#Amhara
" በአማራ ክልል ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ አራዝመዋል። ትምህርት ከፓለቲካ ነጻ መሆን አለበት " - የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት
በአማራ ክልል በ " ፋኖ " ታጣቂዎችና በመንግስት መካከል ከአንድ ዓመት በላይ ባስቆጠረው የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች የቅበላ ጊዜ ማራዘማቸው ይህም ደግሞ በተማሪዎች ላይ ጭንቀት መደቀኑ ተሰምቷል።
ዩኒቨርሲቲዎቹ የተማሪዎቻቸውን የቅበላ ጊዜ ማራዘማቸውን እንደተረዳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጸው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት ነው።
የህብረቱ ፕሬዚዳንት ሓየሎም ስዩም፣ " አራት ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ አራዝመዋል " ብሎ ተማሪዎች በጭንቀት ውስጥ በመሆናቸው ባለድርሻ አካላት ለጉዳዩ ትከረት እንዲሰጡ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።
በጸጥታው ችግር የተማሪዎቻቸውን የቅበላ ጊዜ ያራዘሙት፣ " ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ ፣ ደብረ ታቦር እና ኢንጅባራ ዩኒቨርሲቲዎች " መሆናቸውንም ተናግሯል።
" ወሎና ወልዲያ ዩኒቨርሲቲዎች አሁን መንገድ ስለተከፈተ ይቀበላሉ " ያለው የህብረቱ ፕሬዚዳንት ደባርቅ ዩኒቨርቲንም ቅበላውን ሳያራዝም እንዳልቀረ፣ " ሀፋ፣ ሀፋ " የሆነ ሀሳብ ላይ እንደሆነ አስረድቷ።
ህብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ " ትምህርት ከፓለቲካ ነጻ መሆን አለበት " ሲል አሳስቧል።
በአንጻሩ ወልዲያ እና ወሎ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ተቀብለው እያስተማሩ መሆኑ ሲነገር ተስተውሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የተማሪዎቹን ቅበላ አራዝሟል ወይስ አላራዘመም ? ተማሪዎቹን ተቀብሎ እያስተማረ ነው ወይስ አልተጀመረም ? ሲል ወልዲያ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል።
ዩኒቨርሲቲው በምላሹ፣ " አላራዘመም። ተማሪዎቹ እስኪገቡ ድረስ እንጠብቃለን። የመንገድ መዘጋጋቱ ስለሚታወቅ እንደ ሀገር በይፋ ባናራዝምም የቻሉ እየገቡ ነው ያልቻሉ ይገባሉ በፈለጉት ሰዓት " ብሏል።
" በውስጥ ኮሚዩኒኬት ስላደረግን ከተማሪው ከተለያዩ ቅርብ ቦታ (ለምሳሌ ደሴ) እየመጡ ስላሉ አላራዘምንም " ሲልም አክሏል።
ትምህርት ተጀምሯል ? ስንል ላቀረበነው ጥያቄ " ትምህርት አልተጀመረም " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረብንለት ወሎ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ፣ " ተማሪዎችን ተቀብለን እያስተማርን ነው። የኛ ተማሪዎች ገብተዋል። ሲኔር ተማሪዎች በሙሉ ግቢ ነው ያሉት " ብሏል።
" የአዲስ ገቢዎችን በተመለከተ ግን ትምህርት ሚኒስቴር አልመደበም ገና። እንደመደበ እንጠራለን። እኛ ምንም የምናራዝምበት ምክንያት የለም " ነው ያለው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የተማሪዎቹን ቅበላ ያራዘሙ ዩኒቨርሲቲዎችን በተመለከተ ምን እየተሰራ እንደሆነ ማብራሪያ እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።
ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉት ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር)፣ ' ዩኒቨርሲቲዎቹ የራሳቸው ስኬጁል አለ። እኛም የሰጠነው ስኬጁል አለ። ዩኒቨርሲቲዎቹ ይጠየቁ " ከማለት ውጪ ማብራሪያ ለመስጠት ተቆጥቧል።
#TikvahEthioiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" በአማራ ክልል ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ አራዝመዋል። ትምህርት ከፓለቲካ ነጻ መሆን አለበት " - የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት
በአማራ ክልል በ " ፋኖ " ታጣቂዎችና በመንግስት መካከል ከአንድ ዓመት በላይ ባስቆጠረው የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች የቅበላ ጊዜ ማራዘማቸው ይህም ደግሞ በተማሪዎች ላይ ጭንቀት መደቀኑ ተሰምቷል።
ዩኒቨርሲቲዎቹ የተማሪዎቻቸውን የቅበላ ጊዜ ማራዘማቸውን እንደተረዳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጸው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት ነው።
የህብረቱ ፕሬዚዳንት ሓየሎም ስዩም፣ " አራት ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ አራዝመዋል " ብሎ ተማሪዎች በጭንቀት ውስጥ በመሆናቸው ባለድርሻ አካላት ለጉዳዩ ትከረት እንዲሰጡ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።
በጸጥታው ችግር የተማሪዎቻቸውን የቅበላ ጊዜ ያራዘሙት፣ " ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ ፣ ደብረ ታቦር እና ኢንጅባራ ዩኒቨርሲቲዎች " መሆናቸውንም ተናግሯል።
" ወሎና ወልዲያ ዩኒቨርሲቲዎች አሁን መንገድ ስለተከፈተ ይቀበላሉ " ያለው የህብረቱ ፕሬዚዳንት ደባርቅ ዩኒቨርቲንም ቅበላውን ሳያራዝም እንዳልቀረ፣ " ሀፋ፣ ሀፋ " የሆነ ሀሳብ ላይ እንደሆነ አስረድቷ።
ህብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ " ትምህርት ከፓለቲካ ነጻ መሆን አለበት " ሲል አሳስቧል።
በአንጻሩ ወልዲያ እና ወሎ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ተቀብለው እያስተማሩ መሆኑ ሲነገር ተስተውሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የተማሪዎቹን ቅበላ አራዝሟል ወይስ አላራዘመም ? ተማሪዎቹን ተቀብሎ እያስተማረ ነው ወይስ አልተጀመረም ? ሲል ወልዲያ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል።
ዩኒቨርሲቲው በምላሹ፣ " አላራዘመም። ተማሪዎቹ እስኪገቡ ድረስ እንጠብቃለን። የመንገድ መዘጋጋቱ ስለሚታወቅ እንደ ሀገር በይፋ ባናራዝምም የቻሉ እየገቡ ነው ያልቻሉ ይገባሉ በፈለጉት ሰዓት " ብሏል።
" በውስጥ ኮሚዩኒኬት ስላደረግን ከተማሪው ከተለያዩ ቅርብ ቦታ (ለምሳሌ ደሴ) እየመጡ ስላሉ አላራዘምንም " ሲልም አክሏል።
ትምህርት ተጀምሯል ? ስንል ላቀረበነው ጥያቄ " ትምህርት አልተጀመረም " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረብንለት ወሎ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ፣ " ተማሪዎችን ተቀብለን እያስተማርን ነው። የኛ ተማሪዎች ገብተዋል። ሲኔር ተማሪዎች በሙሉ ግቢ ነው ያሉት " ብሏል።
" የአዲስ ገቢዎችን በተመለከተ ግን ትምህርት ሚኒስቴር አልመደበም ገና። እንደመደበ እንጠራለን። እኛ ምንም የምናራዝምበት ምክንያት የለም " ነው ያለው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የተማሪዎቹን ቅበላ ያራዘሙ ዩኒቨርሲቲዎችን በተመለከተ ምን እየተሰራ እንደሆነ ማብራሪያ እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።
ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉት ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር)፣ ' ዩኒቨርሲቲዎቹ የራሳቸው ስኬጁል አለ። እኛም የሰጠነው ስኬጁል አለ። ዩኒቨርሲቲዎቹ ይጠየቁ " ከማለት ውጪ ማብራሪያ ለመስጠት ተቆጥቧል።
#TikvahEthioiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በመሬት ናዳ የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ።
በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጉባ ቆርቻ እና ሻናን ዱንጎ ወረዳዎች ትላንት ማክሰኞ በጣለው ከባድ ዝናብ የተነሣ በተከሠተው የመሬት መናድ፣ 10 ሰዎች መሞታቸውን ወረዳዎቹ አሳውቀዋል።
የጉባ ቆርቻ ወረዳ አስተዳዳር ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል መስከረም 28 ቀን 2017 ዓ/ም በጃርጃታ ቀበሌ ውስጥ በተከሰተው የመሬት መናድ ምክንያት 4 ሰዎች ሲሞቱ በሌላ ቀበሌ በደረሰው አደጋ ደግሞ አንድ ሰው ሞቷል።
በሻናን ዱንጎ ወረዳ በሌሊስቱ ቀበሌ በዚሁ ቀን በተከሰተው ሌላ የመሬት መናድ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት ማለፉን የወረዳው አስተዳዳር ለሬድዮ ጣቢያው ገልጿል።
ነፍስ ይማር !
@tikvahethiopia
በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጉባ ቆርቻ እና ሻናን ዱንጎ ወረዳዎች ትላንት ማክሰኞ በጣለው ከባድ ዝናብ የተነሣ በተከሠተው የመሬት መናድ፣ 10 ሰዎች መሞታቸውን ወረዳዎቹ አሳውቀዋል።
የጉባ ቆርቻ ወረዳ አስተዳዳር ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል መስከረም 28 ቀን 2017 ዓ/ም በጃርጃታ ቀበሌ ውስጥ በተከሰተው የመሬት መናድ ምክንያት 4 ሰዎች ሲሞቱ በሌላ ቀበሌ በደረሰው አደጋ ደግሞ አንድ ሰው ሞቷል።
በሻናን ዱንጎ ወረዳ በሌሊስቱ ቀበሌ በዚሁ ቀን በተከሰተው ሌላ የመሬት መናድ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት ማለፉን የወረዳው አስተዳዳር ለሬድዮ ጣቢያው ገልጿል።
ነፍስ ይማር !
@tikvahethiopia
ስቴም ፖወር !
ኢትዮጵያ ለሚገኙ ወጣት ሴቶች ለ3ተኛ ዙር የቀረበ ጥሪ !
ስቴም ፖወር (STEMpower) ከፊንላንድ ኤምባሲ (Embassy of Finland Ethiopia) እና ከአይቢኤም (IBM) ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ከ1,000 በላይ ሥራ አጥ ወጣት ሴቶችን ተግባራዊ የሥራ ክህሎት ለመስጠት ያለመ " ትጋት " የተሰኘ ፕሮግራም አስተዋውቀዋል።
ባለፉት 2 ዙሮች 1700 በላይ ለሚሆኑ ሴቶች በ Project Management, Web Development , Cyber Security, Digital Marketing , Data Analytics , Information Technology , Job Readiness , Work Readiness ስልጠና የሰጠ ከመሆኑ በተጨማሪ የስራ እድል በመፈጠር ተጠቃሚ እንዲሆኑ እድል አመቻችቷል፡፡
#ነጻ በሚሰጠውና ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው ሰርተፊኬት በሚያስገኘው በዚህ ስልጠና እነዚህን ኮርሶች ለመውሰድ ፍላጎት ያላችሁ ሴቶች ምዝገባ የጀመርን መሆኑን እያሳወቅን ምዝገባው የሚቆየው ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 10 , 2017 ዓ/ም ሲሆን ቀድማችሁ በመመዝገብ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እንጋብዛለን፡፡
እነዚህን ኮርሶች ለመውሰድ ፍላጎት ያላችሁ ከስር ባለውን ሊንክ ይመዝገቡ
👉Link: https://forms.office.com/r/bJedLrdqmd
ኢትዮጵያ ለሚገኙ ወጣት ሴቶች ለ3ተኛ ዙር የቀረበ ጥሪ !
ስቴም ፖወር (STEMpower) ከፊንላንድ ኤምባሲ (Embassy of Finland Ethiopia) እና ከአይቢኤም (IBM) ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ከ1,000 በላይ ሥራ አጥ ወጣት ሴቶችን ተግባራዊ የሥራ ክህሎት ለመስጠት ያለመ " ትጋት " የተሰኘ ፕሮግራም አስተዋውቀዋል።
ባለፉት 2 ዙሮች 1700 በላይ ለሚሆኑ ሴቶች በ Project Management, Web Development , Cyber Security, Digital Marketing , Data Analytics , Information Technology , Job Readiness , Work Readiness ስልጠና የሰጠ ከመሆኑ በተጨማሪ የስራ እድል በመፈጠር ተጠቃሚ እንዲሆኑ እድል አመቻችቷል፡፡
#ነጻ በሚሰጠውና ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው ሰርተፊኬት በሚያስገኘው በዚህ ስልጠና እነዚህን ኮርሶች ለመውሰድ ፍላጎት ያላችሁ ሴቶች ምዝገባ የጀመርን መሆኑን እያሳወቅን ምዝገባው የሚቆየው ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 10 , 2017 ዓ/ም ሲሆን ቀድማችሁ በመመዝገብ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እንጋብዛለን፡፡
እነዚህን ኮርሶች ለመውሰድ ፍላጎት ያላችሁ ከስር ባለውን ሊንክ ይመዝገቡ
👉Link: https://forms.office.com/r/bJedLrdqmd
እሁድ ጥቅምት 3 ከሰዓት 9፡15 ብርቅዬ አትሌቶቻችንን በችካጎ ማራቶን ይሳተፋሉ!
