TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማንነት የሚያሳይ ፎቶ ይፋ አድርጓል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋልኳቸው በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አውሮፕላን…
#Update
የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።
ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia
የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።
ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ጥንቃቄ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፥ " ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች ማታለያ ወደ ማይናማር እና ታይላንድ ከመጓዝ ሊታቀቡ ይገባል " ሲል አሳስቧል።
ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች በይነ መረብን በመጠቀም በርካታ ዜጎች ችግር ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል።
" ዜጎች ባልተረጋገጡ አማላይ ማስታወቂያዎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው " ብለዋል።
" በጃፓን የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮን የዜጎችን ችግር ለመፍታት ጥረት እያደርገ ነው " ብለው ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎቹ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ተናግረዋል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፥ " ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች ማታለያ ወደ ማይናማር እና ታይላንድ ከመጓዝ ሊታቀቡ ይገባል " ሲል አሳስቧል።
ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች በይነ መረብን በመጠቀም በርካታ ዜጎች ችግር ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል።
" ዜጎች ባልተረጋገጡ አማላይ ማስታወቂያዎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው " ብለዋል።
" በጃፓን የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮን የዜጎችን ችግር ለመፍታት ጥረት እያደርገ ነው " ብለው ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎቹ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ተናግረዋል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia