ መውረስ ጀመረ " ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ግን ከእውነት የራቀ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ውዥምብሩ የተፈጠረው በዚህ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የከተማዋ ገቢዎች ቢሮ ከዚህ ቀደም ይሰራ እንደነበረው ያለ ደረሰኝ ግብይት እንዳይፈፀም ለማድረግ ያለመ የቁጥጥር ስራ እነደሆነ ኃላፊው ጠቁመዋል።

ከህዳር 1 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዘመቻ መልክ ነው እየተሰራ ያለው።

ከዚህም በተጨማሪ ቢሮው በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የመርካቶን የንግድ እንቅስቃሴ የሚቆጣጠሩ ባለሙያዎች " ያለ እጅ መንሻ " የማይሰሩ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብሎ ሁሉንም የመርካቶ ተቆጣጣሪዎችን በማንሳት በአዲስ መተካቱንም ተናግሯል።

ያለ ደረሰኝ ሲገበያይ የተገኘን ማንኛውም ሰው 100 ሺህ ብር እንደሚቀጣም አሳውቋል።

ቢሮው መርካቶን ጨምሮ በሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች ያሉ አምራቾች፣ አስመጪዎችና ቸርቻሪዎች የትኛውንም ግብይት በደረሰኝ እንዲፈፅሙ ይገደዳሉ ማለቱን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ገልጿል።

ነጋዴዎች ምን ይላሉ ?

በመርካቶ ያለው ችግር ውስብስብ ያለና ከላይ ጀምሮ መጥራት ያለበት ነው።

በተለይ ደግሞ የገቢዎች ተቆጣጣሪ የሚባሉት ያለ ገንዘብ ያለ ሙስና አይሰሩም።

ሆን ብለውም የማስጨነቅ ስራ በመስራት ከነጋዴው ገንዘብ የመቀበልን ተግባራ ስራቸው ያደረጉ እንዳሉ ይገልጻሉ።

ያለ ደረሰኝ ግብይት ተደረገ ተብሎም የገንዘብ ድርድር የሚያደርጉ ተቆጣጣሪዎችም አሉ።

ደረሰኝን በተመለከተ ቸርቻሪው ላይ ጣትን ከመቀሰር ከላይ ጀምሮ ያለውን ነገር ማጥራት እንደሚገባ ነጋዴዎች ጠቁመዋል።

#AddisAbaba #Merkato

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ግለሰቦቹ ከአንዳንዶቹ ነጋዴዎች ባዘጋጁት ተሽከርካሪ እቃዎችን ጭነው ሄደዋል " - ቢሮው ሰኞ ዕለት በመርካቶ ያሉ ነጋዴዎች " ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ነው የመጣነው " ያሉ ሰዎች ያለ ደረሰኝ ለምን ሸጣችሁ በሚል እቃችንን ወርሰውብናል ብለዋል። በዚህና ተያያዥ ምክንያቶች በእለቱ በመርካቶ ያሉ በርከት ያሉ ሱቆች ዝግ ሆነው ውለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ፥ የተባለው ችግር…
" የቢሮ ሰራተኛ መሆናቸውን መታወቂያና መለያ ባጅ ጠይቋቸው  " - ገቢዎች ቢሮ

ዛሬ የገቢዎች ቢሮ መርካቶ ሸራ ተራ አካባቢ " በገቢዎች ቢሮ ሰራተኛ " ስም ሲያጭበረብር ነበረ የተባለ ግለሰብ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል።

ቢሮው ከአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ጋር አካሄድኩት ባለው ክትትል ነው ግለሰቡ የተያዘው።

በቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪ ግለሰብ በመርካቶ ገበያ በአንድ ግለሰብ ሱቅ ውስጥ በመግባት የዕቃዎች ደረሰኝ ሲጠይቅና ሲያጭበረብር በደረሰ ጥቆማ መሠረት ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ መያዙን ቢሮው አስረድቷል።

ቢሮው " የንግዱ ማህበረሰብ ማንኛውም በግል ወይም በቡድን የሚንቀሳቀሱ አጭበርባሪዎች ወደ ንግድ ስፍራቸው ሲመጡ የቢሮ ሰራተኛ መሆናቸውን መታወቂያና መለያ ባጅ በመጠየቅ ሊያረጋግጥ ይገባል " ብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ አጠራጣሪ ድርጊቶች ሲያጋጥሙት በነፃ የስልክ መስመር  7075 በመጠቀም እንዲጠቁም ጥሪ አቅርቧል።

በተለይ መርካቶ ገበያ የሚሰሩ ዜጎች " ከገቢዎች ነው የመጣነው " በሚሉ አካላት በሆነው ባልሆነው ገንዘብ እንደሚጠየቁ ፤ " ያለ ደረሰኝ ስትሸጡ ነበር " በማለትም የገንዘብ ድርድር አድርገው ከነጋዴዎች ገንዘብ የሚቀበሉ ሰራተኞች እንዳሉ ይናገራሉ።

በአንዳንድ ሰራተኞች ምክንያት ስራ መስራት እንዳልተቻለና ከነጋዴው ገንዘብ የሚቀበሉትም የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠር መሆኑንም አስረድተዋል።

በዚህም በቸርቻሪው ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እንደሚደርስ በማመልከት ቢሮው መጀመሪያ የራሱን ሰራተኞች እንዲጠራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠቱት ቃል ጠይቀዋል።