መልካም ዕድል ለአትሌቶቻችን! 💚💛❤️
ይህንን ደማቅ ሩጫ በቀጥታ በSS Africa ቻናል 227 በቤተሰብ ፓኬጅ ይከታተሉ! ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/dg1
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
መልካም ዕድል ለአትሌቶቻችን! 💚💛❤️
ይህንን ደማቅ ሩጫ በቀጥታ በSS Africa ቻናል 227 በቤተሰብ ፓኬጅ ይከታተሉ! ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/dg1
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
መቐለ ? የመቐለ ከተማ ም/ቤት ዛሬ አካሂዶታል በተባለ ሰብሰባ ፥ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመራው ህወሓት ውስጥ የስራ አስፈፃሚ አባል ሆነው የተመረጡትን ዶ/ር ረዳኢ በርሀ የከተማዋ ከንቲባ ሆኖው እንዲያገለግሉ በ1 የተቃውሞ በ5 ድምፀ ተአቅቦ እንደመረጣቸው ተሰምቷል። የከተማዋ ም/ቤት ከተማዋ በከንቲባነት ሲመሩ የቆዩት በዶ/ር ደብረፅዮን በሚመራው ህወሓት የማእከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑትን አቶ…
" መንግስትን በሃይል ለመፈንቀል የሚደረግ ሙከራ የሚወገዝና ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን ይፋ አደርገናል " - አቶ ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ መስከረም 29/2017 ዓ.ም ከቢቢሲ FOCUS ON AFRICA ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።
በዚህም ወቅት ፤ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት በውይይት የሚፈታበት መንገድ ዝግ እንዳልሆነ አመላክተዋል።
" ሆኖም በጊዚያዊ አስተዳደሩ ላይ እየተደረጉ ያሉ ህጋዊ ያልሆኑ ተግባራት / መንግስትን በኃል ለመፈቀል የሚደረግ ሙኩራ የሚወገዙና ተጠያቂነት የሚስከትሉ መሆናቸው ህዝብ እንዲያውቃቸው ማድረጋችን ልክ ነው " ብለዋል።
" ሂደቱን ተከትሎ የተጠያቂነት አስራር ተግባራዊ እንደሚሆን ሁሉም ሊያውቀው የሚገባ ጉዳይ ነው " ሲሉ አክለዋል።
የትግራይ ህዝብ ችግሮች በተባባሱበት ወቅት ለምን አንድነታችሁ መጠበቅ አቃታችሁ ? የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ጌታቸው " ይህ ትልቅ ወድቀት ነው ፤ እንደ ድርጅት እና ስራ አስፈፃሚ አባል የሆንኩበት ህወሓት ወድቀዋል ፤ ቢሆንም ጥቂት አመራሮች መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት በመረዳት ለመፍታት ስንሞክር ቀላል የማይባል ፈተና እና እንቅፋት እየገጠመን ይገኛል " ብለዋል።
ከዚህ በመመለስ ግን ፈተናውን ለማለፍ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ መስከረም 29/2017 ዓ.ም ከቢቢሲ FOCUS ON AFRICA ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።
በዚህም ወቅት ፤ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት በውይይት የሚፈታበት መንገድ ዝግ እንዳልሆነ አመላክተዋል።
" ሆኖም በጊዚያዊ አስተዳደሩ ላይ እየተደረጉ ያሉ ህጋዊ ያልሆኑ ተግባራት / መንግስትን በኃል ለመፈቀል የሚደረግ ሙኩራ የሚወገዙና ተጠያቂነት የሚስከትሉ መሆናቸው ህዝብ እንዲያውቃቸው ማድረጋችን ልክ ነው " ብለዋል።
" ሂደቱን ተከትሎ የተጠያቂነት አስራር ተግባራዊ እንደሚሆን ሁሉም ሊያውቀው የሚገባ ጉዳይ ነው " ሲሉ አክለዋል።
የትግራይ ህዝብ ችግሮች በተባባሱበት ወቅት ለምን አንድነታችሁ መጠበቅ አቃታችሁ ? የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ጌታቸው " ይህ ትልቅ ወድቀት ነው ፤ እንደ ድርጅት እና ስራ አስፈፃሚ አባል የሆንኩበት ህወሓት ወድቀዋል ፤ ቢሆንም ጥቂት አመራሮች መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት በመረዳት ለመፍታት ስንሞክር ቀላል የማይባል ፈተና እና እንቅፋት እየገጠመን ይገኛል " ብለዋል።
ከዚህ በመመለስ ግን ፈተናውን ለማለፍ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#MoE
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በ 'Remedial' ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ ሞልተው እንዲጨርሱ መገለጹ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ " አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በሲስተም ችግር ምክንያት የተማሪዎቻችንን የትምህርት መስክ እና የዩኒቨርስቲ ምርጫ መሙላት ተቸግረናል " ባሉት መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር የምርጫ መሙያ ጊዜውን እስከ ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
@tikvahethiopia
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በ 'Remedial' ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ ሞልተው እንዲጨርሱ መገለጹ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ " አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በሲስተም ችግር ምክንያት የተማሪዎቻችንን የትምህርት መስክ እና የዩኒቨርስቲ ምርጫ መሙላት ተቸግረናል " ባሉት መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር የምርጫ መሙያ ጊዜውን እስከ ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
@tikvahethiopia
#WorldMentalHealthDay
"ሥራ የመስራት እድሜ ላይ ከደረሱ ስድስት አዋቂዎች አንዱ የአዕምሮ ጤና ችግር ያጋጥማቸዋል" - ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም
የ2024 #የዓለም_የአእምሮ_ጤና_ቀን በዛሬው እለት እየተከበረ ይገኛል። የዘንድሮው ቀን "የአእምሮ ጤና በስራ ቦታ ላይ" በሚል መሪ ሀሳብ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል።
ከአለም ህዝብ 60 በመቶ የሚሆኑ ሰዎች በስራ አለም ላይ እንደሆኑ የአለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል።
በስራ ላይ ካሉት ሰራተኞች ውስጥም ግማሽ የሚሆኑት የአእምሮ ጤና ችግር እንደሚያጋጥማቸው የአለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በዛሬው እለት የዓለም የአእምሮ ጤና ቀንን አስመልክተው ባስተላለፉት መልእክት ተናግረዋል።
የስራ አለም ላይ ያሉ ሰራተኞች በሚገጥማቸው የአእምሮ ጤና ችግርም በየአመቱ 1 ትሪሊዮን ዶላር እንደሚጠፋ ዶ/ር ቴድሮስ ጠቅሰዋል።
ሰራተኞችን ለአእምሮ ጤና ችግር የሚዳርገው ምንድነው?
