TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#NBE : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ማክሰኞ የካቲት 18 ቀን 2017 እንደሚያካሂድ አሳውቋል። ለጨረታ የሚቀርበው የውጭ ምንዛሪ መጠን 60 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን፣ ጨረታው ለሁሉም ባንኮች ክፍት እነደሚሆን ገልጿል። @tikvahethiopia
#NBE : ብሔራዊ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት መሰረት፣ የአንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 135 ነጥብ 6185 ብር መሆኑን ይፋ አደረገ።

በዚህ ጨረታ 27 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተሳትፎ መኖሩን ገልጿል።

ባንኩ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ከዋጋና ከውጭ ምንዛሪ መረጋጋት ጋር በሚስማማ መልኩ ተጨማሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ አስታውቋል።

ይህ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የገንዘብ ገበያውን ለማረጋጋትና የውጭ ምንዛሪ ተገኝነትን ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑ ተጠቁሟል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ትግበራ ከገባ ካለፈው ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አንስቶ የአሁን የውጭ ምንዛሬ ሽያጭ ጨረታ ሲወጣ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል ።

በዚህም በመጀመሪያዉ ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ107 ነጥብ 9 ብር ዋጋ መሸጡን እና 27 ባንኮች በጨረታው ላይ መሳተፋቸውን ገልፆ ነበር።
#Capital

@tikvahethiopia