TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ውጤት : የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዛሬ ይገለጻል።
የትምህርት ሚኒስቴር በውጤቱ ዙሪያ ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጥታ የሚያሰራጭ ይሆናል።
ይጠብቁ !
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የትምህርት ሚኒስቴር በውጤቱ ዙሪያ ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጥታ የሚያሰራጭ ይሆናል።
ይጠብቁ !
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
🙏2.05K😭704❤250🕊170👏124🥰93😡89😱85🤔79😢62
#AddisAbaba
" የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ? ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ? " - ፖለቲከኛ አቶ አበባ አካሉ
የኮሪደር ስራው ላይ የሚነሱት ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
የአዲስ አበባ ከተማን ገጽታ ይቀይራል የተባለው የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
አሁን ላይ ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ስራ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ ነው።
የአሁኑን ጨምሮ ከቀደመው (የተጠናቀቀው) ስራ ጋር በተያያዘ ግን ብዙ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት አንድ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር። በዚህም ወቅት የተለያዩ ጥያቄዎች ተጠይቀዋል። ከንቲባዋን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን ተጠየቀ ? ምንስ ተመለሰ ?
በውይይቱ ተሳታፊ ከነበሩት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
አቶ አበበ " የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ ይሄ የኮሪደር ልማትን አይቃወምም። እኛ የአሮጌ ከተማ ፍቅር የለብንም። ቡቱቶ የሆነ ከተማ ፍቅር የለብንም። urbanization እየሰፋ ነው የሚሄደው ፤ ከተሜነት እየሰፋ ሲሄድ የህዝብ ቁጥር ሲጨምር ከዓለም ጋር መዘመን አለብን። ምንም ጥርጥር የለውም። እኛም እኮ የምንዝናናበት ነው የተሰራው ኮሪደር። ነገር ግን የሚሰሩት ልማቶች የሚሰሩት ለሰው ነው ፤ ስለዚህ ምን ያክል ነው የተጠናው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
በተጨማሪ ለከንቲባዋ ፦
➡ ለመሆኑ ከኮሪደር ስራ ጋር ተያይዞ ለአዲስ አበባ ህዝብ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ የለም ? የአዲስ አበባ ህዝብ ኑሮ አያሳስበውም ? አሁን ያለበት የኑሮ ደረጃ አያሳስበውም ?
➡ የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ?
➡ ' እዬዬም እኮ ሲደላ ነው ' ለምን ኑሮው አይታይም የህዝቡ ?
➡ ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ?
➡ ፒያሳ ተነሳ ጥሩ ስራ ተሰርቷል በጣም ውብ ነው ደስ ይላል ፤ የተሰራው ውስጥም ነው ተቀምጠን የምንወያየው ግን በዚህ ፍጥነት አልተቻኮለም ?
➡ በየመንገዱ የሚሰሩ ፣ ጀብሎ የሆነው የሚቸረችሩ ወጣቶች የት ሄዱ ? ሁሉም ነገር ዝግ ተደርጎባቸዋል። ... ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?
" የኮሪደር ስራ ቅድሚያ ልንሰጠው ይገባል ወይ ? እንዲህ መቸኮልስ ለምን አስፈለገ ፤ በርካታ የከተማው ህዝብ ጥያቄዎች የሉም ወይ ? የሚለው መነሳቱ ጥሩ ነው።
የኮሪደር ልማት ስራ ሲሰራ ሌሎች ስራዎችና አገልግሎቶች ወደኃላ ተብለዋል ማለት አይደለም። አስማምተን ነው እየሰራን ያለነው።
በተናበበ መንገድ አቅደን ፤ ሌሊትም ቀንም ለመስራት ራሳችንን አሳምንነን ነው እየሰራን ያለነው። ስራም ተከፋፍለን ነው። ቢሮ ማገልገል ያለበት ቢሮ ነው። እኛም ሙሉ ጊዜያችን ኮሪደር ብቻ አይደለም። ኮሪደር እያስተባበርን ሌሎች ስራዎችም እንሰራለን።
የኑሮ ውድነት ተነስቷል ፤ ችግሩ ስለገባን ነው የአዲስ አበባ ህጻናት ባዶ ሰሃን ያለ ሃጢያታቸው ምግብ ሳይኖራቸው ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ተደርጎ ያለ እድሜያቸው እንዲዋሹ ያለ ጥፋታቸው ፤ ከመራባቸው በላይ ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ባዶ ሰሃን ይዘው ትምህርት ቤት የሚወደቁበትን ታሪክ አይደል እንዴ የቀየርነው ?
ለ800 ሺህ ተማሪዎች ዩኒፎርም እናቀርባለን፣ ደብተርና የትምህርት ቁሳቁስ እናቀርባለን ፤ ምግብ በቀን ሁለት ጊዜ ጥዋት ቁርስ ይበላሉ ምሳቸውን በልተው ወደቤት ይሄዳሉ ፤ ቤት ውስጥ ያለውን ገመና ስለምናውቅ ነው።
ትውልድ መገንባት አለበት ሀገራቸውን እየጠሉ እያማረሩ ማደግ ስለሌለባቸው። የአዲስ አበባ እናቶችን የኑሮ ጫና በሚገባ አይተነው ነው። ጓዳቸውን አይተን ነው።
ሁለተኛ በየቦታው ቦታ አመቻችተን ከ190 በላይ የእሁድ ገበያ የፈጠርነው ከስግብግብ ነጋዴዎች ነዋሪዎችን ለማስጣል የሰራነው የኑሮ ውድነቱ ስለሚገባን አይደለም ?
እነኛህ የአዲስ አበባ ከተማ የመግቢያ በሮች ላይ 5 ትልልቅ የገበያ ማዕከላት በቢሊዮን ልክ እንደ ኮሪደር ልማት በፍጥነት የገነባነው የኑሮ ውድነት ጫናው ስለሚገባን አይደለም ? ለምን አልተደረገም ከዚህ በፊት።
ገበሬው ቀጥታ አምጥቶ ምርት እንዲሸጥ ደላላው ከመሃል እንዲወጣ አላደረግንም እንዴ ?
አረጋውያን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ማግኘት አቅቷቸው አልተመለከትንም ፤ ' ተረጂነትን ታስፋፋላችሁ ' እየተባለን ስንተች ትችቱን ወደጎን ብለን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ የሚያገኙበትን 21 የምገባ ማዕከላት ገንብተን እየመገብን ነው።
ከመንግሥት በጀት ውጭ 30,000 ቤቶች ገንብተን በነጻ ድሆችን አንስተን ዝቅ ብለን ያስገባንበት የህግ ግዴት አለብን እንዴ ? 30,000 ከመንግሥት በጀት ውጭ ነው። ውሃ የሚያፈስባቸው ከመጸዳጃ ቤት ጋር የሚኖሩ አንስተን አስገብተናቸዋል።
የኮሪደር ስራ በሰራንበት 2016 ዓ/ም ላይ ብቻ 18,000 ከትንሽ ፕሮጀክቶች እስከ አድዋ ድረስ ሰርተን ለህዝባችን ክፍት አድርገናል። የት የት እንደሆኑ ዳታ እንሰጣለን ሂዱና እዩ።
አጠቃላይ የከተማው ችግር እና ያለንበት ጥልቅ ድህነት በ1 ፣ በ3 ፣ በ5 ዓመት ተስርቶ አያልቅም የዘመናትን ውዝፍ በአንድ ጊዜ አልጨረሳችሁም ከሆነ ትክክል አይደለም። ሊያልቅ አይችልም።
በአንድ በኩል እኚህን ቶሎ ቅረፉ በሌላ በኩል አትቸኩሉ አብሮ አይሄድም።
ኮሪደር ስራ በባለሞያዎች በደንብ ተጠንቶ ነው የተጀመረው። መነሻው መዋቅራዊ ፕላን ነው። ያጠናንባቸውን አካባቢዎች ዶክመንቱ ይፋዊ ስለሆነ ማየት ይቻላል። የፕላን ጥሰቱ ልክ የለውም።
በየሰፈሩ ያሉ የፍሳሽ መስመሮች የተዘጉ ናቸው፣ እሳት አደጋ ሲፈጠር እንኳን ገብተን ማጥፋት አቅቶናል። ይቃጠሉ ይለቁ ? ከቆሻሻ ጋር መኖር የኢትዮጵያውያን ክብር ይመጥናል ? ጠረኑን አይታችሁታል ? እንዲህ ባልናገር ጥሩ ነበር ግን እውነታው ይሄ ነው።
ሰው ፍሳሽ ከላይ እየወረደበት እንዲተኛ፣ እናቶች ቆጥ ላይ እንጀራ እንዲጋግሩ ፣ እናቶች ከስር ልጆቻቸውንና የልጅ ልጆቻቸውን ይዘው ያድራሉ ከላይ ቆጥ ሰርተው ያከራያሉ። እነዚህ አካባቢዎች ታሪካቸው ይኸው ነው።
ቤቶቹ አርጅተዋል። በጭቃና በእንጨት ነው የተሰሩት አረጁ ግዜያቸው አለፈ ወደቁ በቆርቆሮ ቢለበዱ፣ ላስቲክ ቢታሰርባቸው ችግር መከላከል አይችሉም።
ወቀሳ የምታነሱ ሰዎች ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ በሴት እህቶቻችን እና እናቶች ላይ የሚፈጸመው ወንጀል ለምን አያማችሁም ? ወይስ አታውቁም ? የዜግነት ክብራችንን አይመጥንም ነበር። ስለዚህ ክብራችንን በሚመጥን መንገድ ማልማት ይገባል።
ወደው አልነበረም ከቆሻሻ ጋር ሲኖሩ የነበሩት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ አልፈው መጥተው ያ እንዲቀጥል የሚቀርበው ጥያቄ ፍጹም ተቀባይነት የለውም።
- ገቢያችን እንዲያድግ
- የስራ እድል በስፋት እንዲፈጠር
- ዜጎች ንጹህ ፅዱ ቦታ እንዲገበያዩ፣ እንዲሰሩ ፣ እንዲኖሩ ለማስቻለው ስራዎችን እየሰራን ያለነው።
የምንቸኩለው ጊዜ ስለሌለን ነው። ጉስቁልና ድህነት ውስጥ ነው ያለነው። ውርደት አለ ከዚህ ውስጥ መውጣት አለብን። አንዳንዶች የኛ ኑሮ ሻል ስላለ የድሃው አይታየን ይሆናል ! ከዚህ በላይ እንቸኩላለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
" የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ? ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ? " - ፖለቲከኛ አቶ አበባ አካሉ
የኮሪደር ስራው ላይ የሚነሱት ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
የአዲስ አበባ ከተማን ገጽታ ይቀይራል የተባለው የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
አሁን ላይ ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ስራ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ ነው።
የአሁኑን ጨምሮ ከቀደመው (የተጠናቀቀው) ስራ ጋር በተያያዘ ግን ብዙ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት አንድ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር። በዚህም ወቅት የተለያዩ ጥያቄዎች ተጠይቀዋል። ከንቲባዋን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን ተጠየቀ ? ምንስ ተመለሰ ?
በውይይቱ ተሳታፊ ከነበሩት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
አቶ አበበ " የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ ይሄ የኮሪደር ልማትን አይቃወምም። እኛ የአሮጌ ከተማ ፍቅር የለብንም። ቡቱቶ የሆነ ከተማ ፍቅር የለብንም። urbanization እየሰፋ ነው የሚሄደው ፤ ከተሜነት እየሰፋ ሲሄድ የህዝብ ቁጥር ሲጨምር ከዓለም ጋር መዘመን አለብን። ምንም ጥርጥር የለውም። እኛም እኮ የምንዝናናበት ነው የተሰራው ኮሪደር። ነገር ግን የሚሰሩት ልማቶች የሚሰሩት ለሰው ነው ፤ ስለዚህ ምን ያክል ነው የተጠናው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
በተጨማሪ ለከንቲባዋ ፦
➡ ለመሆኑ ከኮሪደር ስራ ጋር ተያይዞ ለአዲስ አበባ ህዝብ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ የለም ? የአዲስ አበባ ህዝብ ኑሮ አያሳስበውም ? አሁን ያለበት የኑሮ ደረጃ አያሳስበውም ?
➡ የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ?
➡ ' እዬዬም እኮ ሲደላ ነው ' ለምን ኑሮው አይታይም የህዝቡ ?
➡ ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ?
➡ ፒያሳ ተነሳ ጥሩ ስራ ተሰርቷል በጣም ውብ ነው ደስ ይላል ፤ የተሰራው ውስጥም ነው ተቀምጠን የምንወያየው ግን በዚህ ፍጥነት አልተቻኮለም ?
➡ በየመንገዱ የሚሰሩ ፣ ጀብሎ የሆነው የሚቸረችሩ ወጣቶች የት ሄዱ ? ሁሉም ነገር ዝግ ተደርጎባቸዋል። ... ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?
" የኮሪደር ስራ ቅድሚያ ልንሰጠው ይገባል ወይ ? እንዲህ መቸኮልስ ለምን አስፈለገ ፤ በርካታ የከተማው ህዝብ ጥያቄዎች የሉም ወይ ? የሚለው መነሳቱ ጥሩ ነው።
የኮሪደር ልማት ስራ ሲሰራ ሌሎች ስራዎችና አገልግሎቶች ወደኃላ ተብለዋል ማለት አይደለም። አስማምተን ነው እየሰራን ያለነው።
በተናበበ መንገድ አቅደን ፤ ሌሊትም ቀንም ለመስራት ራሳችንን አሳምንነን ነው እየሰራን ያለነው። ስራም ተከፋፍለን ነው። ቢሮ ማገልገል ያለበት ቢሮ ነው። እኛም ሙሉ ጊዜያችን ኮሪደር ብቻ አይደለም። ኮሪደር እያስተባበርን ሌሎች ስራዎችም እንሰራለን።
የኑሮ ውድነት ተነስቷል ፤ ችግሩ ስለገባን ነው የአዲስ አበባ ህጻናት ባዶ ሰሃን ያለ ሃጢያታቸው ምግብ ሳይኖራቸው ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ተደርጎ ያለ እድሜያቸው እንዲዋሹ ያለ ጥፋታቸው ፤ ከመራባቸው በላይ ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ባዶ ሰሃን ይዘው ትምህርት ቤት የሚወደቁበትን ታሪክ አይደል እንዴ የቀየርነው ?
ለ800 ሺህ ተማሪዎች ዩኒፎርም እናቀርባለን፣ ደብተርና የትምህርት ቁሳቁስ እናቀርባለን ፤ ምግብ በቀን ሁለት ጊዜ ጥዋት ቁርስ ይበላሉ ምሳቸውን በልተው ወደቤት ይሄዳሉ ፤ ቤት ውስጥ ያለውን ገመና ስለምናውቅ ነው።
ትውልድ መገንባት አለበት ሀገራቸውን እየጠሉ እያማረሩ ማደግ ስለሌለባቸው። የአዲስ አበባ እናቶችን የኑሮ ጫና በሚገባ አይተነው ነው። ጓዳቸውን አይተን ነው።
ሁለተኛ በየቦታው ቦታ አመቻችተን ከ190 በላይ የእሁድ ገበያ የፈጠርነው ከስግብግብ ነጋዴዎች ነዋሪዎችን ለማስጣል የሰራነው የኑሮ ውድነቱ ስለሚገባን አይደለም ?
እነኛህ የአዲስ አበባ ከተማ የመግቢያ በሮች ላይ 5 ትልልቅ የገበያ ማዕከላት በቢሊዮን ልክ እንደ ኮሪደር ልማት በፍጥነት የገነባነው የኑሮ ውድነት ጫናው ስለሚገባን አይደለም ? ለምን አልተደረገም ከዚህ በፊት።
ገበሬው ቀጥታ አምጥቶ ምርት እንዲሸጥ ደላላው ከመሃል እንዲወጣ አላደረግንም እንዴ ?
አረጋውያን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ማግኘት አቅቷቸው አልተመለከትንም ፤ ' ተረጂነትን ታስፋፋላችሁ ' እየተባለን ስንተች ትችቱን ወደጎን ብለን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ የሚያገኙበትን 21 የምገባ ማዕከላት ገንብተን እየመገብን ነው።
ከመንግሥት በጀት ውጭ 30,000 ቤቶች ገንብተን በነጻ ድሆችን አንስተን ዝቅ ብለን ያስገባንበት የህግ ግዴት አለብን እንዴ ? 30,000 ከመንግሥት በጀት ውጭ ነው። ውሃ የሚያፈስባቸው ከመጸዳጃ ቤት ጋር የሚኖሩ አንስተን አስገብተናቸዋል።
የኮሪደር ስራ በሰራንበት 2016 ዓ/ም ላይ ብቻ 18,000 ከትንሽ ፕሮጀክቶች እስከ አድዋ ድረስ ሰርተን ለህዝባችን ክፍት አድርገናል። የት የት እንደሆኑ ዳታ እንሰጣለን ሂዱና እዩ።
አጠቃላይ የከተማው ችግር እና ያለንበት ጥልቅ ድህነት በ1 ፣ በ3 ፣ በ5 ዓመት ተስርቶ አያልቅም የዘመናትን ውዝፍ በአንድ ጊዜ አልጨረሳችሁም ከሆነ ትክክል አይደለም። ሊያልቅ አይችልም።
በአንድ በኩል እኚህን ቶሎ ቅረፉ በሌላ በኩል አትቸኩሉ አብሮ አይሄድም።
ኮሪደር ስራ በባለሞያዎች በደንብ ተጠንቶ ነው የተጀመረው። መነሻው መዋቅራዊ ፕላን ነው። ያጠናንባቸውን አካባቢዎች ዶክመንቱ ይፋዊ ስለሆነ ማየት ይቻላል። የፕላን ጥሰቱ ልክ የለውም።
በየሰፈሩ ያሉ የፍሳሽ መስመሮች የተዘጉ ናቸው፣ እሳት አደጋ ሲፈጠር እንኳን ገብተን ማጥፋት አቅቶናል። ይቃጠሉ ይለቁ ? ከቆሻሻ ጋር መኖር የኢትዮጵያውያን ክብር ይመጥናል ? ጠረኑን አይታችሁታል ? እንዲህ ባልናገር ጥሩ ነበር ግን እውነታው ይሄ ነው።
ሰው ፍሳሽ ከላይ እየወረደበት እንዲተኛ፣ እናቶች ቆጥ ላይ እንጀራ እንዲጋግሩ ፣ እናቶች ከስር ልጆቻቸውንና የልጅ ልጆቻቸውን ይዘው ያድራሉ ከላይ ቆጥ ሰርተው ያከራያሉ። እነዚህ አካባቢዎች ታሪካቸው ይኸው ነው።
ቤቶቹ አርጅተዋል። በጭቃና በእንጨት ነው የተሰሩት አረጁ ግዜያቸው አለፈ ወደቁ በቆርቆሮ ቢለበዱ፣ ላስቲክ ቢታሰርባቸው ችግር መከላከል አይችሉም።
ወቀሳ የምታነሱ ሰዎች ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ በሴት እህቶቻችን እና እናቶች ላይ የሚፈጸመው ወንጀል ለምን አያማችሁም ? ወይስ አታውቁም ? የዜግነት ክብራችንን አይመጥንም ነበር። ስለዚህ ክብራችንን በሚመጥን መንገድ ማልማት ይገባል።
ወደው አልነበረም ከቆሻሻ ጋር ሲኖሩ የነበሩት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ አልፈው መጥተው ያ እንዲቀጥል የሚቀርበው ጥያቄ ፍጹም ተቀባይነት የለውም።
- ገቢያችን እንዲያድግ
- የስራ እድል በስፋት እንዲፈጠር
- ዜጎች ንጹህ ፅዱ ቦታ እንዲገበያዩ፣ እንዲሰሩ ፣ እንዲኖሩ ለማስቻለው ስራዎችን እየሰራን ያለነው።
የምንቸኩለው ጊዜ ስለሌለን ነው። ጉስቁልና ድህነት ውስጥ ነው ያለነው። ውርደት አለ ከዚህ ውስጥ መውጣት አለብን። አንዳንዶች የኛ ኑሮ ሻል ስላለ የድሃው አይታየን ይሆናል ! ከዚህ በላይ እንቸኩላለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
❤1.25K😡485👏133😢69🙏49🤔46🕊29😭25😱7🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba #ኮንዶሚኒየም
🔵 " ከ97 ጀምሮ የቆጠቡ ሰዎች መቼ ነው የሚደርሳቸው ፤ መቼ ነው የሚኖሩበት ? ሳይኖሩበት ሊሞቱ ነው እኮ ! " - አቶ አበበ አካሉ
⚫ " የ97 ደግሞ የሚባል የለም። እኛ እስከምናውቀው ዘግተናል " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ከአዲስ አበባ የኮሪደር ስራ ጋር በተያየዘ በርካቶች በልማት ተነሺነት ከኖሩበት አካባቢ ተነስተው ወደ ተለያዩ ጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲገቡ እየተደረገ ነው።
ምንም እንኳን ተነሺዎቹ መግባታቸው ላይ ቅሬታ ባይፈጥርም ከ97 አንስቶ ሲቆጥቡ የኖሩ ነዋሪዎች መፍትሄ ሳያገኙ መቅረታቸው እና አሁን ላይ አስተዳደሩ ቤት የተሰጠ መሆኑ ቅሬታ አሳድሯል።
ከሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት በተካሄደ የኮሪደር ስራውን በሚመለከት የውይይት መድረክ ላይ ይኸው ቅሬታና ጥያቄ ተነስቷል።
ጥያቄውን ካነሱት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
" ሲቆጥቡ የኖሩ ሰዎች ጉዳይ ምን ደረሰ ? አሁን ማህበረሰቡ ምን ያማል ከተማ አስተዳደሩን ' እኛ በቆጠብነው ገንዘብ ነው የልማት ተናሺዎችን እያሰፈረ ያለው ' የሚል ሮሮ አለ።
ለዚህ ምንድነው ምላሻችሁ ?
ከ97 ጀምሮ የቆጠቡ ሰዎች መቼ ነው የሚደርሳቸው ፤ መቼ ነው የሚኖሩበት ሳይኖሩበት ሊሞቱ ነው እኮ ! " ሲሉ ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?
" የኮንዶሚኒየም ቤት እስኪ ከየት አምጥታችሁ ነው በዚህ ደረጃ ያላችሁ ኃላፊዎች ' በቆጡት ገንዘብ ነው የሚሰራው ' የምትሉት።
እነ ንግድ ባንክ ናቸው ብሩን የሚያቀርቡት እስቲ እንነጋገር ትንሽ ወደ መረጃው ጠጋ ብላችሁ ብናወራ ምናለበት።
ኮንዶሚኒየም በብድር ነው የሚሰራው። የከተማ አስተዳደሩ በጀቱን አስይዞ ነው የሚበደረው።
ለምንድነው የሚቆጥቡት ? ከተባለ ዕጣ የደረሳቸው ዕለት የሚከፍሉትን እንዳያጡ ነው። እንጂ ቤቱን መገንቢያ አይደለም። ልክ ቤቱ ሲገነባ ብሩን ይከፍሉታል።
ሁለተኛ እንዴት ነው እኛ ብቻችንን የምንጠየቅበት ? ቤት ባልተዘጋጀበት በሚሊዮኖች መዝግቦ ቆጥቡ ብሎ ኃላፊነት ወስዶ የሰራ አካል እያለ ለምንድነው እኛ የምንወቀሰው ?
ቤት ሳያዘጋጅ ዜጎችን ልክ እንደ ማታለያ በሚሊየን መዝግቦ የበተነ እያለ ለምንድነው እኛ የምንወቀሰው ?
የኮንዶሚኒየም ቤት አጠቃላይ አንድ ቦታ እጅብ ብሎ ስለተሰራ ብዙ ይመስላችኋል እንጂ እስካሁን እስካጠናቀቅነው ያለው 300,000 ነው። የተመዘገበው በሚሊዮን ነው። በየጊዜው ተስፋ ቆርጦ፣ ተጣርቶ ተጣርቶ እኛ የደረስንበት 600,000 ነው። አክተቭ ይቆጥብ የነበረው። ግን ቤት ማግኘት እንዳለባቸው እናምናለን። ቤት ማግኘት አለባቸው።
ካለቁት ኮንዶሚኒየሞች ብራቸው ተዘርፎ፣ ቀድሞ ተከፍሎ ያልተሰራ 80 ህንጻ ብር ተከፍሎበት ጥለው ሄደዋል። በብዙ ውጣውረድ ነው 139,000 ቤቶችን የጨረስነው። የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ብቻ።
አሁንም ቢሆን ግን የከተማችን ነዋሪዎች ቤት ማግኘት አለባቸው። ለዚህም በኮንዶሚኒየም ብቻ አይደለም እንደ ቀድሞ በሚፈለገው ደረጃ ብድር ማግኘት አልቻልንም ከባንክ። ኮንዶሚኒየም መጥፎ ስለሆነ አላቆምነውም።
ከተማ አስተዳደሩ ዕዳ እየከፈለ ነው። ንግድ ባንክ የሚያበድረው የባለሃብትን ገንዘብ ነው አይደል ? 56 ቢሊዮን የኮንዶሚኒየም ዕዳ ነው የተረከብነው ዋስትና የሚሰጠው ከተማ አስተዳደሩ ስለሆነ ክፈሉ ተባልን ተገደድን በለውጥ ዘመኑ 30 ቢሊዮን ከፍለናል የኮንዶሚኒየም ዕዳ።
ይህ ሁሉ ዕዳ አንደኛ በከፍተኛ ሰብሲዲ ስለሚሰራ ነው ፤ ሌላው ያልተሰሩ ቤቶች የተከፈለባቸው አሉ። ሳይከፍሉ ሲሸጡ በተለያየ መንገድ ሲተላለፉ የነበሩ ቤት ውስጥ ያገኘናቸው ሰዎች ከግለሰብ የገዙ ናቸው፤ ሊገደዱ አይችሉም የኮንዶሚኒየም ክፈሉ ተብለው። አጣርተን እኮ በሚዲያ ነግረናችኋል ፤ ያጋጠመንን።
አሁን በግልና በመንግሥት አጋርነት ወደ 100,000 ቤቶች አስጀምረናል። የቁጠባ ቤቶችንም እየሰራን እያከራየን ነው። በሪስልቴትም በግል የሚሰሩትን እንደ ከተማው ፕሮጀክት ጠጋ ብለን እያገዝን ቶሎ እንዲጨርሱ እያደረግን ነው።
እስካሁን የቆጠቡትን አሁን በግልና መንግሥት ትብብር ከምንሰራው ውስጥ ቅድሚያ ሊያገኙ የሚችሉበትን አግባብ እየተከተልን ነው። ሁለተኛ ደግሞ ተደራጅተው በማህበር እንዲሰሩ ...እስካሁን ለተደራጁት መሬት አስረክበናል።
መነገጃ አታድርጉት፤ ከእውነታው ውጭ መነጋጃ ማድረጉ አይጠቅምም።
የ97 ደግሞ የሚባል የለም። እኛ እስከምናውቀው ዘግተናል። ባለፈው ያስጨረስናቸውን ኮንዶሚኒየም ቤቶች ቅድሚያ 97 አክቲቭ ቆጣቢዎች ሁሉ ዕጣ እንዲወጣላቸው ተደርጓል።
እነሱ ከወጣላቸው በኃላ ዲአክቲቬት ያደረገውን አካውን አክቲቬት ያደረገ ካለ እሱ ስለቆጠበ ቤት ስለሚፈልግ ለሚቀጥለው ጊዜ ሊታይ ይገባል ፤ እንጂ በዚህ መንገድ መቅረብ የለበትም " ሲሉ መልሰዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
🔵 " ከ97 ጀምሮ የቆጠቡ ሰዎች መቼ ነው የሚደርሳቸው ፤ መቼ ነው የሚኖሩበት ? ሳይኖሩበት ሊሞቱ ነው እኮ ! " - አቶ አበበ አካሉ
⚫ " የ97 ደግሞ የሚባል የለም። እኛ እስከምናውቀው ዘግተናል " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ከአዲስ አበባ የኮሪደር ስራ ጋር በተያየዘ በርካቶች በልማት ተነሺነት ከኖሩበት አካባቢ ተነስተው ወደ ተለያዩ ጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲገቡ እየተደረገ ነው።
ምንም እንኳን ተነሺዎቹ መግባታቸው ላይ ቅሬታ ባይፈጥርም ከ97 አንስቶ ሲቆጥቡ የኖሩ ነዋሪዎች መፍትሄ ሳያገኙ መቅረታቸው እና አሁን ላይ አስተዳደሩ ቤት የተሰጠ መሆኑ ቅሬታ አሳድሯል።
ከሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት በተካሄደ የኮሪደር ስራውን በሚመለከት የውይይት መድረክ ላይ ይኸው ቅሬታና ጥያቄ ተነስቷል።
ጥያቄውን ካነሱት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
" ሲቆጥቡ የኖሩ ሰዎች ጉዳይ ምን ደረሰ ? አሁን ማህበረሰቡ ምን ያማል ከተማ አስተዳደሩን ' እኛ በቆጠብነው ገንዘብ ነው የልማት ተናሺዎችን እያሰፈረ ያለው ' የሚል ሮሮ አለ።
ለዚህ ምንድነው ምላሻችሁ ?
ከ97 ጀምሮ የቆጠቡ ሰዎች መቼ ነው የሚደርሳቸው ፤ መቼ ነው የሚኖሩበት ሳይኖሩበት ሊሞቱ ነው እኮ ! " ሲሉ ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?
" የኮንዶሚኒየም ቤት እስኪ ከየት አምጥታችሁ ነው በዚህ ደረጃ ያላችሁ ኃላፊዎች ' በቆጡት ገንዘብ ነው የሚሰራው ' የምትሉት።
እነ ንግድ ባንክ ናቸው ብሩን የሚያቀርቡት እስቲ እንነጋገር ትንሽ ወደ መረጃው ጠጋ ብላችሁ ብናወራ ምናለበት።
ኮንዶሚኒየም በብድር ነው የሚሰራው። የከተማ አስተዳደሩ በጀቱን አስይዞ ነው የሚበደረው።
ለምንድነው የሚቆጥቡት ? ከተባለ ዕጣ የደረሳቸው ዕለት የሚከፍሉትን እንዳያጡ ነው። እንጂ ቤቱን መገንቢያ አይደለም። ልክ ቤቱ ሲገነባ ብሩን ይከፍሉታል።
ሁለተኛ እንዴት ነው እኛ ብቻችንን የምንጠየቅበት ? ቤት ባልተዘጋጀበት በሚሊዮኖች መዝግቦ ቆጥቡ ብሎ ኃላፊነት ወስዶ የሰራ አካል እያለ ለምንድነው እኛ የምንወቀሰው ?
ቤት ሳያዘጋጅ ዜጎችን ልክ እንደ ማታለያ በሚሊየን መዝግቦ የበተነ እያለ ለምንድነው እኛ የምንወቀሰው ?
የኮንዶሚኒየም ቤት አጠቃላይ አንድ ቦታ እጅብ ብሎ ስለተሰራ ብዙ ይመስላችኋል እንጂ እስካሁን እስካጠናቀቅነው ያለው 300,000 ነው። የተመዘገበው በሚሊዮን ነው። በየጊዜው ተስፋ ቆርጦ፣ ተጣርቶ ተጣርቶ እኛ የደረስንበት 600,000 ነው። አክተቭ ይቆጥብ የነበረው። ግን ቤት ማግኘት እንዳለባቸው እናምናለን። ቤት ማግኘት አለባቸው።
ካለቁት ኮንዶሚኒየሞች ብራቸው ተዘርፎ፣ ቀድሞ ተከፍሎ ያልተሰራ 80 ህንጻ ብር ተከፍሎበት ጥለው ሄደዋል። በብዙ ውጣውረድ ነው 139,000 ቤቶችን የጨረስነው። የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ብቻ።
አሁንም ቢሆን ግን የከተማችን ነዋሪዎች ቤት ማግኘት አለባቸው። ለዚህም በኮንዶሚኒየም ብቻ አይደለም እንደ ቀድሞ በሚፈለገው ደረጃ ብድር ማግኘት አልቻልንም ከባንክ። ኮንዶሚኒየም መጥፎ ስለሆነ አላቆምነውም።
ከተማ አስተዳደሩ ዕዳ እየከፈለ ነው። ንግድ ባንክ የሚያበድረው የባለሃብትን ገንዘብ ነው አይደል ? 56 ቢሊዮን የኮንዶሚኒየም ዕዳ ነው የተረከብነው ዋስትና የሚሰጠው ከተማ አስተዳደሩ ስለሆነ ክፈሉ ተባልን ተገደድን በለውጥ ዘመኑ 30 ቢሊዮን ከፍለናል የኮንዶሚኒየም ዕዳ።
ይህ ሁሉ ዕዳ አንደኛ በከፍተኛ ሰብሲዲ ስለሚሰራ ነው ፤ ሌላው ያልተሰሩ ቤቶች የተከፈለባቸው አሉ። ሳይከፍሉ ሲሸጡ በተለያየ መንገድ ሲተላለፉ የነበሩ ቤት ውስጥ ያገኘናቸው ሰዎች ከግለሰብ የገዙ ናቸው፤ ሊገደዱ አይችሉም የኮንዶሚኒየም ክፈሉ ተብለው። አጣርተን እኮ በሚዲያ ነግረናችኋል ፤ ያጋጠመንን።
አሁን በግልና በመንግሥት አጋርነት ወደ 100,000 ቤቶች አስጀምረናል። የቁጠባ ቤቶችንም እየሰራን እያከራየን ነው። በሪስልቴትም በግል የሚሰሩትን እንደ ከተማው ፕሮጀክት ጠጋ ብለን እያገዝን ቶሎ እንዲጨርሱ እያደረግን ነው።
እስካሁን የቆጠቡትን አሁን በግልና መንግሥት ትብብር ከምንሰራው ውስጥ ቅድሚያ ሊያገኙ የሚችሉበትን አግባብ እየተከተልን ነው። ሁለተኛ ደግሞ ተደራጅተው በማህበር እንዲሰሩ ...እስካሁን ለተደራጁት መሬት አስረክበናል።
መነገጃ አታድርጉት፤ ከእውነታው ውጭ መነጋጃ ማድረጉ አይጠቅምም።
የ97 ደግሞ የሚባል የለም። እኛ እስከምናውቀው ዘግተናል። ባለፈው ያስጨረስናቸውን ኮንዶሚኒየም ቤቶች ቅድሚያ 97 አክቲቭ ቆጣቢዎች ሁሉ ዕጣ እንዲወጣላቸው ተደርጓል።
እነሱ ከወጣላቸው በኃላ ዲአክቲቬት ያደረገውን አካውን አክቲቬት ያደረገ ካለ እሱ ስለቆጠበ ቤት ስለሚፈልግ ለሚቀጥለው ጊዜ ሊታይ ይገባል ፤ እንጂ በዚህ መንገድ መቅረብ የለበትም " ሲሉ መልሰዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
😡1.67K❤552😭156🙏70😱69👏60🤔46🕊45😢38🥰27
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " ያለደረሰኝ አትሽጡ አልን እንጂ እቃ እንወርሳለን ያለ አካል የለም " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ " በከተማዋ በርካታ ነጋዴዎች በግብር ከፋይነት ተመዝግበው ደረሰኝ የማይሰጡ በመሆናቸው እና ችግሩም በጣም እየሰፋ በመሆኑ ወጥነት ባለው መንገድ ህጉን እንዲያከብሩ እና ወደስርዓት እንዲገቡ ለማድረግ እየሰራው ነው " ሲል ገልጿል። ቢሮው የታክስ ኢንተለጀንስ…
የዛሬው የመርካቶ ገበያ ውሎ ምን ይመስላል ?
በዛሬው እለት በመርካቶ የሚገኙ የተለያዩ የገበያ ማዕከላት ተዘግተው መዋላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረገው ቅኝት ማየት ችሏል።
የመርካቶ ገበያም ከዚህ ቀደም ከነበረው የንግድ እንቅስቃሴ ተቀዛቅዞ መዋሉን ነጋዴዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ተዘግተው ከዋሉት የገበያ ማዕከላት መካከል
ሚሊተሪ ተራ ፤ ዱባይ ተራ ፤ አድማስ እና አመዴ ገበያ አካባቢ የሚገኙ ሱቆች ይገኙበታል።
ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን የዘጉት ከደረሰኝ ጋር በተገናኘ ውዝግብ መሆኑ ታውቋል።
ነጋዴዎቹ ዛሬ ጠዋት በርካታ የንግድ ሱቆች ዝግ እንደነበሩ የተናገሩ ሲሆን በከሰአቱ የገበያ ሁኔታ አንዳንድ ሱቆች እንደተከፈቱ ገልፀዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ከሰዓት በኋላ ባደረጉት ቅኝት የጣና ገበያ ፣ ሲዳሞ ተራ እና ቦምብ ተራ አካባቢ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንደታዩበት ታዝበዋል።
በተወሰነ መልኩም ወደ ሸማ ተራ እና መሃል መርካቶ አካባቢዎች መደበኛ የንግድ እንቅስቃሴዎችን መመልከት ተችሏል።
ሆኖም ግን በሸማ ተራ ፣ ድር ተራ እና ሰሀን ተራ አካባቢዎች የነበረው የንግድ እንቅስቃሴ የተቀዛቀዘ መሆኑን ነጋዴዎች ነግረውናል።
በዛሬው እለት በሰሀን ተራ አካባቢ በግምት 8 ሰዓት ገደማ ላይ ነጋዴዎች " አነስተኛ ነው " ያሉት እሳት ተነስቶ እንደነበር ጠቁመዋል። ነገር ግን እሳቱ ሳይስፋፋ ወዲያው በነጋዴው ርብርብ እንደጠፋ ጠቅሰዋል።
በሰሀን ተራ አካባቢ የሚገኙት ሱቆች በአክሲዮን የገበያ ማዕከልን ለመገንባት ሱቆቻቸውን ለቀው እየወጡ እንደሆነም ካነጋገርናቸው ነጋዴዎች ተረድተናል።
በዚህ አካባቢ የሚገኙት ነጋዴዎች ሱቃቸውን የለቀቁት በስምምንነት መሆኑንም ተናግረዋል።
የተለቀቁትም ሱቆች ከወረዳው የመሬት የልማት አስተዳደር ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበት " ታሽጓል " የሚል ጽሑፍ ተለጥፎባቸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የተለያዩ የመርካቶ ነጋዴዎች በሸማ ተራ ከተከሰተው የእሳት አደጋ በኋላ " ስራ የለም " ሲሉ ገልፀዋል።
በተጨማሪም ያለ ደረሰኝ ሲነግዱ የተገኙ ነጋዴዎች ላይ ይጣላል የተባለው ቅጣት የተጋነነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሱቆቹ የተዘጉት " ግብይቶች ሁሉ በደረሰኝ ይካሄዱ " የሚለው ተቃውሞ እንዳልሆነ አንድ ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀ የመረጃ ምንጭ ገልጿል።
የመረጃ ምንጩ " ግብይቶች በደረሰኝ የሚደረጉ ቢሆንም ተቆጣጣሪ አካላት የተሸጡ እቃዎችን የሚያሳይ ደረሰኝ በሚጠይቁበት እና በምናሳያቸው ወቅት ከሚገባው በታች ነው የቆረጣችሁት በማለት በ6 ወር ሰርተነው የማናቀውን 100 ሺህ ቅጣት ጥለውብን ይሄዳሉ " በማለት አማረዋል።
በአንፃሩ አንድ ሌላ ነጋዴ እንደገለፁት ከንግድ ስራ መንግስት ማግኘት የሚገባው ገቢ ቢኖርም ይህ አሰራር የማይመቻቸው እና ደረሰኝ የማይቆርጡ ነጋዴዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
ከዚህ ቀደም ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የታክስ ኢንተለጀንስ እና የምርመራ ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ነጋሽ " መርካቶ በባህሪው ብዙ የክልል ግብር ከፋዮች የሚያለቅሱበት ቦታ ነው የሌሎች ክፍለ ከተሞች ግብር ከፋዮችም ቅሬታ ያቀርባሉ ደረሰኝ አይሰጡም በሚል ትልቅ ችግር ስላለበት ትኩረት ተደርጎበት ያለ ነው እንጂ አዲስ አይደለም " የሚል ምላሽ ሰጥተው ነበር።
ዳይሬክተሩ አክለውም " ቦታው በልዩ ሁኔታ (በግብር አሰባሰብ) በመንግስት ትኩረት ተደርጎበት ሊሰራበት የሚፈለግ አካባቢ ነው ነገር ግን ከአሰራር አንጻር በሚፈለገው ልክ ማሳካት አልተቻለም " ማለታቸው ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
በዛሬው እለት በመርካቶ የሚገኙ የተለያዩ የገበያ ማዕከላት ተዘግተው መዋላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረገው ቅኝት ማየት ችሏል።
የመርካቶ ገበያም ከዚህ ቀደም ከነበረው የንግድ እንቅስቃሴ ተቀዛቅዞ መዋሉን ነጋዴዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ተዘግተው ከዋሉት የገበያ ማዕከላት መካከል
ሚሊተሪ ተራ ፤ ዱባይ ተራ ፤ አድማስ እና አመዴ ገበያ አካባቢ የሚገኙ ሱቆች ይገኙበታል።
ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን የዘጉት ከደረሰኝ ጋር በተገናኘ ውዝግብ መሆኑ ታውቋል።
ነጋዴዎቹ ዛሬ ጠዋት በርካታ የንግድ ሱቆች ዝግ እንደነበሩ የተናገሩ ሲሆን በከሰአቱ የገበያ ሁኔታ አንዳንድ ሱቆች እንደተከፈቱ ገልፀዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ከሰዓት በኋላ ባደረጉት ቅኝት የጣና ገበያ ፣ ሲዳሞ ተራ እና ቦምብ ተራ አካባቢ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንደታዩበት ታዝበዋል።
በተወሰነ መልኩም ወደ ሸማ ተራ እና መሃል መርካቶ አካባቢዎች መደበኛ የንግድ እንቅስቃሴዎችን መመልከት ተችሏል።
ሆኖም ግን በሸማ ተራ ፣ ድር ተራ እና ሰሀን ተራ አካባቢዎች የነበረው የንግድ እንቅስቃሴ የተቀዛቀዘ መሆኑን ነጋዴዎች ነግረውናል።
በዛሬው እለት በሰሀን ተራ አካባቢ በግምት 8 ሰዓት ገደማ ላይ ነጋዴዎች " አነስተኛ ነው " ያሉት እሳት ተነስቶ እንደነበር ጠቁመዋል። ነገር ግን እሳቱ ሳይስፋፋ ወዲያው በነጋዴው ርብርብ እንደጠፋ ጠቅሰዋል።
በሰሀን ተራ አካባቢ የሚገኙት ሱቆች በአክሲዮን የገበያ ማዕከልን ለመገንባት ሱቆቻቸውን ለቀው እየወጡ እንደሆነም ካነጋገርናቸው ነጋዴዎች ተረድተናል።
በዚህ አካባቢ የሚገኙት ነጋዴዎች ሱቃቸውን የለቀቁት በስምምንነት መሆኑንም ተናግረዋል።
የተለቀቁትም ሱቆች ከወረዳው የመሬት የልማት አስተዳደር ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበት " ታሽጓል " የሚል ጽሑፍ ተለጥፎባቸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የተለያዩ የመርካቶ ነጋዴዎች በሸማ ተራ ከተከሰተው የእሳት አደጋ በኋላ " ስራ የለም " ሲሉ ገልፀዋል።
በተጨማሪም ያለ ደረሰኝ ሲነግዱ የተገኙ ነጋዴዎች ላይ ይጣላል የተባለው ቅጣት የተጋነነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሱቆቹ የተዘጉት " ግብይቶች ሁሉ በደረሰኝ ይካሄዱ " የሚለው ተቃውሞ እንዳልሆነ አንድ ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀ የመረጃ ምንጭ ገልጿል።
የመረጃ ምንጩ " ግብይቶች በደረሰኝ የሚደረጉ ቢሆንም ተቆጣጣሪ አካላት የተሸጡ እቃዎችን የሚያሳይ ደረሰኝ በሚጠይቁበት እና በምናሳያቸው ወቅት ከሚገባው በታች ነው የቆረጣችሁት በማለት በ6 ወር ሰርተነው የማናቀውን 100 ሺህ ቅጣት ጥለውብን ይሄዳሉ " በማለት አማረዋል።
በአንፃሩ አንድ ሌላ ነጋዴ እንደገለፁት ከንግድ ስራ መንግስት ማግኘት የሚገባው ገቢ ቢኖርም ይህ አሰራር የማይመቻቸው እና ደረሰኝ የማይቆርጡ ነጋዴዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
ከዚህ ቀደም ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የታክስ ኢንተለጀንስ እና የምርመራ ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ነጋሽ " መርካቶ በባህሪው ብዙ የክልል ግብር ከፋዮች የሚያለቅሱበት ቦታ ነው የሌሎች ክፍለ ከተሞች ግብር ከፋዮችም ቅሬታ ያቀርባሉ ደረሰኝ አይሰጡም በሚል ትልቅ ችግር ስላለበት ትኩረት ተደርጎበት ያለ ነው እንጂ አዲስ አይደለም " የሚል ምላሽ ሰጥተው ነበር።
ዳይሬክተሩ አክለውም " ቦታው በልዩ ሁኔታ (በግብር አሰባሰብ) በመንግስት ትኩረት ተደርጎበት ሊሰራበት የሚፈለግ አካባቢ ነው ነገር ግን ከአሰራር አንጻር በሚፈለገው ልክ ማሳካት አልተቻለም " ማለታቸው ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
😢585❤262😭99😡85👏62🕊31🤔26🙏26😱21🥰17
" የዕዳ ሽግሽግ ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ትልቅ የእፎይታ ጊዜን ይሰጣል " - ዓብዱልመናን መሐመድ (ዶ/ር)
የገንዘብ ሚኒስቴር ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ከመንግስታዊ አበዳሪዎቿ ጋራ በምርህ ደረጃ የዕዳ ሽግሽግ ለማድረግ መስማማቷን አስታውቋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ዙርያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየት የሰጡት፣ የፋይናንስ ባለሙያው ዶ/ር ዓብዱልመናን መሐመድ፣ " ስምምነቱ የግድ የዕዳ ስረዛን ላያካትት ይችላል፣ ግን ደግሞ የዕዳ መክፈያ ጊዜ ማራዘም በራሱ፣ ትልቅ ድል ነው " ይላሉ፡፡
በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ጉዳዮች ላይ ለረጅም ጊዜ ትንታኔና አስተያየት በመስጠት የሚታወቁት ዶ/ር ዓብዱል መናን፣ ለውጭ ዕዳ መክፈያ ሊውል የነበረው የውጭ ምንዛሪ፣ ለሀገር ውስጥ ክምችት ማሳደጊያ እና ለሀገራዊ ልማት ሊጠቅም እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
ዶ/ር ዓብዱልመናን መሐመድ በዝርዝር ምን አሉ ?
" ድርድሩ አራት አመታትን የፈጀ ነው፡፡ ሀገሪቱ ግጭት ውስጥም ስለነበረች፣ ይህ ፖለቲካዊ ምክንያት ሆኖ ለድርድሩ መዘግየቱ አስተዋፅኦ ሳያደርግ አልቀረም፡፡ አበዳሪዎቹ ሀገራት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም / IMF ጋራ መስማማትም እንደ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠውት ነበረ፡፡
ኢትዮጵያ፣ ባለፈው ሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ከተደረገው አጠቃላይ የማክሮ ኢከኮኖሚ ማሻሻያ ጋራ ተያይዞ ከዓለምአቀፉ የገንዘብ ተቋም ጋራ ተስማምታለች፡፡ ከዛም፣ ቻይና እና ፈረንሳይ የሚመሩት የአበዳሪዎች ቡድን ጋራ ሲደረግ የነበረው የዕዳ ሽግሽግ ድርድር ቀጠለ።
የኢትዮጵያ መንግስት ከአበዳሪዎቹ ሀገራት ጋራ በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መደረሱን ገልጿል፡፡ እርምጃው ደስ ይላል፣ የዕዳ መክፈያ ጊዜን በማራዘም ትንሽ ፋታ ያገኛል፡፡
ይህ ስምምነት የብድር ስረዛን ላያካትት ይችላል፡፡ ግን ደግሞ የዕዳ አከፋፈል ስርዓት ለውጥ በራሱ ትልቅ ነገር ነው፡፡ ሀገሪቱ ዕዳዋን የምትከፍልበትን ጊዜ ያራዝምልታል ማለት ነው፡፡
በአምስት አመት ውስጥ መክፈል የነበረብህን ዕዳ በአስር አመት ክፈል ስትባል፣ ትልቅ ፋታ ይሰጥሀል፡፡ በአሁኑ ስምምነት መሰረት የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ዕዳውን ለመክፈል የ 3 እና 4 አመታት ፋታ ያገኛል " ብለዋል።
የገንዘብ ሚኒስቴር በመግለጫው፣ የዕዳ ሽግሽግ ድርድሩ፣ በቡድን 20 ሀገራት ማዕቀፍ መሰረት 8.4 ቢሊዮን ዶላር የሚሸፍን እንደሆነ በመግለጫው አስታውቋል፡፡
ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ጋራ በተደረገው ስምምነት መሰረትም፣ ኢትዮጵያ የ3.5 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ እንዲሸጋሸግላት በመደራደር ላይ መሆኗን አመልክቷል፡፡
አሁን በመርህ ደረጃ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ ከ 2023 እስከ 2028 ድረስ የሚቆይ የ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ መክፈያ ጊዜ እፎይታ ማግኘቷን ተገልጿል፡፡
ዶ/ር ዓብዱልመናን ስለዚህ ጉዳይ ሲያስረዱ እንዲህ ይላሉ ፦
" ኢትዮጵያ በርከት ያለ የውጭ እዳ አለባት፡፡ ከተለያዩ ሀገራት ሌሎች ብድሮችም ቢኖሩም የመክፈያ ጊዜያቸው ረጅም በመሆኑ አንገብጋቢ አይደሉም፡፡
በጣም አንገብጋቢ የነበረው ከአጠቃላይ ዕዳዋ 8.4 ቢሊዮን ዶላሩ ነው፡፡ ለምን ብትል፣ የመክፈያ ጊዜው በመቃረቡ ነው አንገብጋቢ የሆነው፡፡ በዚህኛው የእዳ መጠን ላይ፣ የዕዳ ሽግሽግ እንዲደረግ አራት አመታትን የፈጀ ድርድር ነው የተደረገው፡፡
ከዓለምቀፉ የገንዘብ ድርጅት ጋራ በተደረገው ስምምነት መሰረት ደግሞ፣ ከ8.4 ቢሊዮን ዶላሩ ውስጥ በ3.5 ቢሊዮን ዶላሩ ላይ የዕዳ ሽግሽግ ድርድር እንዲደረግ ግፊት ሲደረግ ነበር፡፡
አሁን የኢትዮጵያ መንግስት በ2.5 ቢሊዮን ዶላሩ ላይ በመርህ ደረጃ የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት ላይ መደረሱን አስታውቋል፡፡ ይህ ማለት እ.ኤ.አ እስከ 2028 ዓ.ም ድረስ የእዳ መክፈያ ጊዜ ተራዝሟል ነው፡፡ እስከዛ ድረስ እፎይታ አግኝተናል፡፡ "
ዶ/ር ዓብዱልመናን የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት መደረጉ ኢኮኖሚያዊ አንድምታው ምንድነው ? ብለን ላነሳንላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ፦
" የእዳ መክፈያ ጊዜን በማራዘም እፎይታ ሲገኝ፣ ለውጭ ዕዳ መክፈያ ስንጠቀምበት የነበረው ሀብት፣ የሀገር ውስጥ የውጭ ምንዛሪ ክምችትን ለማሳደግና ለልማት ስራዎች ልናውለው እንችላለን " ብለዋል፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የገንዘብ ሚኒስቴር ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ከመንግስታዊ አበዳሪዎቿ ጋራ በምርህ ደረጃ የዕዳ ሽግሽግ ለማድረግ መስማማቷን አስታውቋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ዙርያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየት የሰጡት፣ የፋይናንስ ባለሙያው ዶ/ር ዓብዱልመናን መሐመድ፣ " ስምምነቱ የግድ የዕዳ ስረዛን ላያካትት ይችላል፣ ግን ደግሞ የዕዳ መክፈያ ጊዜ ማራዘም በራሱ፣ ትልቅ ድል ነው " ይላሉ፡፡
በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ጉዳዮች ላይ ለረጅም ጊዜ ትንታኔና አስተያየት በመስጠት የሚታወቁት ዶ/ር ዓብዱል መናን፣ ለውጭ ዕዳ መክፈያ ሊውል የነበረው የውጭ ምንዛሪ፣ ለሀገር ውስጥ ክምችት ማሳደጊያ እና ለሀገራዊ ልማት ሊጠቅም እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
ዶ/ር ዓብዱልመናን መሐመድ በዝርዝር ምን አሉ ?
" ድርድሩ አራት አመታትን የፈጀ ነው፡፡ ሀገሪቱ ግጭት ውስጥም ስለነበረች፣ ይህ ፖለቲካዊ ምክንያት ሆኖ ለድርድሩ መዘግየቱ አስተዋፅኦ ሳያደርግ አልቀረም፡፡ አበዳሪዎቹ ሀገራት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም / IMF ጋራ መስማማትም እንደ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠውት ነበረ፡፡
ኢትዮጵያ፣ ባለፈው ሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ከተደረገው አጠቃላይ የማክሮ ኢከኮኖሚ ማሻሻያ ጋራ ተያይዞ ከዓለምአቀፉ የገንዘብ ተቋም ጋራ ተስማምታለች፡፡ ከዛም፣ ቻይና እና ፈረንሳይ የሚመሩት የአበዳሪዎች ቡድን ጋራ ሲደረግ የነበረው የዕዳ ሽግሽግ ድርድር ቀጠለ።
የኢትዮጵያ መንግስት ከአበዳሪዎቹ ሀገራት ጋራ በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መደረሱን ገልጿል፡፡ እርምጃው ደስ ይላል፣ የዕዳ መክፈያ ጊዜን በማራዘም ትንሽ ፋታ ያገኛል፡፡
ይህ ስምምነት የብድር ስረዛን ላያካትት ይችላል፡፡ ግን ደግሞ የዕዳ አከፋፈል ስርዓት ለውጥ በራሱ ትልቅ ነገር ነው፡፡ ሀገሪቱ ዕዳዋን የምትከፍልበትን ጊዜ ያራዝምልታል ማለት ነው፡፡
በአምስት አመት ውስጥ መክፈል የነበረብህን ዕዳ በአስር አመት ክፈል ስትባል፣ ትልቅ ፋታ ይሰጥሀል፡፡ በአሁኑ ስምምነት መሰረት የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ዕዳውን ለመክፈል የ 3 እና 4 አመታት ፋታ ያገኛል " ብለዋል።
የገንዘብ ሚኒስቴር በመግለጫው፣ የዕዳ ሽግሽግ ድርድሩ፣ በቡድን 20 ሀገራት ማዕቀፍ መሰረት 8.4 ቢሊዮን ዶላር የሚሸፍን እንደሆነ በመግለጫው አስታውቋል፡፡
ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ጋራ በተደረገው ስምምነት መሰረትም፣ ኢትዮጵያ የ3.5 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ እንዲሸጋሸግላት በመደራደር ላይ መሆኗን አመልክቷል፡፡
አሁን በመርህ ደረጃ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ ከ 2023 እስከ 2028 ድረስ የሚቆይ የ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ መክፈያ ጊዜ እፎይታ ማግኘቷን ተገልጿል፡፡
ዶ/ር ዓብዱልመናን ስለዚህ ጉዳይ ሲያስረዱ እንዲህ ይላሉ ፦
" ኢትዮጵያ በርከት ያለ የውጭ እዳ አለባት፡፡ ከተለያዩ ሀገራት ሌሎች ብድሮችም ቢኖሩም የመክፈያ ጊዜያቸው ረጅም በመሆኑ አንገብጋቢ አይደሉም፡፡
በጣም አንገብጋቢ የነበረው ከአጠቃላይ ዕዳዋ 8.4 ቢሊዮን ዶላሩ ነው፡፡ ለምን ብትል፣ የመክፈያ ጊዜው በመቃረቡ ነው አንገብጋቢ የሆነው፡፡ በዚህኛው የእዳ መጠን ላይ፣ የዕዳ ሽግሽግ እንዲደረግ አራት አመታትን የፈጀ ድርድር ነው የተደረገው፡፡
ከዓለምቀፉ የገንዘብ ድርጅት ጋራ በተደረገው ስምምነት መሰረት ደግሞ፣ ከ8.4 ቢሊዮን ዶላሩ ውስጥ በ3.5 ቢሊዮን ዶላሩ ላይ የዕዳ ሽግሽግ ድርድር እንዲደረግ ግፊት ሲደረግ ነበር፡፡
አሁን የኢትዮጵያ መንግስት በ2.5 ቢሊዮን ዶላሩ ላይ በመርህ ደረጃ የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት ላይ መደረሱን አስታውቋል፡፡ ይህ ማለት እ.ኤ.አ እስከ 2028 ዓ.ም ድረስ የእዳ መክፈያ ጊዜ ተራዝሟል ነው፡፡ እስከዛ ድረስ እፎይታ አግኝተናል፡፡ "
ዶ/ር ዓብዱልመናን የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት መደረጉ ኢኮኖሚያዊ አንድምታው ምንድነው ? ብለን ላነሳንላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ፦
" የእዳ መክፈያ ጊዜን በማራዘም እፎይታ ሲገኝ፣ ለውጭ ዕዳ መክፈያ ስንጠቀምበት የነበረው ሀብት፣ የሀገር ውስጥ የውጭ ምንዛሪ ክምችትን ለማሳደግና ለልማት ስራዎች ልናውለው እንችላለን " ብለዋል፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
😡709❤193👏186😭67🙏48🤔38🕊33😢31😱22🥰9💔5
" በመመሪያው መሰረት ምርታቸውን በንጥረ ነገር ያበለጸጉ አምራቾች እንደ ገና መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል " - የምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን
ከፋብሪካዎች የሚወጡ የምግብ ዘይትና የዱቄት ምርቶች በንጥረ ነገር እንዲበለፅጉ የሚያስገድደው ረቂቅ መመሪያ በሦስት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ወደ ስራ ይገባል መባሉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የምግብ ምዝገባና ፈቃድ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ አስፋው በንጥረ ነገር የበለፀጉ የምግብ ዘይቶችና የዱቄት ምርቶችን ለመመዝገብ የሚያስችል መመሪያ መዘጋጀቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
መመሪያው ተግባራዊ ከሆነ በኋላ በመመሪያው መሰረት የበለጸጉ ምግቦችን የማያመርቱ የምግብ ዱቄት እና የዘይት አምራች ድርጅቶች ምርትን የማሰራጨት የገበያ ፈቃድ አይሰጣቸውም ብለዋል።
ሃላፊው በዝርዝር ባነሱት ሃሳብ ምን አሉ ?
" አዲስ ነገር አይደለም ከዚህም በፊት ይታወቃል የምግብ ዱቄት እና የዘይት ምርቶች በንጥረ ነገር እንዲበለጽጉ የሚል ግዴታ በአዋጅ የተጣለው በ2014 ዓም ነበር።
ይህንን ለማስፈጸም በምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን የተለያዩ መመሪያዎች ይዘጋጃሉ ይህ መመሪያም የስንዴ እና የዘይት አምራች ድርጅቶች ምርታቸውን በባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ከማስመዝገባቸው አስቀድሞ ምን ምን ነገሮች ማሟላት አለባቸው የሚለውን የያዘ መመሪያ ነው።
መመሪያውን ከአምራቾች ጋር የማወያየት ሥራ እየሰራን ነው።
ምርቶቹ ከዚህም በፊት የተመዘገቡ ነበሩ ነገር ግን በአስፈላጊው ንጥረ ነገር ሳይበለጽጉ ነበር እንዲመዘገቡ የተደረጉት አሁን ደግሞ በመመሪያው መሰረት አምራቾች ምርታቸውን በንጥረ ነገር ካበለጸጉ በኋላ እንደ ገና መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ከዚህ ቀደም ምግብን በሚመለከት የሚያስመዘግቡበት መመሪያ ነበር የአሁኑ መመሪያ ሊካተት ስለሚገባው ንጥረ ነገር (ቫይታሚን) ራሱን ችሎ ወጥቶ ነው።
መመሪያው እንደመጀመሪያ ለዱቄት፣ ለዘይት እና ጨው ተብሎ ቢወጣም ከዚህ በኋላ ማንኛውም አምራች ' ምርቴን በንጥረ ነገር አበለጽጋለሁ ' ብሎ ቢመጣ የሚስተናገድበት መመሪያ ነው የተዘጋጀው።
በመመሪያው መሰረት ማንኛውም በንጥረ ነገር የበለጸገ ምርት ደረጃ ሳይለጠፍበት ወደ ገበያ የማይወጣ ሲሆን በምርቶቻቸው ላይ በማንኛውም ጊዜ ለውጥ ካደረጉ ለባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ማሳወቅ ይጠበቅባቸዋል።
መመሪያው በአመራር ደረጃ ከሳምንት በፊት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል የሚስተካከሉ ነገሮች ሃሳብ ተሰጥተውበታል ከሦስት ሳምንት በኋላ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
ከፋብሪካዎች የሚወጡ የምግብ ዘይትና የዱቄት ምርቶች በንጥረ ነገር እንዲበለፅጉ የሚያስገድደው ረቂቅ መመሪያ በሦስት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ወደ ስራ ይገባል መባሉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የምግብ ምዝገባና ፈቃድ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ አስፋው በንጥረ ነገር የበለፀጉ የምግብ ዘይቶችና የዱቄት ምርቶችን ለመመዝገብ የሚያስችል መመሪያ መዘጋጀቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
መመሪያው ተግባራዊ ከሆነ በኋላ በመመሪያው መሰረት የበለጸጉ ምግቦችን የማያመርቱ የምግብ ዱቄት እና የዘይት አምራች ድርጅቶች ምርትን የማሰራጨት የገበያ ፈቃድ አይሰጣቸውም ብለዋል።
ሃላፊው በዝርዝር ባነሱት ሃሳብ ምን አሉ ?
" አዲስ ነገር አይደለም ከዚህም በፊት ይታወቃል የምግብ ዱቄት እና የዘይት ምርቶች በንጥረ ነገር እንዲበለጽጉ የሚል ግዴታ በአዋጅ የተጣለው በ2014 ዓም ነበር።
ይህንን ለማስፈጸም በምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን የተለያዩ መመሪያዎች ይዘጋጃሉ ይህ መመሪያም የስንዴ እና የዘይት አምራች ድርጅቶች ምርታቸውን በባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ከማስመዝገባቸው አስቀድሞ ምን ምን ነገሮች ማሟላት አለባቸው የሚለውን የያዘ መመሪያ ነው።
መመሪያውን ከአምራቾች ጋር የማወያየት ሥራ እየሰራን ነው።
ምርቶቹ ከዚህም በፊት የተመዘገቡ ነበሩ ነገር ግን በአስፈላጊው ንጥረ ነገር ሳይበለጽጉ ነበር እንዲመዘገቡ የተደረጉት አሁን ደግሞ በመመሪያው መሰረት አምራቾች ምርታቸውን በንጥረ ነገር ካበለጸጉ በኋላ እንደ ገና መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ከዚህ ቀደም ምግብን በሚመለከት የሚያስመዘግቡበት መመሪያ ነበር የአሁኑ መመሪያ ሊካተት ስለሚገባው ንጥረ ነገር (ቫይታሚን) ራሱን ችሎ ወጥቶ ነው።
መመሪያው እንደመጀመሪያ ለዱቄት፣ ለዘይት እና ጨው ተብሎ ቢወጣም ከዚህ በኋላ ማንኛውም አምራች ' ምርቴን በንጥረ ነገር አበለጽጋለሁ ' ብሎ ቢመጣ የሚስተናገድበት መመሪያ ነው የተዘጋጀው።
በመመሪያው መሰረት ማንኛውም በንጥረ ነገር የበለጸገ ምርት ደረጃ ሳይለጠፍበት ወደ ገበያ የማይወጣ ሲሆን በምርቶቻቸው ላይ በማንኛውም ጊዜ ለውጥ ካደረጉ ለባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ማሳወቅ ይጠበቅባቸዋል።
መመሪያው በአመራር ደረጃ ከሳምንት በፊት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል የሚስተካከሉ ነገሮች ሃሳብ ተሰጥተውበታል ከሦስት ሳምንት በኋላ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
❤240🙏53😡34😭28👏23🤔13😢11💔11🕊3🥰2😱1
" ሰው ይምጣ ሲመጣ ግን የተመዘገበ ሰው መሆን አለበት። በአንድ ቦታ ወንጀል ሰርቶ የመጣ ሰው አዲስ አበባን መደበቂያ ማድረግ የለበትም " - ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ
የአዲስ አበባ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ፅ/ቤት የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን ለኅብረተሰቡ ለማስተዋወቅና ለማስገንዘብ የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር።
በዚህ መድረክ ላይ በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ለተሳታፊዎች በተለይ ከሲቪል ምዝገባ እና ከቆሻሻ አስተዳደር ጋር ተያይዞ እየተሰሩ ባሉ ሥራዎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መድረኩን ተከታትሎ ነበር።
ዋና ሥራ አስኪያጁ ምን አሉ ?
" ከዚህ ቀደም አንድ ሰው አንድ ነው የሚለውን ማረጋገጥ ባለመቻላችን በሁለት በሦስት ማንነት መታወቂያ ማውጣት፤ የታክስ ማጭበርበር እንዲሁም በተጭበረበረ ማንነት የንብረት ቅሚያ ይከናወን ነበር " ብለዋል።
አሁን ላይ " አዲስ አበባ ውስጥ በአንድ ስም መታወቂያ ያወጣ ሰው ዳግም በዛ ስም መታወቂያ የማያወጣበትን ሥርዓት ፈጥረናል " ሲሉ በሲቪል ምዝገባ ረገድ የተሰራውን ሥራ አስረድተዋል።
አብዛኛው ሰው የፋይዳ መታወቂያ የሚመዘገበው በአስገዳጅ መልኩ ነው የሚሉት ኢንጂነር ወንድሙ " ይሄ መሆን አልነበረበትም " ሲሉ የማኅበረሰቡ ግንዛቤ አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
" ለምንድነው ፋይዳ የማትመዘገበው ? ሲባል ' ምን ያደርግልኛል ' የሚል ሰው በጣም ብዙ ነው ፤ ነገ ከፋይናንስ፣ ከታክስ፣ ከቤት ኪራይ፣ ከመንጃ ፈቃድ፣ ከንብረት ባለይዞታነት ጋር ይያያዛል " ሲሉ ጠቁመዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ አዲስ አበባ የስበት ማዕከል መሆኗን በመጥቀስ ህጋዊ ያልሆኑ ፍልሰቶች መኖራቸው በከተማው መሰረተ ልማት ላይ ጫና እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ጉዳይ ላይ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታን አጭር ማብራሪያ ጠይቋቸዋል።
ምን መለሱ ?
" አዲስ አበባ ውስጥ ያለውን ሰው ማወቅ አለብን ፤ በአግባቡ የተመዘገበ መሆን አለበት። መንግስት አገልግሎት የሚያቀርበው ለ5 ሚሊዮን ነው ለ8 ሚሊዮን የሚለው መታወቅ አለበት።
ሰው ይምጣ ሲመጣ ግን የተመዘገበ ሰው መሆን አለበት። በአንድ ቦታ ወንጀል ሰርቶ የመጣ ሰው አዲስ አበባን መደበቂያ ማድረግ የለበትም ከተማ አስተዳደሩ ያወቀው ነዋሪ መሆን አለበት። ያንን ማድረግ የሚያስችል ሥራ እየሰራን ነው ያለነው " ብለዋል።
በውይይት መድረኩ ከዚሁ ከሲቪል ምዝገባ ጋር ተያይዞ የተነሳው ጉዳይ በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች እየተከናወነ ያለው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጉዳይ ነው።
ለሚቀጥለው ዓመት የትምህርት ዘመን ምዝገባ የፋይዳ መታወቂያ በመስፈርትነት በማስቀመጥ ለዚህም በአንድ ወር ውስጥ 450 ሺ ተማሪዎችን ለመመዝገብ ታቅዶ ስራ ቢጀመርም መመዝገብ የተቻለው 130 ሺ የሚሆኑትን መሆኑን ዋና ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
" ወላጆች የተሟላ መረጃ አይልኩልንም " ያሉት ኢንጂነር ወንድሙ አንዳንዶቹ ለራሳቸውም የፋይዳ መታወቂያ የሌላቸው መሆኑን በመጥቀስ የግንዛቤ እጥረት ለሥራው ፈተና መሆኑን አንስተዋል።
በተመሳሳይ ከሞት እና ጋብቻ ሰርተፊኬት ጋር ተያይዞ የማስመዝገብ ባህሉ ደካማ መሆኑን በማንሳት በተለይ ከሞት ምዝገባ ጋር ተያይዞ ከሃይማኖት ተቋማት ጋር አብሮ በመስራት እዛው ሰርተፊኬት የሚያገኙበት ሁኔታ እየተመቻቸ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ ከተማ ወደ 5 ሚሊዮን ነዋሪዎች አሏት ተብሎ እንደሚታሰብ በዚሁ መድረክ የተገለጸ ሲሆን የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ድረገጽ ላይ ያለው መረጃ እንደሚያመለክተው በከተማዋ የተመዘገቡ 2.7 ሚሊዮን እንዲሁም የዲጂታል መታወቂያ የወሰዱት 2.1 ሚሊዮን የሚሆኑት ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ፅ/ቤት የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን ለኅብረተሰቡ ለማስተዋወቅና ለማስገንዘብ የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር።
በዚህ መድረክ ላይ በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ለተሳታፊዎች በተለይ ከሲቪል ምዝገባ እና ከቆሻሻ አስተዳደር ጋር ተያይዞ እየተሰሩ ባሉ ሥራዎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መድረኩን ተከታትሎ ነበር።
ዋና ሥራ አስኪያጁ ምን አሉ ?
" ከዚህ ቀደም አንድ ሰው አንድ ነው የሚለውን ማረጋገጥ ባለመቻላችን በሁለት በሦስት ማንነት መታወቂያ ማውጣት፤ የታክስ ማጭበርበር እንዲሁም በተጭበረበረ ማንነት የንብረት ቅሚያ ይከናወን ነበር " ብለዋል።
አሁን ላይ " አዲስ አበባ ውስጥ በአንድ ስም መታወቂያ ያወጣ ሰው ዳግም በዛ ስም መታወቂያ የማያወጣበትን ሥርዓት ፈጥረናል " ሲሉ በሲቪል ምዝገባ ረገድ የተሰራውን ሥራ አስረድተዋል።
አብዛኛው ሰው የፋይዳ መታወቂያ የሚመዘገበው በአስገዳጅ መልኩ ነው የሚሉት ኢንጂነር ወንድሙ " ይሄ መሆን አልነበረበትም " ሲሉ የማኅበረሰቡ ግንዛቤ አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
" ለምንድነው ፋይዳ የማትመዘገበው ? ሲባል ' ምን ያደርግልኛል ' የሚል ሰው በጣም ብዙ ነው ፤ ነገ ከፋይናንስ፣ ከታክስ፣ ከቤት ኪራይ፣ ከመንጃ ፈቃድ፣ ከንብረት ባለይዞታነት ጋር ይያያዛል " ሲሉ ጠቁመዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ አዲስ አበባ የስበት ማዕከል መሆኗን በመጥቀስ ህጋዊ ያልሆኑ ፍልሰቶች መኖራቸው በከተማው መሰረተ ልማት ላይ ጫና እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ጉዳይ ላይ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታን አጭር ማብራሪያ ጠይቋቸዋል።
ምን መለሱ ?
" አዲስ አበባ ውስጥ ያለውን ሰው ማወቅ አለብን ፤ በአግባቡ የተመዘገበ መሆን አለበት። መንግስት አገልግሎት የሚያቀርበው ለ5 ሚሊዮን ነው ለ8 ሚሊዮን የሚለው መታወቅ አለበት።
ሰው ይምጣ ሲመጣ ግን የተመዘገበ ሰው መሆን አለበት። በአንድ ቦታ ወንጀል ሰርቶ የመጣ ሰው አዲስ አበባን መደበቂያ ማድረግ የለበትም ከተማ አስተዳደሩ ያወቀው ነዋሪ መሆን አለበት። ያንን ማድረግ የሚያስችል ሥራ እየሰራን ነው ያለነው " ብለዋል።
በውይይት መድረኩ ከዚሁ ከሲቪል ምዝገባ ጋር ተያይዞ የተነሳው ጉዳይ በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች እየተከናወነ ያለው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጉዳይ ነው።
ለሚቀጥለው ዓመት የትምህርት ዘመን ምዝገባ የፋይዳ መታወቂያ በመስፈርትነት በማስቀመጥ ለዚህም በአንድ ወር ውስጥ 450 ሺ ተማሪዎችን ለመመዝገብ ታቅዶ ስራ ቢጀመርም መመዝገብ የተቻለው 130 ሺ የሚሆኑትን መሆኑን ዋና ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
" ወላጆች የተሟላ መረጃ አይልኩልንም " ያሉት ኢንጂነር ወንድሙ አንዳንዶቹ ለራሳቸውም የፋይዳ መታወቂያ የሌላቸው መሆኑን በመጥቀስ የግንዛቤ እጥረት ለሥራው ፈተና መሆኑን አንስተዋል።
በተመሳሳይ ከሞት እና ጋብቻ ሰርተፊኬት ጋር ተያይዞ የማስመዝገብ ባህሉ ደካማ መሆኑን በማንሳት በተለይ ከሞት ምዝገባ ጋር ተያይዞ ከሃይማኖት ተቋማት ጋር አብሮ በመስራት እዛው ሰርተፊኬት የሚያገኙበት ሁኔታ እየተመቻቸ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ ከተማ ወደ 5 ሚሊዮን ነዋሪዎች አሏት ተብሎ እንደሚታሰብ በዚሁ መድረክ የተገለጸ ሲሆን የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ድረገጽ ላይ ያለው መረጃ እንደሚያመለክተው በከተማዋ የተመዘገቡ 2.7 ሚሊዮን እንዲሁም የዲጂታል መታወቂያ የወሰዱት 2.1 ሚሊዮን የሚሆኑት ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
😡220❤164👏25🕊18🙏14🤔8😢7😭7😱5🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ.ም በዓለ ሆሣዕና ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከብሯል። ቅድስት ቤተክርስቲያን ፥ " የሆሣዕና በዓል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም አእሩግና…
" ሆሣዕና '' (የዐብይ ጾም 8ኛ ሳምንት)
ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሁዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣዔ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው።
ሆሣዕና ማለት የቃሉ ትርጉም " እባክህ አሁን አድን " ማለት ነው።
ዕለቱ ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም ሽማግሌዎች እና ሕፃናት '' ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም '' በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት ነው፡፡
ይህ ዕለት በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘንባባ ተይዞ፣ እየተዘመረ እጅግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ይታሰባል።
በዐብይ ጾም ከሰርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሣዔ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡
በዚህ ጊዜ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት ካህናት መስቀል በእጃቸው አይዙም፣ አያሳልሙም ፣ ይፍቱኝ ተብሎ ወደካህን አይቀረብም፤ ይህ ሳምንት የጌታን የመጨረሻው ስቃይ የሚታሰብበት ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
#Repost
@tikvahethiopia
ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሁዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣዔ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው።
ሆሣዕና ማለት የቃሉ ትርጉም " እባክህ አሁን አድን " ማለት ነው።
ዕለቱ ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም ሽማግሌዎች እና ሕፃናት '' ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም '' በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት ነው፡፡
ይህ ዕለት በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘንባባ ተይዞ፣ እየተዘመረ እጅግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ይታሰባል።
በዐብይ ጾም ከሰርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሣዔ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡
በዚህ ጊዜ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት ካህናት መስቀል በእጃቸው አይዙም፣ አያሳልሙም ፣ ይፍቱኝ ተብሎ ወደካህን አይቀረብም፤ ይህ ሳምንት የጌታን የመጨረሻው ስቃይ የሚታሰብበት ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
#Repost
@tikvahethiopia
8❤2.96K🙏290😡66🕊51🥰36🤔23😱19😭17👏15😢6
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኮሌጆች ወደ ጠቅላላ ትምህርት ለመግባት ዝግጅት ላይ ናቸው " -አስተያየት ሰጪ የዘርፉ ተዋናዮች ➡️ " አብዛኞቹ ኮሌጆች በራሳቸው መንገድ መክሰማቸው አይቀርም " አብዛኞቹ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መቀጠል ስላልቻሉ ትምህርት ቤት ከፍተው ለመስራት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ስማችን አይጠቀስ ያሉና በዘርፉ የተሰማሩ ተዋናዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ፣…
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት " ስጋት ላይ ጥሎናል " ያሉት አዲስ መመሪያ ምን ይዟል ?
የኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አሰራር ስርዓት ለማስያዝ በሚል ዳግም ምዝገባ በማካሔድ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም በሰጣቸው መግለጫዎች አስታውቋል፡፡
በዚህ ሒደት 85 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዲሱ መስፈርት መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ እንደሚዘጉም ተገልፆ ነበር፡፡
በመመሪያው መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ያመለከቱት 287 ተቋማትም፣ አብዛኞቹ መስፈርቱን እንደማያሟሉ እየተገለፀ ይገኛል፡፡ ሆኖም እስካሁን ድረስ በአዲሱ መመሪያ ተመዝነው የትኞቹ እንደሚቀጥሉና እንደማይቀጥሉ አልተገለፀም፡፡
የዘርፉ ተዋናዮች በበኩላቸው፣ “ የዳግም ምዝገባ መመሪያውና የያዛቸው መመዘኛዎች የሚተገበሩና የሚያሰሩ አይደሉም፣ በዚህ መመሪያ ተመዝነው የሚቀጥሉት ተቋማት ጥቂቶች ብቻ ነው የሚሆኑት፣ አብዛኞቹም መዘጋታቸው አይቀሬ ነው ” ይላሉ፡፡
ለመሆኑ በዳግመ ምዝገባ መመሪያው ላይ የተቀመጡት ዋና ዋናዎቹ መመዘኛዎች ምን ይላሉ፣ የትምህርት ተቋማቱን ስጋት ላይ የጣሉትስ እንዴት ነው በማለት የጠየቅናቸው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች የሚከተለውን አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል፡፡
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች ፦
“ በመመሪያ ላይ የተቀመጠውና የግል ተቋማትን አቅም ያላገናዘበው አንደኛው መመዘኛ የመማሪያ ህንፃን ይመለከታል፡፡ አንድ ተቋም አምስትና ከዚያ በላይ ፕሮግራሞችን የሚሰጥ ከሆነ አንድ ሙሉ ህንፃ ብቻውን መያዝ አለበት ይላል፡፡ አብዛኞቹ ኮሌጆች የሆነ አንድ ህንፃ ላይ የተወሰኑ ፎቆችን ተከራይተው የሚሰሩ ናቸው፡፡ ይህን ፎቅ ብቻችሁን ያዙት ሲባሉ አቅሙ የላቸውም፡፡
መንግስት እንዲህ አይነት መመሪያ ሲያወጣ በሊዝ መሬት እንድናገኝና የራሳችንን ህንፃ እንድንገነባ እንኳ ሁኔታዎችን አያመቻችም፡፡ ለትምህርት ዘርፍ የተመቻቹ ዕድሎች የሉም፡፡ ለምሳሌ ከውጭ የሚገቡ ለትምህርት አስፈላጊ የሆኑ መፃህፍት፣ ኮምፒዩተሮችና ቁሳቁሶች ከቀረጥ ነፃ መግባት ነበረባቸው፣ ይህ አልተደረገም፡፡
ሁለተኛው መስፈርት የሰው ሀይልን የሚመለከት ነው፡፡ አስተማሪዎችና የቢሮ ሰራተኞች የዶክትሬት ዲግሪ ያላቸው ይሁኑ ይላል፡፡
በእኛ ሀገር ያሉ ዶክተሮች ጥቂቶች ናቸው፡፡ ብዙዎቹ በመንግስት ድጋፍ በውጭ ሀገራት የተማሩ ናቸው፡፡ ቀደም ሲል የግል ኮሌጆች ከመንግስት ተቋማት መምህራንን እየተጋሩ ሲያስተምሩ ነበር፡፡
ይህም ጥያቄ ሲያስነሳ የመንግስት አካላት ባሉበት ውይይት ሲደረግበት ነበር፡፡ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን በሁለቱም ቦታዎች እንዲያስተምሩ/ዱዋል ኢምፕሎይመንት/ እንዲፈቀድላቸው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በአንድ ፕሮግራም ውስጥ ብዙ ፒኤችዲ የያዙ መምህራን አሉ፣ ትርፍ ሰዓት አላቸው፣ ጫና አይበዛባቸውም፡፡ ስለዚህ በግል ኮሌጆችም ያስተምሩ የሚል ነበር ውይይቱ፡፡
ይህ ውይይት መጨረሻው ላይ ከደረሰ በኋላ ወደኋላ ተመለሰ፡፡ ምክንያቱ አይታወቅም፡፡ በዚህ ምክንያት ዶክተር መምህራንን አናገኝም፡፡
ከላይ ካለው ከዲኑ ጀምሮ እስከ ቢሮ ሰራተኞች ድረስ ዶክተሮች ይሁኑ ይላል መመሪያው፡፡ እስከ ማስተርስ ድረስ የሚያስተምሩት መምህራን ዶክተሮች ቢሆኑ እንስማማለን፣ ሁሉም የተቋሙ ሰራተኞች ዶክተሮች ይሁኑ ማለት ግን አያስኬድም፡፡ በቂ የሰው ሀይል የለም ገበያው ውስጥ፡፡
ሶስተኛው ነጥብ፣ ከመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ የተቀመጠው ነው፡፡ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና፣ በትንሹ 25 ከመቶ ተማሪዎችን ያላሳለፈ ተቋም መዘጋት እንዳለበት ይገልፃል መመዘኛው፡፡ ይህን መስፈርት ልተግብረው ስትል ችግር ያመጣል፡፡
ለምሳሌ ፦ በ2016 ዓ.ም የነበረውን የመውጫ ፈተና ብነግርህ፣ 202 ተቋማት ተፈታኝ ተማሪዎችን አቅርበው፣ 25 ተቋማት አንድም ተማሪ አላሳለፉም፡፡ ከ25 በመቶ በላይ ያሳለፉትም 27 ናቸው፡፡ ከዚህ ውጭ ያሉት ይዘጋሉ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ መመዘኛ የሚደረስበት አይደለም፡፡ ይህ በሒደት ነው እንጂ በአንዴ ይተግበር መባል የለበትም፡፡
አራተኛው አስቸጋሪ መመዘኛ የምንለው የስፖርት ማዘውተሪያ በሚል የተቀመጠው ነው፡፡ ይህም በተወሰነ ደረጃ የሚያስኬድ አይደለም፡፡
አዲስ ተቋም ከሆነ ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን ብር በዝግ አካውንት/የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥ አለበት የሚልም አለ፡፡ ይህ በጣም ከባድ ነው፡፡ አዳዲስ ተቋማት ቁሳቁስ ነው ሊያሟሉበት የሚገባው ይህን ገንዘብ፡፡
ገበያው ላይ ያለው ተማሪም ዝቅተኛ ነው፡፡ በመመሪያው ላይ ያሉትን መመዘኛዎች ሁሉ አሟልተው ዳግም ተመዘገቡ እንኳን ብንል፣ ተቋማቱ ተማሪ የማያገኙ ከሆነ መዘጋታቸው አይቀርም፡፡ ስለዚህ ሞክሩት፣ ስርዓቱ በራሱ ከገበያ ያስወጣችኋል ነው እያሉን ያሉት በአጭሩ፡፡ ይህ ሁሉ ተደምሮ ሁኔታውን ከባድ ያደርገዋል፡፡
በአዲሱ መመሪያ ላይ ሀሳብ ሰጥተናል፡፡ በማህበራችን በኩል መሻሻል አለበት የምንለውን ጉዳይ በሰነድ አዘጋጅተን አስገብተናል፣ አንድም ማስተካከያ አልተደረገም፣ ጥያቄያችን መልስ አላገኘም፡፡
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ያዘጋጀው መድረክም፣ ይህን መመሪያ እወቁት የሚል እንጂ፣ በመመሪያው ላይ እንወያይ የሚል አልነበረም፡፡ የእኛን አስተያየት አካትቱ በሚል ብዙ ጭቅጭቅ ነበር፣ ሰሚ አላገኘንም፡፡ መጀመሪያ ያስተዋወቁን መመሪያ ፀድቆ ነው ወደ ትግበራ የተገባው፡፡
ጥያቄያችን ይህ እርምጃ በሒደት መወሰድ/መተግበር ነበረበት የሚል ነው፡፡ በአንዴ መደረግ የለበትም፡፡ በአንድ ቀን ሁሉንም ነገር ከመሰረቱ እንቀይረው ማለት አያስኬድም፣ አሉታዊ ተፅዕኖም ያስከትላል፡፡ ተማሪዎች ከአንድ ተቋም ወደ ሌላ ተቋም እየተዛወሩ በመንገላታት ላይ ናቸው፡፡ በርካታ ሰራተኞቻቸውን የበተኑ ተቋማት አሉ፡፡ የተቋማት አሰራር ስርዓት መያዝ አለበት፣ የትምህርት ጥራትም መረጋገጥ አለበት፣ ግን ደግሞ ይህ መሆን የሚችለው በሒደት ነው፡፡ ይህ መታየት አለበት፡፡ ”
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በዚህ ጉዳይ ዙርያ ምላሽና ማብራሪያ ይዞ ይቀርባል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አሰራር ስርዓት ለማስያዝ በሚል ዳግም ምዝገባ በማካሔድ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም በሰጣቸው መግለጫዎች አስታውቋል፡፡
በዚህ ሒደት 85 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዲሱ መስፈርት መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ እንደሚዘጉም ተገልፆ ነበር፡፡
በመመሪያው መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ያመለከቱት 287 ተቋማትም፣ አብዛኞቹ መስፈርቱን እንደማያሟሉ እየተገለፀ ይገኛል፡፡ ሆኖም እስካሁን ድረስ በአዲሱ መመሪያ ተመዝነው የትኞቹ እንደሚቀጥሉና እንደማይቀጥሉ አልተገለፀም፡፡
የዘርፉ ተዋናዮች በበኩላቸው፣ “ የዳግም ምዝገባ መመሪያውና የያዛቸው መመዘኛዎች የሚተገበሩና የሚያሰሩ አይደሉም፣ በዚህ መመሪያ ተመዝነው የሚቀጥሉት ተቋማት ጥቂቶች ብቻ ነው የሚሆኑት፣ አብዛኞቹም መዘጋታቸው አይቀሬ ነው ” ይላሉ፡፡
ለመሆኑ በዳግመ ምዝገባ መመሪያው ላይ የተቀመጡት ዋና ዋናዎቹ መመዘኛዎች ምን ይላሉ፣ የትምህርት ተቋማቱን ስጋት ላይ የጣሉትስ እንዴት ነው በማለት የጠየቅናቸው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች የሚከተለውን አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል፡፡
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች ፦
“ በመመሪያ ላይ የተቀመጠውና የግል ተቋማትን አቅም ያላገናዘበው አንደኛው መመዘኛ የመማሪያ ህንፃን ይመለከታል፡፡ አንድ ተቋም አምስትና ከዚያ በላይ ፕሮግራሞችን የሚሰጥ ከሆነ አንድ ሙሉ ህንፃ ብቻውን መያዝ አለበት ይላል፡፡ አብዛኞቹ ኮሌጆች የሆነ አንድ ህንፃ ላይ የተወሰኑ ፎቆችን ተከራይተው የሚሰሩ ናቸው፡፡ ይህን ፎቅ ብቻችሁን ያዙት ሲባሉ አቅሙ የላቸውም፡፡
መንግስት እንዲህ አይነት መመሪያ ሲያወጣ በሊዝ መሬት እንድናገኝና የራሳችንን ህንፃ እንድንገነባ እንኳ ሁኔታዎችን አያመቻችም፡፡ ለትምህርት ዘርፍ የተመቻቹ ዕድሎች የሉም፡፡ ለምሳሌ ከውጭ የሚገቡ ለትምህርት አስፈላጊ የሆኑ መፃህፍት፣ ኮምፒዩተሮችና ቁሳቁሶች ከቀረጥ ነፃ መግባት ነበረባቸው፣ ይህ አልተደረገም፡፡
ሁለተኛው መስፈርት የሰው ሀይልን የሚመለከት ነው፡፡ አስተማሪዎችና የቢሮ ሰራተኞች የዶክትሬት ዲግሪ ያላቸው ይሁኑ ይላል፡፡
በእኛ ሀገር ያሉ ዶክተሮች ጥቂቶች ናቸው፡፡ ብዙዎቹ በመንግስት ድጋፍ በውጭ ሀገራት የተማሩ ናቸው፡፡ ቀደም ሲል የግል ኮሌጆች ከመንግስት ተቋማት መምህራንን እየተጋሩ ሲያስተምሩ ነበር፡፡
ይህም ጥያቄ ሲያስነሳ የመንግስት አካላት ባሉበት ውይይት ሲደረግበት ነበር፡፡ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን በሁለቱም ቦታዎች እንዲያስተምሩ/ዱዋል ኢምፕሎይመንት/ እንዲፈቀድላቸው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በአንድ ፕሮግራም ውስጥ ብዙ ፒኤችዲ የያዙ መምህራን አሉ፣ ትርፍ ሰዓት አላቸው፣ ጫና አይበዛባቸውም፡፡ ስለዚህ በግል ኮሌጆችም ያስተምሩ የሚል ነበር ውይይቱ፡፡
ይህ ውይይት መጨረሻው ላይ ከደረሰ በኋላ ወደኋላ ተመለሰ፡፡ ምክንያቱ አይታወቅም፡፡ በዚህ ምክንያት ዶክተር መምህራንን አናገኝም፡፡
ከላይ ካለው ከዲኑ ጀምሮ እስከ ቢሮ ሰራተኞች ድረስ ዶክተሮች ይሁኑ ይላል መመሪያው፡፡ እስከ ማስተርስ ድረስ የሚያስተምሩት መምህራን ዶክተሮች ቢሆኑ እንስማማለን፣ ሁሉም የተቋሙ ሰራተኞች ዶክተሮች ይሁኑ ማለት ግን አያስኬድም፡፡ በቂ የሰው ሀይል የለም ገበያው ውስጥ፡፡
ሶስተኛው ነጥብ፣ ከመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ የተቀመጠው ነው፡፡ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና፣ በትንሹ 25 ከመቶ ተማሪዎችን ያላሳለፈ ተቋም መዘጋት እንዳለበት ይገልፃል መመዘኛው፡፡ ይህን መስፈርት ልተግብረው ስትል ችግር ያመጣል፡፡
ለምሳሌ ፦ በ2016 ዓ.ም የነበረውን የመውጫ ፈተና ብነግርህ፣ 202 ተቋማት ተፈታኝ ተማሪዎችን አቅርበው፣ 25 ተቋማት አንድም ተማሪ አላሳለፉም፡፡ ከ25 በመቶ በላይ ያሳለፉትም 27 ናቸው፡፡ ከዚህ ውጭ ያሉት ይዘጋሉ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ መመዘኛ የሚደረስበት አይደለም፡፡ ይህ በሒደት ነው እንጂ በአንዴ ይተግበር መባል የለበትም፡፡
አራተኛው አስቸጋሪ መመዘኛ የምንለው የስፖርት ማዘውተሪያ በሚል የተቀመጠው ነው፡፡ ይህም በተወሰነ ደረጃ የሚያስኬድ አይደለም፡፡
አዲስ ተቋም ከሆነ ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን ብር በዝግ አካውንት/የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥ አለበት የሚልም አለ፡፡ ይህ በጣም ከባድ ነው፡፡ አዳዲስ ተቋማት ቁሳቁስ ነው ሊያሟሉበት የሚገባው ይህን ገንዘብ፡፡
ገበያው ላይ ያለው ተማሪም ዝቅተኛ ነው፡፡ በመመሪያው ላይ ያሉትን መመዘኛዎች ሁሉ አሟልተው ዳግም ተመዘገቡ እንኳን ብንል፣ ተቋማቱ ተማሪ የማያገኙ ከሆነ መዘጋታቸው አይቀርም፡፡ ስለዚህ ሞክሩት፣ ስርዓቱ በራሱ ከገበያ ያስወጣችኋል ነው እያሉን ያሉት በአጭሩ፡፡ ይህ ሁሉ ተደምሮ ሁኔታውን ከባድ ያደርገዋል፡፡
በአዲሱ መመሪያ ላይ ሀሳብ ሰጥተናል፡፡ በማህበራችን በኩል መሻሻል አለበት የምንለውን ጉዳይ በሰነድ አዘጋጅተን አስገብተናል፣ አንድም ማስተካከያ አልተደረገም፣ ጥያቄያችን መልስ አላገኘም፡፡
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ያዘጋጀው መድረክም፣ ይህን መመሪያ እወቁት የሚል እንጂ፣ በመመሪያው ላይ እንወያይ የሚል አልነበረም፡፡ የእኛን አስተያየት አካትቱ በሚል ብዙ ጭቅጭቅ ነበር፣ ሰሚ አላገኘንም፡፡ መጀመሪያ ያስተዋወቁን መመሪያ ፀድቆ ነው ወደ ትግበራ የተገባው፡፡
ጥያቄያችን ይህ እርምጃ በሒደት መወሰድ/መተግበር ነበረበት የሚል ነው፡፡ በአንዴ መደረግ የለበትም፡፡ በአንድ ቀን ሁሉንም ነገር ከመሰረቱ እንቀይረው ማለት አያስኬድም፣ አሉታዊ ተፅዕኖም ያስከትላል፡፡ ተማሪዎች ከአንድ ተቋም ወደ ሌላ ተቋም እየተዛወሩ በመንገላታት ላይ ናቸው፡፡ በርካታ ሰራተኞቻቸውን የበተኑ ተቋማት አሉ፡፡ የተቋማት አሰራር ስርዓት መያዝ አለበት፣ የትምህርት ጥራትም መረጋገጥ አለበት፣ ግን ደግሞ ይህ መሆን የሚችለው በሒደት ነው፡፡ ይህ መታየት አለበት፡፡ ”
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በዚህ ጉዳይ ዙርያ ምላሽና ማብራሪያ ይዞ ይቀርባል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
❤1.71K😡99🙏56😭50👏21🕊21😢20🤔17🥰16😱10
#AddisAbaba
" በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " - ገቢዎች ቢሮ
ከሐምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ/ም ድረስ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ ደንበኞች ግብራቸውን ማሳወቅ የጀመሩ ሲሆን እስከ ሐምሌ 30/2017 ዓም ድረስ ግብር ግብራቸውን እያሳወቁ ይቆያሉ።
ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር ለየት ባለ መልኩ በየደረጃው ያሉ ግብር ከፋዮች በወጣላቸው መርሃ ግብር መሰረት ግብራቸውን እንዲከፍሉ እንደሚደረግ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ ሰውነት " ከዚህ ቀደም የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሃምሌ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ነበር የሚከፍሉት ዘንድሮ ይህ አሰራር ተቀይሮ ሃምሌን ለዝግጅት እንዲጠቀሙት እና ግብራቸውን ከ ነሐሴ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ እንዲከፍሉ ተወስኗል አከፋፈላቸውም በስም ቅደም ተከተል ይሆናል " ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በስም ቅደም ተከተል እንዲከፍሉ መደረጉ ግብር ከፋዩ ላይ መጨናነቆች እንዳይኖሩ እና ለብልሹ አሰራሮች እንዳይዳረጉ ያግዛል ነው ያሉት።
አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?
" የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋይ ደንበኞች በነሐሴ ወር የመጀመሪያው ሳምንት ላይ የስም ዝርዝራቸው ከ A-D ያሉ ግብር ከፋዮች የሚስተናገዱበት ፕሮግራም ወጥቷል፣ በዚህም መሰረት ግብር ከፋዩን በአራት ሳምንት በመከፋፈል አመታዊ ግብራቸውን እንዲያሳውቁ እና እንዲከፍሉ ይደረጋል።
የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮችን በሚመለከትም ከዚህ ቀደም ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 የአመታዊ ግብራቸውን የመክፈያ እና የማሳወቂያ ጊዜያቸው ነበር።
እነዚህ ግብር ከፋዮችም ሐምሌ እና ነሃሴን ለዝግጅት ተጠቅመው መስከረም እና ጥቅምትን ግብራቸውን የሚከፍሉበት ፕሮግራም ወጥቷል።
ቢሮው በተለያዩ ጊዜያት ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ወቅት የተነሱ የተለያዩ ችግሮች ነበሩ እነዚህን የተጠቀሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ በጥናት የተለዩ 24 አይነት አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግተናል ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለምሳሌ የኦዲት ጥራት ጋር ላይ ከአሰራር ጋር በተያያዘ ባሉ ክፍተቶች ምክንያት ሁለት ኦዲተሮች አንድ አይነት ፋይል ተመልክተው ውሳኔ ሲወስኑ ግን ሁለት አይነት ውሳኔ የሚወስኑበት አሰራር ነበር ይህንን ለማስቀረት የሚያስችል የአሰራር ስርአት ተዘርግቷል።
ከሂሳብ መዝገብ ጋር በተገናኘም የሂሳም መዝገብ መያዝ ያለባቸው ግብር ከፋዮች መዝገቡን ባለመያዛቸው በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ ነበር።
አፈጻጸም ላይ በነበረ ክፍተት ምክንያት በተለይም የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ ሲስተናገዱ የቆዩ ቢሆንም ከአሁኑ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ጀምሮ ያለ ሂሳብ መዝገብ አይሰራም።
ሂሳብ መዝገብ ሳይዙ የሚመጡ ከሆነ ግን የሚወሰነው ውሳኔ አስተማሪ የሚሆን ይሆናል።
የግብር አሰባሰብ ስርአቱም ከእጅ ንክኪ በጸዳ መንገድ እንዲሆን በማሰብ የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋዮች በET-TAX በተሰኘ በተቋሙ በለማ መተግበሪያ እቤታቸው ተቀምጠው ግብራቸውን የሚያውቁበት እና የሚከፍሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
በSMS በሚደርሳቸው መረጃም በTelebirr እና CBE Birr ግብራቸውን መክፈል ይችላሉ።
የደረጃ 'ሀ' እና የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮችም በተመሳሳይ E-TAX በተሰኘ መተግበሪያ እንዲከፍሉ እያደረግን ያለንበት ሁኔታ አለ ነገር ግን ሁሉም ወደዚህ አሰራር ስርአት ገና አልገቡም።
ከፍተኛ ግብር ከፋዮች 100 ፕርሰንት ወደዚህ አሰራር ስርአት ገብተዋል ቀሪዎቹ በየቅርንጫፉ እቅድ ተይዞ አብዛኛው ግብር ከፋይ ወደዚህ አሰራር እንዲገባ እየተሰራ ነው።
የኦዲት ጥራትን የሚያረጋግጥ የስራ ክፍል ተደራጅቷል ኦዲተሩ የወሰነው ውሳኔ ምን ያህል ጥራት አለው የሚለውን ያረጋግጣል ከፍተኛ ልዩነት ከተፈጠረም ግብር ከፋዩ እንዲከፈል ይደረጋል፣ ይህንን የወሰነው አካልም ተጠያቂ ይሆናል።
የግብር ከፋዩን ሂሳብ መዝግብ የሚያዘጋጁ ባለሞያዎች በሚመለከት ከዚህ ቀደም ከግብር ከፋዩ ጋር በመደራደር ከፍተኛ የሆነ ግብር የመሰወር ስራ የሚሰሩበት እና የተሳሳቱ ሰነዶችን የሚያቀርቡበት ሁኔታ ነበር።
በዚህ ጊዜ ግብር ከፋዩን ኦዲት አድርገን ገንዘቡን ብናስከፍልም የሂሳብ ባለሞያዎቹ ተጠያቂ የምናደርግበት አሰራር አልነበረም አሁን የሂሳብ ባለሞያዎቹም ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር ዘርግተናል።
ኦንላይን ግብይትንም ለመቆጣጠር እና ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ የሚቻልበት የአሰራር ስረዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።
ከማዕከል ሁሉንም ቅርንጫፎች ለመቆጣጠር የሚያስችል ካሜራ አስገጥመናል።
በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
" በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " - ገቢዎች ቢሮ
ከሐምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ/ም ድረስ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ ደንበኞች ግብራቸውን ማሳወቅ የጀመሩ ሲሆን እስከ ሐምሌ 30/2017 ዓም ድረስ ግብር ግብራቸውን እያሳወቁ ይቆያሉ።
ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር ለየት ባለ መልኩ በየደረጃው ያሉ ግብር ከፋዮች በወጣላቸው መርሃ ግብር መሰረት ግብራቸውን እንዲከፍሉ እንደሚደረግ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ ሰውነት " ከዚህ ቀደም የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሃምሌ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ነበር የሚከፍሉት ዘንድሮ ይህ አሰራር ተቀይሮ ሃምሌን ለዝግጅት እንዲጠቀሙት እና ግብራቸውን ከ ነሐሴ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ እንዲከፍሉ ተወስኗል አከፋፈላቸውም በስም ቅደም ተከተል ይሆናል " ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በስም ቅደም ተከተል እንዲከፍሉ መደረጉ ግብር ከፋዩ ላይ መጨናነቆች እንዳይኖሩ እና ለብልሹ አሰራሮች እንዳይዳረጉ ያግዛል ነው ያሉት።
አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?
" የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋይ ደንበኞች በነሐሴ ወር የመጀመሪያው ሳምንት ላይ የስም ዝርዝራቸው ከ A-D ያሉ ግብር ከፋዮች የሚስተናገዱበት ፕሮግራም ወጥቷል፣ በዚህም መሰረት ግብር ከፋዩን በአራት ሳምንት በመከፋፈል አመታዊ ግብራቸውን እንዲያሳውቁ እና እንዲከፍሉ ይደረጋል።
የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮችን በሚመለከትም ከዚህ ቀደም ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 የአመታዊ ግብራቸውን የመክፈያ እና የማሳወቂያ ጊዜያቸው ነበር።
እነዚህ ግብር ከፋዮችም ሐምሌ እና ነሃሴን ለዝግጅት ተጠቅመው መስከረም እና ጥቅምትን ግብራቸውን የሚከፍሉበት ፕሮግራም ወጥቷል።
ቢሮው በተለያዩ ጊዜያት ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ወቅት የተነሱ የተለያዩ ችግሮች ነበሩ እነዚህን የተጠቀሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ በጥናት የተለዩ 24 አይነት አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግተናል ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለምሳሌ የኦዲት ጥራት ጋር ላይ ከአሰራር ጋር በተያያዘ ባሉ ክፍተቶች ምክንያት ሁለት ኦዲተሮች አንድ አይነት ፋይል ተመልክተው ውሳኔ ሲወስኑ ግን ሁለት አይነት ውሳኔ የሚወስኑበት አሰራር ነበር ይህንን ለማስቀረት የሚያስችል የአሰራር ስርአት ተዘርግቷል።
ከሂሳብ መዝገብ ጋር በተገናኘም የሂሳም መዝገብ መያዝ ያለባቸው ግብር ከፋዮች መዝገቡን ባለመያዛቸው በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ ነበር።
አፈጻጸም ላይ በነበረ ክፍተት ምክንያት በተለይም የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ ሲስተናገዱ የቆዩ ቢሆንም ከአሁኑ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ጀምሮ ያለ ሂሳብ መዝገብ አይሰራም።
ሂሳብ መዝገብ ሳይዙ የሚመጡ ከሆነ ግን የሚወሰነው ውሳኔ አስተማሪ የሚሆን ይሆናል።
የግብር አሰባሰብ ስርአቱም ከእጅ ንክኪ በጸዳ መንገድ እንዲሆን በማሰብ የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋዮች በET-TAX በተሰኘ በተቋሙ በለማ መተግበሪያ እቤታቸው ተቀምጠው ግብራቸውን የሚያውቁበት እና የሚከፍሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
በSMS በሚደርሳቸው መረጃም በTelebirr እና CBE Birr ግብራቸውን መክፈል ይችላሉ።
የደረጃ 'ሀ' እና የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮችም በተመሳሳይ E-TAX በተሰኘ መተግበሪያ እንዲከፍሉ እያደረግን ያለንበት ሁኔታ አለ ነገር ግን ሁሉም ወደዚህ አሰራር ስርአት ገና አልገቡም።
ከፍተኛ ግብር ከፋዮች 100 ፕርሰንት ወደዚህ አሰራር ስርአት ገብተዋል ቀሪዎቹ በየቅርንጫፉ እቅድ ተይዞ አብዛኛው ግብር ከፋይ ወደዚህ አሰራር እንዲገባ እየተሰራ ነው።
የኦዲት ጥራትን የሚያረጋግጥ የስራ ክፍል ተደራጅቷል ኦዲተሩ የወሰነው ውሳኔ ምን ያህል ጥራት አለው የሚለውን ያረጋግጣል ከፍተኛ ልዩነት ከተፈጠረም ግብር ከፋዩ እንዲከፈል ይደረጋል፣ ይህንን የወሰነው አካልም ተጠያቂ ይሆናል።
የግብር ከፋዩን ሂሳብ መዝግብ የሚያዘጋጁ ባለሞያዎች በሚመለከት ከዚህ ቀደም ከግብር ከፋዩ ጋር በመደራደር ከፍተኛ የሆነ ግብር የመሰወር ስራ የሚሰሩበት እና የተሳሳቱ ሰነዶችን የሚያቀርቡበት ሁኔታ ነበር።
በዚህ ጊዜ ግብር ከፋዩን ኦዲት አድርገን ገንዘቡን ብናስከፍልም የሂሳብ ባለሞያዎቹ ተጠያቂ የምናደርግበት አሰራር አልነበረም አሁን የሂሳብ ባለሞያዎቹም ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር ዘርግተናል።
ኦንላይን ግብይትንም ለመቆጣጠር እና ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ የሚቻልበት የአሰራር ስረዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።
ከማዕከል ሁሉንም ቅርንጫፎች ለመቆጣጠር የሚያስችል ካሜራ አስገጥመናል።
በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
❤966😡476😭89😱44🤔22🙏22🕊20😢10👏8💔7🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የ2017 ዓ/ም የግብር ዘመን ግብር አወሳሰንና አሰባሰብ አሰራር ይፋ አድርጓል።
አዲሱ መመሪያ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመክፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው ግብር ከፋዮችን በሚመለከት።
እንዲሁም የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ያልተወጡ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ዝርዝር ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ተፈርሞ ለሁሉም ለግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተልኳል።
ደብዳቤው "የተወሰኑ ግብር ከፋዬች በህጉ የተጣለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ ባለው የተለየ ባህሪ ምክንያት መቸገራቸውን በተለያየ ጊዜ በመጥቀስ አቤቱታ ያቀረቡ" መሆኑን ገልጿል።
ይሁን እንጂ የግብር ሕጉ ለየትኛውም የንግድ ዘርፍ በተለየ መልኩ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ቀሪ አለማድረጉንም አሳውቋል።
ይህንኑ ግዴታ አለመወጣትም አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለየ ባህሪ ያላቸው የተወሰኑ የሥራ ዘርፎች የግብር ህጉን ድንጋጌዎች በአስከበረ አግባብ የገቢ አሰበሰቡን እና የአገልግሎት አሰጣቱን ፍታሀዊነት ማዕከል ያደረገ የአሰራር ሥርዓት ለ2017 የግብር ማሳወቂያ ጊዜ ሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታን ተፈጻሚነት በቅጣት ብቻ በማለፍ ማዘግየት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።
ስለሆነም የደረጃ "ሀ" እና የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዬች የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ግብር ከፋዬች በማይወጡበት ጊዜ ለደረጃ «ሐ» ግብር ከፋዬች የወጣውን ገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 የትርፍ ሕዳግ እና በግምት ግብር አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 138/2010 በቁርጥ የወጪ ሰንጠረዥ መጠቀም ዘርፉ ግዴታውን በገቢ ግብር ሕጉ መሰረት እንዳይወጣ ከተማውም ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳይሰበስብ ምክንያት ስለሚሆን ይህንኑ ክፍተት ለመዝጋት በገቢ ግብር አዋጁ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 80 መሰረት ግብር በግምት በሚሰላበት ጊዜ፦
ከግብር ከፋዮች ግንዛቤ የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ እና ሥራቸውም ከመንግስት ጋር በተገባ ውል ብቻ የሚያከናውኑ በማህበር የተደራጁ :-
- የትምህርት ቤቶችና የምገባ ማዕከላት መጋቢ እናቶች
- በከተማ ጽዳትና ውበት ደረቅ ቆሻሻ እና ገጸ-ምድር ማስዋብ ላይ የተሰማሩ
- ከንግድ ቢሮ ትስስር የተፈጠረላቸው የሸገር ዳቦን የሚሸጡ ማህበራት
ከመንግስት ተቋማት ጋር ያላቸውን ውልና በበጀት ዓመቱ ከአሰራቸው የመንግስት ተቋም ዓመቱን ሙሉ የተከፈላቸውን ክፍያ የሚገልጽ መረጃ ሲያመጡ መረጃን መሰረት አድርጎ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ገቢው ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
በተጨማሪም የሸገር ዳቦን የሚሸጡ በተጓዳኝ የሚከናውኑ የንግድ ስራዎች መኖራቸው በመስክ ምልከታ ተረጋግጦ በየዘርፉ የቀን ገቢ ግምት እንዲገመትላቸው ተደርጎ ግብሩ ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-
➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።
(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የ2017 ዓ/ም የግብር ዘመን ግብር አወሳሰንና አሰባሰብ አሰራር ይፋ አድርጓል።
አዲሱ መመሪያ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመክፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው ግብር ከፋዮችን በሚመለከት።
እንዲሁም የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ያልተወጡ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ዝርዝር ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ተፈርሞ ለሁሉም ለግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተልኳል።
ደብዳቤው "የተወሰኑ ግብር ከፋዬች በህጉ የተጣለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ ባለው የተለየ ባህሪ ምክንያት መቸገራቸውን በተለያየ ጊዜ በመጥቀስ አቤቱታ ያቀረቡ" መሆኑን ገልጿል።
ይሁን እንጂ የግብር ሕጉ ለየትኛውም የንግድ ዘርፍ በተለየ መልኩ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ቀሪ አለማድረጉንም አሳውቋል።
ይህንኑ ግዴታ አለመወጣትም አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለየ ባህሪ ያላቸው የተወሰኑ የሥራ ዘርፎች የግብር ህጉን ድንጋጌዎች በአስከበረ አግባብ የገቢ አሰበሰቡን እና የአገልግሎት አሰጣቱን ፍታሀዊነት ማዕከል ያደረገ የአሰራር ሥርዓት ለ2017 የግብር ማሳወቂያ ጊዜ ሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታን ተፈጻሚነት በቅጣት ብቻ በማለፍ ማዘግየት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።
ስለሆነም የደረጃ "ሀ" እና የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዬች የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ግብር ከፋዬች በማይወጡበት ጊዜ ለደረጃ «ሐ» ግብር ከፋዬች የወጣውን ገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 የትርፍ ሕዳግ እና በግምት ግብር አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 138/2010 በቁርጥ የወጪ ሰንጠረዥ መጠቀም ዘርፉ ግዴታውን በገቢ ግብር ሕጉ መሰረት እንዳይወጣ ከተማውም ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳይሰበስብ ምክንያት ስለሚሆን ይህንኑ ክፍተት ለመዝጋት በገቢ ግብር አዋጁ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 80 መሰረት ግብር በግምት በሚሰላበት ጊዜ፦
ከግብር ከፋዮች ግንዛቤ የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ እና ሥራቸውም ከመንግስት ጋር በተገባ ውል ብቻ የሚያከናውኑ በማህበር የተደራጁ :-
- የትምህርት ቤቶችና የምገባ ማዕከላት መጋቢ እናቶች
- በከተማ ጽዳትና ውበት ደረቅ ቆሻሻ እና ገጸ-ምድር ማስዋብ ላይ የተሰማሩ
- ከንግድ ቢሮ ትስስር የተፈጠረላቸው የሸገር ዳቦን የሚሸጡ ማህበራት
ከመንግስት ተቋማት ጋር ያላቸውን ውልና በበጀት ዓመቱ ከአሰራቸው የመንግስት ተቋም ዓመቱን ሙሉ የተከፈላቸውን ክፍያ የሚገልጽ መረጃ ሲያመጡ መረጃን መሰረት አድርጎ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ገቢው ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
በተጨማሪም የሸገር ዳቦን የሚሸጡ በተጓዳኝ የሚከናውኑ የንግድ ስራዎች መኖራቸው በመስክ ምልከታ ተረጋግጦ በየዘርፉ የቀን ገቢ ግምት እንዲገመትላቸው ተደርጎ ግብሩ ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-
➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።
(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
1❤1.32K😡175🤔35🙏35🥰26😢23🕊23😭22😱18👏16
" አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል።
አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤዢያ 27 መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን ወደ ቬትናም ሃኖይ ከተማ የሚያደርገው በረራ 28 ኛው መዳረሻው ይሆናል።
አቶ መስፍን " 190 በረራዎች በሳምንት ወደ ኤዢያ እናደርግ ነበር የአሁኑ በረራ በሳምንት ለ አራት ቀናት የሚከናወን በመሆኑ በአህጉሩ በሳምንት የምናደርገውን በረራ ወደ 194 ከፍ አድርገነዋል " ብለዋል።
ሃኖይ ለንግድ እና ለቱሪዝም የምትመረጥ መዳረሻ በመሆኗም የቀጥታ በረራ በመጀመሩ 120 የሚሆኑ አፍሪካውያን በዛሬው ምሽት ወደ ቬትናም ሃኖይ እንደሚጓዙ ተገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው " አየር መንገዱ በየጊዜው የሚጨምራቸው መዳረሻዎች በምን መስፈርት የተመረጡ ናቸው ? አፍሪካን እርስ በእርስ የማገናኘት ሥራስ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ምን ምላሽ ሰጡ ?
" ወደ አንድ ሃገር እና ከተማ የበረራ መስመር ከመክፈታችን በፊት የአዋጭነት ጥናት እናካሄዳለን።
አዋጭነት ማለት ገበያው አለ ወይ በረራ ብንጀምርስ በቂ መንገደኛ እናገኛለን ወይ የሚለው ላይ ጥናት እናካሂዳለን።
ያ ጥናት በቂ መንገደኛ አለ ሲለን በረራውን እንጀምራለን።
እድገት የሚመጣው አዳዲስ የበረራ መስመሮችን በመጨመር ወይም ባሉት ላይ የበረራ ምልልሱን በመጨመር ነው።
አፍሪካ ውስጥ በአሁኑ ሰአት በ 40 ሃገራት ወደ 61 ከተሞች እንበራለን።
ወደ ፊት እያየን የምንበርባቸው ሃገሮች ተጨማሪ ከተሞችን አዋጭ ሆነው ስናገኛቸው ፈቃዱን እንዳገኘን እንበራለን።
በተጨማሪም የማንበርባቸው ሃገሮችም ፈቃድ እንዳገኘን አዋጭነት እያየን እንበራለን በዚህ መንገድ አፍሪካ ውስጥ መዳረሻችንን እና የበረራ ምልልሱን እንጨምራለን።
አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል።
አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤዢያ 27 መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን ወደ ቬትናም ሃኖይ ከተማ የሚያደርገው በረራ 28 ኛው መዳረሻው ይሆናል።
አቶ መስፍን " 190 በረራዎች በሳምንት ወደ ኤዢያ እናደርግ ነበር የአሁኑ በረራ በሳምንት ለ አራት ቀናት የሚከናወን በመሆኑ በአህጉሩ በሳምንት የምናደርገውን በረራ ወደ 194 ከፍ አድርገነዋል " ብለዋል።
ሃኖይ ለንግድ እና ለቱሪዝም የምትመረጥ መዳረሻ በመሆኗም የቀጥታ በረራ በመጀመሩ 120 የሚሆኑ አፍሪካውያን በዛሬው ምሽት ወደ ቬትናም ሃኖይ እንደሚጓዙ ተገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው " አየር መንገዱ በየጊዜው የሚጨምራቸው መዳረሻዎች በምን መስፈርት የተመረጡ ናቸው ? አፍሪካን እርስ በእርስ የማገናኘት ሥራስ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ምን ምላሽ ሰጡ ?
" ወደ አንድ ሃገር እና ከተማ የበረራ መስመር ከመክፈታችን በፊት የአዋጭነት ጥናት እናካሄዳለን።
አዋጭነት ማለት ገበያው አለ ወይ በረራ ብንጀምርስ በቂ መንገደኛ እናገኛለን ወይ የሚለው ላይ ጥናት እናካሂዳለን።
ያ ጥናት በቂ መንገደኛ አለ ሲለን በረራውን እንጀምራለን።
እድገት የሚመጣው አዳዲስ የበረራ መስመሮችን በመጨመር ወይም ባሉት ላይ የበረራ ምልልሱን በመጨመር ነው።
አፍሪካ ውስጥ በአሁኑ ሰአት በ 40 ሃገራት ወደ 61 ከተሞች እንበራለን።
ወደ ፊት እያየን የምንበርባቸው ሃገሮች ተጨማሪ ከተሞችን አዋጭ ሆነው ስናገኛቸው ፈቃዱን እንዳገኘን እንበራለን።
በተጨማሪም የማንበርባቸው ሃገሮችም ፈቃድ እንዳገኘን አዋጭነት እያየን እንበራለን በዚህ መንገድ አፍሪካ ውስጥ መዳረሻችንን እና የበረራ ምልልሱን እንጨምራለን።
አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tikvahethiopia
❤1.08K👏55🕊21😡16🙏13😭13🥰9🤔9😱1