#AddisAbaba #Merkato

@tikvahethiopia
" መኪናው አስፓልት ዳር ቆሞ ቢገኝም ውስጥ የነበረው እቃ ግን ተዘርፎ ተወስዷል " - አመልካቾች

ከሰሞኑን አንድ ዝርፊያ በአዲስ አበባ ተፈጽሟል።

ከላይ በምስሉ ላይ የሚታየው ታርጋ ቁጥሩ ኮድ 3 - 00434 አ.አ የሆነ እቃ ጫኝ አይሱዙ መኪና ከነጫነው እቃ በተደራጁ ዘራፊዎች ተወስዶባቸው እንደነበር ባለቤቶቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ከጫነው እቃ ጭምር የተዘረፈውን መኪና ያዩ ወገኖችም እንዲያፏልጓቸው ብዙ ሲጥሩ ከቆዩ በኃላ ንብረቱ ተወስዶ መኪናው ግን ሃና ማርያም አካባቢ መንገድ ዳር ቆሞ ተገኝቷል።

ዝርፊያው እንዴት ተፈጸመ ?

መኪናው ከቀናት በፊት ከኮዩ ፈጬ የንግድ እቃ ጭኖ መርካቶ ለማራገፍ መንገድ ይጀምራል።

ሳር ቤት ኪንግስ ሆቴል አከባቢ ሲደርስ ግን የወታደር ሬንጀር ልብስ የለበሱ እና የታጠቁ
ሰዎች በአባዱላ መኪና መንገድ በመዝጋት መኪናውን ያስቆሙታል።

በተጨማሪም ልክ የህግ አስከባሪ አካላት (ወታደር) እንደሆኑ በማስመሰል ሹፌሩን " መንጃ ፍቃድ አምጣ " ብለው ጠይቀው ህገወጥ እቃ እንደጫነ ጥቆማ ደርሷቸው ያስቆሙት መሆኑን እና መኪናው ለፍተሻ የሚፈለግ መሆኑን ይገልጻሉ።

ሹፌሩም የጫነው እቃ መርካቶ የሚራገፍ የንግድ እቃ መሆኑን ገልፆ እቃው የተገዛበትን ደረሰኝ በማሳየት ጭምር ለማስረዳት ይሞክራል።

ይሁንና ግን ልክ እንደ ህግ አስከባሪ / ወታደር ልብስ ለብሰውና ታጥቀው እና ተደራጅተው የመጡት ዘራፊዎች " መኪናው ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ መፈተሸ አለበት " በማለት ሹፌሩን እያዋከቡ እና እየደበደቡ አውርደው ወደያዙት አባዱላ መኪና ያስገቡታል።

የእነርሱ ሹፌር ደግሞ ወደ አይሱዙው ገብቶ መኪኖቹ ፊት እና ኋላ ሆነው እየተከታተሉ ይሔዳሉ፡፡

ይሁንና ግን ቡልጋሪያ አከባቢ ሲደርሱ አይሱዙው ወደ ሌላ አቅጣጫ ሲያመራ ሹፌሩን የጫነው አባዱላ ደግሞ ወደ ሌላ አቅጣጫ ይዞራል።

በዚህ ሰዓት ሹፌሩ " ህግ ቦታ እየወሰድንህ ነው አላላችሁኝም ወይ ? ለምንድነው መኪናው ወደ ሌላ አቅጣጫ የሚሔደው ? " የሚል ጥያቄ ሲያነሳ ውስጥ ያሉት ዘራፊዎች ሹፌሩን እራሱን እስከሚስት ድረስ በመደብደብ እና በማፈን ጭምብል አልብሰው በፍጥነት እየነዱ ይጓዛሉ።

በዚህ ሁኔታ ለረጅም ርቀት ከተጓዙ በኋላ ኃጫሉ መንገድ ወደ ጋርመንት መሔጃው ጋር ሹፌሩን ከመኪናው አውርደው ጥለውት ይሰወራሉ።

ሁኔታው ከተፈጠረ በኋላ አከባቢው ላይ የደረሱ ሰዎች ሹፌሩን አፋፍሰው ጤና ጣቢያ ያደረሱ ሲሆን ሹፌሩም አራሱን ከመሳት ከነቃ በኋላ ጉዳዩን ወንጀሉ ለተፈፀመበት አከባቢ ፖሊስ ጣቢያ አመልክቷል።

ከቀናት በኃላ በተደረገ ፍለጋ መኪናው ሃና ማርያም አስፓልት ዳር ቆሞ ሊገኝ ችሏል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መኪና ከጫነው እቃ ጭምር እንደተዘረፈባቸው የገለጹት አመልካቾች ፥ " ምንም እንኳን መኪናው ቆሞ ቢገኝም ውስጥ ተጭኖ የነበረው ከ3.4 እስከ 4 ሚሊዮን ብር የሚገመት እቃ ተዘርፎ ተወስዷል " ብለዋል።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ እስካሁን የተያዘ ሰው እንደሌለ ጠቁመዋል።

ሌሎች ወገኖች መሰል ነገር እንዳይፈጸምባቸው በማለት ይህንን ጉዳይ ለጥንቃቄ ይረዳ ዘንድ ማጋራታቸውን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia