TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደረገ። የ2017 የቴክኒክና ሙያ የመደበኛ ስልጠና ዘመን መቁረጫ ነጥብ ዛሬ ይፋ ተደርጓል። የመቁረጫ ነጥቡ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia
የ2017 የቴክኒክና ሙያ የመደበኛ ስልጠና ዘመን መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆኗል።

የተፈጥሮ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት !

🟢 የስልጠና ደረጃ 1 እና 2

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 141 እና ከዚያ በታች፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 137 እና ከዚያ በታች፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 138 እና ከዚያ በታች፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 134 እና ከዚያ በታች፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤

🟡 የስልጠና ደረጀ 3 እና 4 ፦

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 142 እና ከዚያ በላይ፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 138 እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 139 እና እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና ከዚያ በላይ፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤

🔴 የስልጠና ደረጀ 5 ፦

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 179 እና ከዚያ በላይ፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 167 እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 170 እና እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 162 እና ከዚያ በላይ፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 154 እና ከዚያ በላይ፤

⬇️

የማህበራዊ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት !

🟢 የስልጠና ደረጃ 1 እና 2

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 139 ከዚያ በታች፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና ከዚያ በታች፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 134 እና ከዚያ በታች፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤

🟡 የስልጠና ደረጀ 3 እና 4 ፦

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 140 ከዚያ በላይ፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 136 እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤

🔴 የስልጠና ደረጀ 5 ፦

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 172 ከዚያ በላይ፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 164 እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 165 እና እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 160 እና ከዚያ በላይ፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 154 እና ከዚያ በላይ፤


#TikvahEthiopia🇪🇹

@tikvahethiopia
267🙏77🤔35👏32😭29🕊19😡17😢16😱14🥰10
#MoE

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባ በቅርቡ እንደሚገለጽ አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ፤ " በ2016 የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ምደባ በቅርቡ ይገለጸል " ብሏል።

ተማሪዎች በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
🙏978😡432160😭96🤔60👏46🕊43😢41😱35🥰34
#MPESASafaricom

መልካም ሰኞ! መልካም ሳምንት!🙌
💫ከዳር እስከ ዳር በፈጣኑ የሳፋሪኮም ኢንተርኔት! እንገናኝ! የተመቸንን ሼር እናድርግ!👍ከወደድነው ጋር እንደልብ እንገናኝ!
አስተማማኙን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!
የቴሌግራም ቦታችንን https://t.iss.one/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!

#SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
👏5850🙏15😡15🥰7🤔6😭6😢2😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
" የጥቅምት ወር ደመወዝ ክፍያ በአዲሱ የተሻሻለው ስኬል መሆን ይጀምራል " - አቶ አህመድ ሽዴ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ፤ የጥቅምት ወር ደመወዝ ክፍያ በአዲሱ የተሻሻለው ስኬል መሆን እንደሚጀምር አሳውቀዋል። " ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ደመወዝ በካቢኔ ተወስኗል። ባለፉት ሳምንታት በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ቅድመ ዝግጅቱ አልቋል ፤ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንም በኩል ቅድመ ዝግጅት አልቋል…
#ደመወዝ : የደመወዝ ጭማሪ ተፈቅዶና በጀቱም ጸድቆ ክፍያው ከጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም.  ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዛሬ አሳውቋል።

ከገንዘብ ሚኒስቴር የተፈቀደው በጀት፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የክፍያ ትዕዛዙን ለ12ቱ ክልሎች፣ ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና ለፌደራል ተቋማት ዛሬ መተላለፉም ተገልጿል።

(ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይፋዊ የደመወዝ ስኬል ከላይ ተያይዟል)

#CivilServiceCommission
#MekuriaHaile

@tikvahethiopia
😡1.17K510😭236🙏117😢78🤔54🕊46👏44😱29🥰22
" እሳቱ ጠንከር ያለ ነው ፤ እስካሁን አልጠፋም ፤ ሰው ንብረት እያሸሸ ነው " - በስፍራው የሚገኙ ሰዎች

በአዲስ አበባ መርካቶ ሸማ ተራ የእሳት አደጋ ተከስቷል።

እሳቱ ከተነሳ በርከታ ደቂቃዎች ቢቆጠሩም እስካሁን መቆጣጠር እንዳልተቻለ በስፍራው የሚገኙ የቤተሰባችን አባላት ገልጸዋል።

" እሳቱ ጠንከር ያለ ነው ፤ በስፍራው እሳት አደጋዎች ለመቆጣጠር ጥረት እያደረጉ ቢሆንም ምንም ሊጠፋ አልቻለም። በስፍራው ላሉ የአደጋ ሰራተኞች ተጨማሪ ቦቴና እገዛ ያስፈልጋል ፤ በውሃ ብቻም የሚሆን አይደለም " ብለዋል።

" በአካባቢው ያሉ እሳቱ ያልደረሰባቸው ሰዎች ንብረታቸውን እያሸሹ ይገኛሉ " ሲሉም አክለዋል።

@tikvahethiopia
😱1.17K😭667😢152🙏133131🕊54🥰26👏24🤔24😡24
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update በመርካቶ ' ሸማ ተራ ' የተነሳው እሳት እስካሁን ሊጠፋ አልቻለም።

እሳቱን ለመቆጣጠር ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም ከእሳቱ መፋፋምና ከቦታው አለመመቸት የተነሳ ሁኔታውን እንዳከበደው በስፍራው የሚገኙ የቤተሰባችን አባላት ጠቁመዋል።

እሳቱ ያልደረሰባቸው ሱቆች እቃቸውን ከስፍራው እያሸሹ ናቸው።

እስካሁን የጉዳቱ መጠን ምን ያህል እንደሆነ ባይታወቀም በርከት ያሉ ሱቆች ግን እየተቃጠሉ ናቸው።

ተጨማሪ መረጀዎችን እንልክላችኋለን።

@tikvahethiopia
😭1.15K😢198109🙏73😱47🕊34🥰27🤔26👏17😡16
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በመርካቶ ' ሸማ ተራ ' የተነሳው እሳት እስካሁን ሊጠፋ አልቻለም። እሳቱን ለመቆጣጠር ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም ከእሳቱ መፋፋምና ከቦታው አለመመቸት የተነሳ ሁኔታውን እንዳከበደው በስፍራው የሚገኙ የቤተሰባችን አባላት ጠቁመዋል። እሳቱ ያልደረሰባቸው ሱቆች እቃቸውን ከስፍራው እያሸሹ ናቸው። እስካሁን የጉዳቱ መጠን ምን ያህል እንደሆነ ባይታወቀም በርከት ያሉ ሱቆች ግን እየተቃጠሉ ናቸው።…
#Update

“ አደጋውን በቁጥጥር ሥር ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው ”  - አቶ ንጋቱ ማሞ

መርካቶ ሸማ ተራ የእሳት አደጋ መከሰቱን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ከኮሚሽኑ ቃላቸውን የሰጡትን አቶ ንጋቱ ማሞ፣  አደጋውን ለመቆጣጠር እርብርብ እየተደረገ ነው ” ብለዋል።

“ ከመሸ ነው ጥሪ የመጣው። ጥሪው እንደመጣ በአቅራቢያው ካሉ የአዲስ ከተማ፣ አራዳ ክፍለ ከተሞች ልከን ነበር ” ብለዋል።

“ ነገር ግን በእነርሱ የሚሸፈን ስላልሆነ ከሁሉም ቅርንጫፍ ጣቢያ የአደጋ መቆጣጠር ማሽነሪዎች፣ አደጋ ጊዜ ሠራተኞች፣ አምቡባንሶች፣ የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች፣ አመራሮች ጭምር ቦታው ላይ ሆነው አመራር እየሰጡ ነው እሳቱን ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር ” ሲሉ አክለዋል።

“ የአደጋ ጊዜ ተሽከርካሪዎች እሳቱ ወደተነሳበህ ቦታ ላይ ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ ቦታው ትንሽ አስቸጋሪ አድርጎታል ” ያሉት አቶ ንጋቱ፣ “ ዞሮ ዞሮ ርብርብ እየተደገ ነው ” ብለዋል።

“ በዚህ ሂደት የጸጥታ ኃይሎች የአካባቢው ማህበረሰብ አሉ። አደጋውን በቁጥጥር ሥር ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።

ያሉትን ሂደቶች እንደሚያደርሱን የገለጹ ሲሆን፣ መረጃው እንደደረሰን የምናጋራ ይሆናል።

ቪድዮ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭1.76K🙏179177😱84😢83🕊43😡36🥰32🤔28👏21
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Update

መርካቶ ' ሸማ ተራ ' የተነሳው ከባድ የእሳት አደጋ እስካሁን አልቆመም።

እሳቱን መቆጣጠር አልተቻለም።

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ " አደጋውን ቶሎ ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለዉን ጥረት  አዳጋች ያደረገዉ የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት ነው " ብለዋል።

አሁን ላይ " በሄሊኮፕተር ለመጠቀም እየጣርን  ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
😭3.64K😢295🙏249173😡143😱77🤔75🕊75👏52🥰42
TIKVAH-ETHIOPIA
#መርካቶ🚨 በመርካቶ ሸማ ተራ የተነሳው እሳት እስካሁን ሊቆም አልቻለም። @tikvahethiopia
#Update

ምሽት 1 ሰዓት አካባቢ በመርካቶ ሸማ ተራ የተነሳውን እሳት እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ስር ማዋል አልተቻለም።

ርብርቡ ግን እንደቀጠለ መሆኑ ተሰምቷል።

የአዲስ አበባ እሣትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍቅሬ ግዛው ምን አሉ ?

- የእሳት አደጋው የተከሰተው 1 ሰዓት ገደማ ነው።

- እሳት መነሳቱን በሰማን ጊዜ አብዛኛዎቹ የእሳት ማጥፊያ መኪናዎች ርብርብ እንዲያደርጉ አሰማርተናል።

- መኪናዎች በወቅቱ ነበር የደረሱት፤ ከደረሱ በኃላ የእሳቱ ባህሪና ሁኔታ ሲታይ ለሌሎች አጋዥ አካላት ፦
° አየር መንገድ
° ፌዴራል ፖሊስ
° ሌሎች ከተማ ውስጥ ያሉ ውሃ አቅራቢ ተቋማት በሙሉ እንዲረባረቡ ተደርጎ እሳቱን ለማጥፋት ጥረት እያደረግን ነው።

- ቦታው በጣም አስቸጋሪ ነው።

- በሁሉም አቅጣጫ በኩል መኪና ገብቶ እሳቱን ለማጥፋት በጣም ፈትኖናል። በተለይ በዙሪያ የሚቀመጡ እቃዎች ቶሎ ተገብቶ የእሳቱን መሰረት እንዳይመታ አድርጓል።

- አካባቢው በቆርቆሮ የተያያዘ ነው። መንገዱ በጣም ጠባብ ነው። ገብተን ለማጥፋት ተቸግረናል።

- በአጋጣሚ ባለሱቆች፣ ነጋዴዎች ዘግተው ወጥተው ነበር። የቆሙ መኪኖችንም ለማስነሳት ችግር ሆኖብን ነበር።

- አሁን ላይ ከቅድሙ እየተሻሻለ ነው። የመቀነስ እና የመጥፋት አዝማሚያ አለው። በተለይ ከዚህ እንዳይሰፋ ወደታች ከወረደ በጣም ሰፊ ቦታ ነው ያለው ቆርቆሮ በቆርቆሮ እሱ ጋር እንዳይደርስ ከበን ለመያዝ ሞክረናል።

- አጋዦች ከመጡ በኃላ እሳቱ ባህሪው እንዳይሰፋ ተሞክሯል። አሁንም ህብረተሰቡ አግዞን ለማጥፋት እየሞከርን ነው። እናጠፋዋለን ብለን እናምናለን።


ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን ከኤ ኤም ኤን ነው የወሰደው።

@tikvahethiopia
😭1.64K🙏258179😢77😱42🕊36😡36🤔27🥰25👏22
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ምሽት 1 ሰዓት አካባቢ በመርካቶ ሸማ ተራ የተነሳውን እሳት እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ስር ማዋል አልተቻለም። ርብርቡ ግን እንደቀጠለ መሆኑ ተሰምቷል። የአዲስ አበባ እሣትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍቅሬ ግዛው ምን አሉ ? - የእሳት አደጋው የተከሰተው 1 ሰዓት ገደማ ነው። - እሳት መነሳቱን በሰማን ጊዜ አብዛኛዎቹ የእሳት ማጥፊያ መኪናዎች ርብርብ እንዲያደርጉ አሰማርተናል።…
#Update

" እዚህ ላይ ባይገታ እሳቱ ሰፊ አካባቢዎች ላይ  ደርሶ ህይወት ያጠፋ ነበር ፤ ሃብትም ይወድም ነበር " - አቶ ፍቅሬ ግዛው

በመርካቶ ሸማ ተራ የደረሰው ውድመት አሳዛኝ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ እሳትና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍቅሬ ግዛው አሁናዊ ሁኔታውን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ኮሚሽነር ፍቅሬ ፤ " አሁን ላይ እሳቱን በቁጥጥራችን ስር አድርገናል ፤ የማጥፋትና የመልቀም ስራ ነው የሚቀረን " ብለዋል።

" እጅግ ከፍተኛ ርብርብ ተደርጎ እዚህ ላይ ባይገታ በጣም ብዙ ቦታ ፣ ሰፊ አካባቢዎች ላይ እሳቱ ደርሶ ህይወት ያጠፋ ነበር ፤ ከዚህ የበለጠ ሃብትም ይወድም ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።

" የአካባቢው አስቸጋሪትነት እሳቱን ለመቆጣጠር ረጅም ሰዓታት ወስዷል " ያሉት ኮሚሽነሩ " ከዚህ በኃላ ብዙ ጉዳት ያደርሳል ብለን አናስብም፤ ተቆጣጥረነዋል ማለት ይቻላል " ብለዋል።

" እሳቱ ዳግም እንዳይቀጥል ቦታውን አዳሩን በሙሉ ተቆጣጥሮ ቅሪት ነገሮች ካሉ እነሱን እያጠፋን እንቀጥላለን ፤ ህብረተሰቡ እሳት ሊያቀጣጥሉ የሚችሉ ነገሮችን ያስወግድ " ሲሉ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከስፍራው ካሉ ነዋሪዎች በደረሰው መልዕክት በእሳቱ በርካታ ንብረት መውደሙን ፣ ከቆርቆሮ ቤቶቹ ወጥቶ አጠገብ ያለ ህንጻ ተያይዞ ከፍተኛ ውድመት መድረሱን፣ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ባይጠፋም ከቅድሙ አንጻር ሲታይ እሳቱ የከፋ እንዳልሆነ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
🙏735😭293177😢79😡68🕊32🤔22👏21🥰17😱9