- ዝቅተኛ የስራ ክህሎት፣ ችሎታ እና አፈፃፀም
- ከመጠን በላይ የሆነ የሥራ ጫና፤ የሰራተኞች እጥረት፤ አድልዎ፣ መገለል፣ ጥቃትና ትንኮሳ
- ረጅም፣ ያልተገደቡ እና ተለዋዋጭ የስራ ሰዓቶች
- አሉታዊ ድርጊቶችን የሚደግፍ ድርጅታዊ ባህል
- ከሥራ ባልደረቦች በቂ ድጋፍ አለማግኘት
- በቂ ያልሆነ ክፍያ፣ የሚጋጩ የሥራ ፍላጎቶች የአእምሮ ጤና እንደሚያስከትሉ የአለም ጤና ድርጅት ገልጿል።
ዶ/ር ቴድሮስ ስራ የመስራት እድሜ ላይ ከደረሱ ስድስት አዋቂዎች አንዱ የአእምሮ ጤና ችግር እንደሚያጋጥመው የገለፁ ሲሆን የአእምሮ ጤናን ለመጠበቅ የሚደረገው ኢንቨስትመንት አነስተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።
ችግሩን ለመከላከል ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ምን መደረግ አለበት አሉ ?
° አሰሪዎች የአእምሮ ጤና ችግር የሚያስከትሉ ችግሮችን በመለየት ምቹ የስራ ከባቢን መፍጠር እንደሚገባቸው፤
° የድርጅት ኃላፊዎች ጭንቀት ያጋጠማቸውን ሰራተኞች እንዲለዩ፣ የስራ ቦታ ላይ የሚያጋጥም የአእምሮ ጤና ችግርን እንዲቀርፉ መስራት እንደሚገባቸው፤
° የስራ ከባቢን ለሰራተኞች ምቹ እንዲሆን ማድረግ፤ አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉም ሰራተኞች በንቃት እንዲሰሩ የሚያስችል የስራ ከባቢ መፍጠር እንደሚገባ ዶ/ር ቴድሮስ ባስተላለፉት መልእክት ተናግረዋል።
ሰራተኞች የአእምሮ ጤና ችግር በሚገጥማቸው ጊዜም ሰዎችን ማውራት፣ ባለሙያ ማማከር ወይም እራሳቸውን ማረጋጋት እንደሚኖርባቸው ዶ/ር ቴድሮስ ገልፀዋል።
Via @tikvahethmagazine
"ሥራ የመስራት እድሜ ላይ ከደረሱ ስድስት አዋቂዎች አንዱ የአዕምሮ ጤና ችግር ያጋጥማቸዋል" - ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም
የ2024 #የዓለም_የአእምሮ_ጤና_ቀን በዛሬው እለት እየተከበረ ይገኛል። የዘንድሮው ቀን "የአእምሮ ጤና በስራ ቦታ ላይ" በሚል መሪ ሀሳብ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል።
ከአለም ህዝብ 60 በመቶ የሚሆኑ ሰዎች በስራ አለም ላይ እንደሆኑ የአለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል።
በስራ ላይ ካሉት ሰራተኞች ውስጥም ግማሽ የሚሆኑት የአእምሮ ጤና ችግር እንደሚያጋጥማቸው የአለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በዛሬው እለት የዓለም የአእምሮ ጤና ቀንን አስመልክተው ባስተላለፉት መልእክት ተናግረዋል።
የስራ አለም ላይ ያሉ ሰራተኞች በሚገጥማቸው የአእምሮ ጤና ችግርም በየአመቱ 1 ትሪሊዮን ዶላር እንደሚጠፋ ዶ/ር ቴድሮስ ጠቅሰዋል።
ሰራተኞችን ለአእምሮ ጤና ችግር የሚዳርገው ምንድነው?
- ዝቅተኛ የስራ ክህሎት፣ ችሎታ እና አፈፃፀም
- ከመጠን በላይ የሆነ የሥራ ጫና፤ የሰራተኞች እጥረት፤ አድልዎ፣ መገለል፣ ጥቃትና ትንኮሳ
- ረጅም፣ ያልተገደቡ እና ተለዋዋጭ የስራ ሰዓቶች
- አሉታዊ ድርጊቶችን የሚደግፍ ድርጅታዊ ባህል
- ከሥራ ባልደረቦች በቂ ድጋፍ አለማግኘት
- በቂ ያልሆነ ክፍያ፣ የሚጋጩ የሥራ ፍላጎቶች የአእምሮ ጤና እንደሚያስከትሉ የአለም ጤና ድርጅት ገልጿል።
ዶ/ር ቴድሮስ ስራ የመስራት እድሜ ላይ ከደረሱ ስድስት አዋቂዎች አንዱ የአእምሮ ጤና ችግር እንደሚያጋጥመው የገለፁ ሲሆን የአእምሮ ጤናን ለመጠበቅ የሚደረገው ኢንቨስትመንት አነስተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።
ችግሩን ለመከላከል ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ምን መደረግ አለበት አሉ ?
° አሰሪዎች የአእምሮ ጤና ችግር የሚያስከትሉ ችግሮችን በመለየት ምቹ የስራ ከባቢን መፍጠር እንደሚገባቸው፤
° የድርጅት ኃላፊዎች ጭንቀት ያጋጠማቸውን ሰራተኞች እንዲለዩ፣ የስራ ቦታ ላይ የሚያጋጥም የአእምሮ ጤና ችግርን እንዲቀርፉ መስራት እንደሚገባቸው፤
° የስራ ከባቢን ለሰራተኞች ምቹ እንዲሆን ማድረግ፤ አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉም ሰራተኞች በንቃት እንዲሰሩ የሚያስችል የስራ ከባቢ መፍጠር እንደሚገባ ዶ/ር ቴድሮስ ባስተላለፉት መልእክት ተናግረዋል።
ሰራተኞች የአእምሮ ጤና ችግር በሚገጥማቸው ጊዜም ሰዎችን ማውራት፣ ባለሙያ ማማከር ወይም እራሳቸውን ማረጋጋት እንደሚኖርባቸው ዶ/ር ቴድሮስ ገልፀዋል።
Via @tikvahethmagazine
#ሪልስቴት
ያልተገነባ ቤት / ግንባታ ከማከናወናቸው በፊት ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ አካውንት እንዲያስቀምጡ ሊገደዱ ነው ፤ በተጨማሪ ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ሊከለከሉ ነው።
ይህንም የሚመለከት ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ቀርቧል።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ምን ይላል ?
ቤት ለመገንባት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ያላገኙ የሪል ስቴት አልሚዎች ደንበኞችን #እንዳይመዘግቡ እና #ቅድመ_ክፍያ እንዳይሰበስቡ ይከለክላል።
በአሁኑ ጊዜ ባለው አሠራር መሠረት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ብቻ ወደ ሪል ስቴት ገበያው ሲቀላቀሉ የነበሩት አልሚዎች፤ በአዲሱ ረቂቅ አዋጅ " የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ " የማውጣት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሀብት ሪል ስቴት አልሚዎች ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ቢያንስ 50 ቤቶችን ገንብተው የሚያስከረክቡ መሆን አለባቸው።
የአገር ውስጥ እና የውጭ አልሚዎች ግንባታውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን " የፋይናንስ አቅርቦት ምንጭ " የማቅረብ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦባቸዋል። ይሁንና ረቂቁ፤ " የቅድሚያ ቤት ሽያጭ ተጠቃሚነት " መብትን ከቅድመ ሁኔታ ጋር ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ሰጥቷል።
ይህ አሠራር የሪል ስቴት አልሚዎች የቤት ግንባታውን ሳያከናውኑ ወይም በሂደት ላይ እያለ ለግንባታው የሚውልን ፋይናንስ የሚያሰባስቡበት እና ገንዘቡብ ለግንባታው የሚያውሉበት መንገድ ነው።
የቤት ግንባታው ሳይከናወን በፊት ከገዢዎች ጋር ውል ማሰር እና ክፍያ መፈጸም ኢትዮጵያ ውስጥ በሪል ስቴት ልማት ላይ በተሰማሩ አልሚዎች በኩል የተለመደ አሰራር ነው።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ፤ በዚህ ዓይነት መልኩ ለግንባታ የሚውለውን ሀብት ማሰባሰብ የሚፈልጉ አልሚዎች " አግባብ ካለዉ አካል ፈቃድ ማቅረብ " ይጠበቅባቸዋል። ይህም ግዴታ ነው።
የቅድመ ሽያጭ ዘዴን መጠቀም የሚፈልጉት ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡት ገንዘብ የሚቀመጥበት የባንክ ሂሳብ እና የገንዘብ አወጣጥ ላይም አስገዳጅ አሠራር በረቂቅ አዋጁ ተጥሎባቸዋል።
አልሚዎቹ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ " የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ " እንዳለባቸው ረቂቅ ሕጉ ላይ ሰፍሯል።
አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው " አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት " እንደሆነም ያስረዳል።
በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ ይወሠናል።
ከዚህም ባሻገር በቅድሚያ የተሸጠው ቤት ተገንብቶ ለተጠቃሚዎች እስከሚተላለፍ ድረስ የቤት የመሥሪያ ቦታው የይዞታ ማስረጃ " በሚመለከተው አካል እንዳይሸጥ፣ እንዳይለወጥ " እንደሚታገድ ረቂቁ ይገልጻል።
ቤት ቀድመው በሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ እነዚህ አስገዳጅ አሠራሮች የተቀመጡት " ደንበኞች የሚደርስባቸውን እንግልት እና ኪሳራ ለመቀነስ በማሰብ " እንደሆነ የአዋጁ ማብራሪያ ያስረዳል።
ረቂቅ አዋጁ በሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ሌሎችንም ግዴታዎች ጥሏል።
በረቂቁ መሠረት፤ የሪል ስቴት አልሚዎች ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ተከልክለዋል።
" ያለደንበኛው ፍላጎት እና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ አይችልም " ይህንን ለማድረግ በቅድሚያ ደንበኛው መስማማት እንዳለበት ያመለክታል።
ሪል ስቴት አልሚዎች ቤት ገዢዎችን መመመዝገብ እና ቅድመ ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉበት ጊዜም ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦበታል።
አልሚዎች ምዝገባ ማድረግ እና ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉት " የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከተረከቡ " በኋላ ነው።
" በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም " የሚለውም ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ከተቀመጡት ግዴታዎች መካከል ነው።
ለሪል ስቴት ልማት አሠራር የሚዘረጋው አዲሱ አዋጅ፤ ከግዴታዎች ባሻገር አልሚዎች ከመንግሥት " መሬት በስፋት " ማግኘት የሚችሉበትን ሂደትም ያስቀመጠ ነው።
ከመንግሥት መሬት " በስፋት " የሚቀርብላቸው አልሚዎች ረቂቁ ላይ ከተጠቀሱ ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ ቢያንስ አንዱን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
ከእነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል በብዛት ቤቶችን መገንባት እና ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ " 40 በመቶውን ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ " ማድረግ የሚለው አንዱ ነው።
ይህንን ቅድመ ሁኔታ የሚከተሉ አልሚዎች የሚገነቡበት ቤት ብዛት " እንደ ከተሞች ደረጃ በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 5 ሺህ " ሊሆን እንደሚችል በረቂቁ ላይ ተጠቅሷል።
መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ መሬት " በስፋት " የሚያቀርበው " በአዲስ አበባ ከ5 ሺ በላይ ቤት ለሚገነባ እና ለሚያስተላልፍ " አልሚ እንደሆነ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።
በሌሎች ከተሞች መሬት " በስፋት " የሚቀርበው እደሚኖራቸው " ተጨባጭ የቤት ፍላጎት " ሲሆን፣ " ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባሉ ከተሞች " ደግሞ ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶችን ለሚገነቡ አልሚዎች እንደሚቀርብላቸው ረቂቁ ያስረዳል።
ከመንግሥት መሬት " በስፋት " ማግኘት የሚፈልጉ አልሚዎች የተቀመጠባቸው ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ከውጭ ምንዛሬ ጋር የተገናኙ ናቸው።
በአገር ውስጥ " በጥራት እና በብዛት የማይገኙ " ግብአቶችን በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (ፍራንኮ ቫሉታ) የሚያስገቡ እንዲሁም የሚያገኙትን ትርፍ እስከ አስር ዓመት ከአገር ሳያወጡ አገር ውስጥ መልሰው የሚጠቀሙ አልሚዎች የዚህ አሠራር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።
" የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይት እና ግመታ " የተሰኘው ይህ ረቂቅ አዋጅ የቀረበለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተጨማሪ ዕይታ ወደ ከተማ፣ መሠረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ መርቶታል።
መረጃው ከቢቢሲ አማርኛ የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
ያልተገነባ ቤት / ግንባታ ከማከናወናቸው በፊት ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ አካውንት እንዲያስቀምጡ ሊገደዱ ነው ፤ በተጨማሪ ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ሊከለከሉ ነው።
ይህንም የሚመለከት ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ቀርቧል።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ምን ይላል ?
ቤት ለመገንባት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ያላገኙ የሪል ስቴት አልሚዎች ደንበኞችን #እንዳይመዘግቡ እና #ቅድመ_ክፍያ እንዳይሰበስቡ ይከለክላል።
በአሁኑ ጊዜ ባለው አሠራር መሠረት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ብቻ ወደ ሪል ስቴት ገበያው ሲቀላቀሉ የነበሩት አልሚዎች፤ በአዲሱ ረቂቅ አዋጅ " የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ " የማውጣት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሀብት ሪል ስቴት አልሚዎች ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ቢያንስ 50 ቤቶችን ገንብተው የሚያስከረክቡ መሆን አለባቸው።
የአገር ውስጥ እና የውጭ አልሚዎች ግንባታውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን " የፋይናንስ አቅርቦት ምንጭ " የማቅረብ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦባቸዋል። ይሁንና ረቂቁ፤ " የቅድሚያ ቤት ሽያጭ ተጠቃሚነት " መብትን ከቅድመ ሁኔታ ጋር ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ሰጥቷል።
ይህ አሠራር የሪል ስቴት አልሚዎች የቤት ግንባታውን ሳያከናውኑ ወይም በሂደት ላይ እያለ ለግንባታው የሚውልን ፋይናንስ የሚያሰባስቡበት እና ገንዘቡብ ለግንባታው የሚያውሉበት መንገድ ነው።
የቤት ግንባታው ሳይከናወን በፊት ከገዢዎች ጋር ውል ማሰር እና ክፍያ መፈጸም ኢትዮጵያ ውስጥ በሪል ስቴት ልማት ላይ በተሰማሩ አልሚዎች በኩል የተለመደ አሰራር ነው።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ፤ በዚህ ዓይነት መልኩ ለግንባታ የሚውለውን ሀብት ማሰባሰብ የሚፈልጉ አልሚዎች " አግባብ ካለዉ አካል ፈቃድ ማቅረብ " ይጠበቅባቸዋል። ይህም ግዴታ ነው።
የቅድመ ሽያጭ ዘዴን መጠቀም የሚፈልጉት ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡት ገንዘብ የሚቀመጥበት የባንክ ሂሳብ እና የገንዘብ አወጣጥ ላይም አስገዳጅ አሠራር በረቂቅ አዋጁ ተጥሎባቸዋል።
አልሚዎቹ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ " የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ " እንዳለባቸው ረቂቅ ሕጉ ላይ ሰፍሯል።
አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው " አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት " እንደሆነም ያስረዳል።
በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ ይወሠናል።
ከዚህም ባሻገር በቅድሚያ የተሸጠው ቤት ተገንብቶ ለተጠቃሚዎች እስከሚተላለፍ ድረስ የቤት የመሥሪያ ቦታው የይዞታ ማስረጃ " በሚመለከተው አካል እንዳይሸጥ፣ እንዳይለወጥ " እንደሚታገድ ረቂቁ ይገልጻል።
ቤት ቀድመው በሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ እነዚህ አስገዳጅ አሠራሮች የተቀመጡት " ደንበኞች የሚደርስባቸውን እንግልት እና ኪሳራ ለመቀነስ በማሰብ " እንደሆነ የአዋጁ ማብራሪያ ያስረዳል።
ረቂቅ አዋጁ በሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ሌሎችንም ግዴታዎች ጥሏል።
በረቂቁ መሠረት፤ የሪል ስቴት አልሚዎች ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ተከልክለዋል።
" ያለደንበኛው ፍላጎት እና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ አይችልም " ይህንን ለማድረግ በቅድሚያ ደንበኛው መስማማት እንዳለበት ያመለክታል።
ሪል ስቴት አልሚዎች ቤት ገዢዎችን መመመዝገብ እና ቅድመ ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉበት ጊዜም ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦበታል።
አልሚዎች ምዝገባ ማድረግ እና ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉት " የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከተረከቡ " በኋላ ነው።
" በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም " የሚለውም ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ከተቀመጡት ግዴታዎች መካከል ነው።
ለሪል ስቴት ልማት አሠራር የሚዘረጋው አዲሱ አዋጅ፤ ከግዴታዎች ባሻገር አልሚዎች ከመንግሥት " መሬት በስፋት " ማግኘት የሚችሉበትን ሂደትም ያስቀመጠ ነው።
ከመንግሥት መሬት " በስፋት " የሚቀርብላቸው አልሚዎች ረቂቁ ላይ ከተጠቀሱ ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ ቢያንስ አንዱን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
ከእነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል በብዛት ቤቶችን መገንባት እና ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ " 40 በመቶውን ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ " ማድረግ የሚለው አንዱ ነው።
ይህንን ቅድመ ሁኔታ የሚከተሉ አልሚዎች የሚገነቡበት ቤት ብዛት " እንደ ከተሞች ደረጃ በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 5 ሺህ " ሊሆን እንደሚችል በረቂቁ ላይ ተጠቅሷል።
መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ መሬት " በስፋት " የሚያቀርበው " በአዲስ አበባ ከ5 ሺ በላይ ቤት ለሚገነባ እና ለሚያስተላልፍ " አልሚ እንደሆነ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።
በሌሎች ከተሞች መሬት " በስፋት " የሚቀርበው እደሚኖራቸው " ተጨባጭ የቤት ፍላጎት " ሲሆን፣ " ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባሉ ከተሞች " ደግሞ ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶችን ለሚገነቡ አልሚዎች እንደሚቀርብላቸው ረቂቁ ያስረዳል።
ከመንግሥት መሬት " በስፋት " ማግኘት የሚፈልጉ አልሚዎች የተቀመጠባቸው ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ከውጭ ምንዛሬ ጋር የተገናኙ ናቸው።
በአገር ውስጥ " በጥራት እና በብዛት የማይገኙ " ግብአቶችን በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (ፍራንኮ ቫሉታ) የሚያስገቡ እንዲሁም የሚያገኙትን ትርፍ እስከ አስር ዓመት ከአገር ሳያወጡ አገር ውስጥ መልሰው የሚጠቀሙ አልሚዎች የዚህ አሠራር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።
" የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይት እና ግመታ " የተሰኘው ይህ ረቂቅ አዋጅ የቀረበለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተጨማሪ ዕይታ ወደ ከተማ፣ መሠረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ መርቶታል።
መረጃው ከቢቢሲ አማርኛ የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኢትዮጵያ
" በቀን ከ500 እስከ 600 ህሙማን ይስተናገዳሉ " - አማኑኤል ሆስፒታል
በየዓመቱ እ.ኤ.አ ኦክቶበር 10 የሚከበረው " የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀን " ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ " በሁሉም የሥራ ቦታ ቅድሚያ ለአዕምሮ ጤና ጊዜው አሁን ነው " በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ውሏል።
በኢትዮጵያ ጫፍ እስከ ጫፍ ያሉ የአዕምሮ ህሙማን ወገኖችን በማከም የሚታወቀው አማኑኤል ስፔላይዝድ የአዕምሮ ህሙማን ሆስፒታልም ህሙማኑን በስፓርታዊ ውድድሮች በማሳተፍ ጨምር በዓሉን አክብሮ መዋሉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
" የበዓሉ ዋነኛ ዓላማ በዓለም ዙሪያ በአዕምሮ ጤናና ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤን ለማሳደግና በአዕምሮ ጤና ክብካቤ ላይ የድጋፍ የሞብላይዜሽን ሥራዎችን ለማጠናከር ነው " ብሏል።
“በአዕምሮ ህሙማን የሚደረጉ መገለሎች አሉ። ሰብዓዊ መብታቸው ሲከበር አይታይም” ያለው ሆስፒታሉ፣ ማንም ሰው በህመሙ ላለመጠቃት ዋስትና የለውምና ህሙማኑን በሥራ ቦታ ጭምር ከማግለል እንዲቆጠብ አሳስቧል።
ይህን ያሉት የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አቢይ የኔዓለም፣ ሆስፒታሉ በቀን የሚታዩ የአዕምሮ ህሙማን ብዛት በተመለከተም ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
" በቁጥር ደረጃ በአማካኝ በቀን ከ500 እስከ 600 ህሙማን ይስተናገዳሉ። ቁጥሩ እንደ ሁኔታዎች ይጨምራም፣ ይቀንሳልም። ለምሳሌ አሁን ላይ የኦሮሚያና የአማራ ክልሎችን ብንወስድ አረመረጋጋቶች አሉ።
እነዚህ አለመረጋጋቶች ደግሞ ሰዎች ወደ ህክምና እንዳይደርሱ ያደርጓቸዋል። ስለዚህ በቅርብ አካባቢ ያሉት ናቸው ወደ ህክምና ሊመጡ የሚችሉት።
ስለዚህ በአማካኝ በቀን ከ500 እስከ 600 ህሙማን በተመላላሽ፣ በድንገተኛ በአስተኝቶ ይታያሉ " ነው ያሉት።
መንግስትና አጋር ድርጅቶች ትኩረት ሊሰጡባቸው የሚገቡ በሆስፒታሉ ያሉ ተግዳሮቶች ምንድን ናቸው ? ተብሎ ከቲክቫህ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፦
" ሆስፒታሉ የግንባት መሠረተ ልማት እጥረት አለበት። ጠባብ በሆነ ቦታ ነው ህክምና የሚሰጠው አስካሁን።
ያው በጤና ሚኒስቴርም በሆስፒታሉ አቅምም የተወሰኑ ጊዜያዊ እፎይታ ሊሰጡ የሚችሉ ውስጥ ላይ የሚሰሩ ማስፋፊያዎች አሉ። እነርሱም በቂ አይደሉም።
ስታንዳርዱን የጠበቀ ግንባታ ነው ሊኖር የሚገባው። ያም በጤና ሚኒስቴር ተይዞ ገና ሌላ ቦታ ላይ የግንባታ ሂደት እየተካሄደበት ያለበት ሁኔታ አለ።
ስለዚህ አንደኛው የመሠረተ ልማት ችግር ነው። ሌላው በስፔሻላይዜሽን ደረጃ በሥነ አዕምሮ ላይ ሰብስፔሻሊቲ ባለሙያዎችም እጥረት የሚታይበት ሁኔታ አለ።
ስለዚህ አጋር ድርጅቶችም መንግስትም ይህንን ትኩረት ሰጥተው በጋራ መረባረብ ቢቻል እንደ አገር የአዕምሮ ጤናን ተደራሽ ማድረግ ማጎልበትም ይቻላል " ሲሉ መልሰዋል።
በሆስፒታሉ ስንት የአዕምሮ ስፒሻሊስት ሀኪሞች አሉ ? ያስፈልጋል ተብሎ የሚታሰበው ምን ያክል ነው ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ ምላሻቸው፣ " ሰባት ስፔሻሊስቶች አሉ። ግን በሬሽዎ ሲሰራ ይሄ በቂ አይደለም። በጣም አናሳ ነው። ከዚያ በላይ ነው የሚጠበቀው " የሚል ነው።
" ለአዕምሮ ጤና ክብካቤ ወይም ደህንነት ዋናውና ወሳኙ ከባቢያችን ነው። መሪ ቃሉም በሁሉም የሥራ ቦታ ቅድሚያ ለአዕምሮ ጤና ግዜው አሁን ነው። ስለዚህ የሥራ ቦታን ደህነት፣ የሰራተኛውን ጤናማ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል " ሲሉ አስገንዝበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" በቀን ከ500 እስከ 600 ህሙማን ይስተናገዳሉ " - አማኑኤል ሆስፒታል
በየዓመቱ እ.ኤ.አ ኦክቶበር 10 የሚከበረው " የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀን " ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ " በሁሉም የሥራ ቦታ ቅድሚያ ለአዕምሮ ጤና ጊዜው አሁን ነው " በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ውሏል።
በኢትዮጵያ ጫፍ እስከ ጫፍ ያሉ የአዕምሮ ህሙማን ወገኖችን በማከም የሚታወቀው አማኑኤል ስፔላይዝድ የአዕምሮ ህሙማን ሆስፒታልም ህሙማኑን በስፓርታዊ ውድድሮች በማሳተፍ ጨምር በዓሉን አክብሮ መዋሉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
" የበዓሉ ዋነኛ ዓላማ በዓለም ዙሪያ በአዕምሮ ጤናና ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤን ለማሳደግና በአዕምሮ ጤና ክብካቤ ላይ የድጋፍ የሞብላይዜሽን ሥራዎችን ለማጠናከር ነው " ብሏል።
“በአዕምሮ ህሙማን የሚደረጉ መገለሎች አሉ። ሰብዓዊ መብታቸው ሲከበር አይታይም” ያለው ሆስፒታሉ፣ ማንም ሰው በህመሙ ላለመጠቃት ዋስትና የለውምና ህሙማኑን በሥራ ቦታ ጭምር ከማግለል እንዲቆጠብ አሳስቧል።
ይህን ያሉት የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አቢይ የኔዓለም፣ ሆስፒታሉ በቀን የሚታዩ የአዕምሮ ህሙማን ብዛት በተመለከተም ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
" በቁጥር ደረጃ በአማካኝ በቀን ከ500 እስከ 600 ህሙማን ይስተናገዳሉ። ቁጥሩ እንደ ሁኔታዎች ይጨምራም፣ ይቀንሳልም። ለምሳሌ አሁን ላይ የኦሮሚያና የአማራ ክልሎችን ብንወስድ አረመረጋጋቶች አሉ።
እነዚህ አለመረጋጋቶች ደግሞ ሰዎች ወደ ህክምና እንዳይደርሱ ያደርጓቸዋል። ስለዚህ በቅርብ አካባቢ ያሉት ናቸው ወደ ህክምና ሊመጡ የሚችሉት።
ስለዚህ በአማካኝ በቀን ከ500 እስከ 600 ህሙማን በተመላላሽ፣ በድንገተኛ በአስተኝቶ ይታያሉ " ነው ያሉት።
መንግስትና አጋር ድርጅቶች ትኩረት ሊሰጡባቸው የሚገቡ በሆስፒታሉ ያሉ ተግዳሮቶች ምንድን ናቸው ? ተብሎ ከቲክቫህ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፦
" ሆስፒታሉ የግንባት መሠረተ ልማት እጥረት አለበት። ጠባብ በሆነ ቦታ ነው ህክምና የሚሰጠው አስካሁን።
ያው በጤና ሚኒስቴርም በሆስፒታሉ አቅምም የተወሰኑ ጊዜያዊ እፎይታ ሊሰጡ የሚችሉ ውስጥ ላይ የሚሰሩ ማስፋፊያዎች አሉ። እነርሱም በቂ አይደሉም።
ስታንዳርዱን የጠበቀ ግንባታ ነው ሊኖር የሚገባው። ያም በጤና ሚኒስቴር ተይዞ ገና ሌላ ቦታ ላይ የግንባታ ሂደት እየተካሄደበት ያለበት ሁኔታ አለ።
ስለዚህ አንደኛው የመሠረተ ልማት ችግር ነው። ሌላው በስፔሻላይዜሽን ደረጃ በሥነ አዕምሮ ላይ ሰብስፔሻሊቲ ባለሙያዎችም እጥረት የሚታይበት ሁኔታ አለ።
ስለዚህ አጋር ድርጅቶችም መንግስትም ይህንን ትኩረት ሰጥተው በጋራ መረባረብ ቢቻል እንደ አገር የአዕምሮ ጤናን ተደራሽ ማድረግ ማጎልበትም ይቻላል " ሲሉ መልሰዋል።
በሆስፒታሉ ስንት የአዕምሮ ስፒሻሊስት ሀኪሞች አሉ ? ያስፈልጋል ተብሎ የሚታሰበው ምን ያክል ነው ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ ምላሻቸው፣ " ሰባት ስፔሻሊስቶች አሉ። ግን በሬሽዎ ሲሰራ ይሄ በቂ አይደለም። በጣም አናሳ ነው። ከዚያ በላይ ነው የሚጠበቀው " የሚል ነው።
" ለአዕምሮ ጤና ክብካቤ ወይም ደህንነት ዋናውና ወሳኙ ከባቢያችን ነው። መሪ ቃሉም በሁሉም የሥራ ቦታ ቅድሚያ ለአዕምሮ ጤና ግዜው አሁን ነው። ስለዚህ የሥራ ቦታን ደህነት፣ የሰራተኛውን ጤናማ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል " ሲሉ አስገንዝበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#Ethiotelecom
🎀 ተጨማሪ 10% ስጦታ ያግኙ!
ከውጭ አገራት ከ99 ብር ጀምሮ የሞባይል አየር ሰዓት ወይም ጥቅል በአጋሮቻችን በኩል ሲላክልዎ ለ30 ቀናት የሚያገለግል የ10% ተጨማሪ ስጦታ ያገኛሉ፡፡
🗓 እስከ ታኅሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም!
ደንብና ሁኔታዎችን https://bit.ly/487Y93d ይመልከቱ!
#telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
🎀 ተጨማሪ 10% ስጦታ ያግኙ!
ከውጭ አገራት ከ99 ብር ጀምሮ የሞባይል አየር ሰዓት ወይም ጥቅል በአጋሮቻችን በኩል ሲላክልዎ ለ30 ቀናት የሚያገለግል የ10% ተጨማሪ ስጦታ ያገኛሉ፡፡
🗓 እስከ ታኅሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም!
ደንብና ሁኔታዎችን https://bit.ly/487Y93d ይመልከቱ!
#telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia