TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

ዛሬ ንጋት 11 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ሰፈራ አካባቢ በደረሰ  የትራፊክ አደጋ 3 ሰዎች መሞታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ፣ ከሟቾች በተጨማሪ 4 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።

አደጋው የደረሰው 7 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ  አንድ ደብል ፒካአፕ ተሽከርካሪ ከቆመ ከባድ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭቶ መሆኑን አስረድተዋል።

የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎችን ከተሽከርካሪው በማውጣት ወደ ህክምና ተቋም እንደላኩ ያወሱት አቶ ንጋቱ ፣ ህይወታቸው ያጡትን ሰዎች አስከሬን ለፖሊስ እንዳስረከቡ፣ ዝርዝር የአደጋ ምክንያት ደግሞ በፖሊስ እየተጣራ እንደሆነ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል፣ ትላንት ምሽት 4 ሰዓት ከ43 ደቂቃ ላይ በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ወረዳ 10 አደይ አበባ አካባቢ በሚገኝ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ላይ እስት አደጋ እንደደረሰ ተናግረዋል።

➡️ አደጋው የደረሰበት ፋብሪካ ፦ DN የጨረቃ ጨርቅ ፋብሪካ
➡️ ሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
➡️ በመጋዘን ውስጥ የነበረ የጥጥ ክምችት ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል።
➡️ የእሳት አደጋው ወደ ፋብሪካው ማሽነሪዎችና ሌሎች ጨርቃ ጨርቆች ላይ ተዛምቶ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ እሳቱን መቆጣጠር ተችሏል።
➡️ አደጋውን ለመቆጣጠር 3 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ፈጅቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በሲዳማ ክልል በወንሾ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱ ወገኖቻችን ቁጥር 9 ደርሷል። 6 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በይርጋለም ሆስፒታል ይገኛሉ። በሌላ በኩል ፤ በዛው ሲዳማ ክልል በቡራ ወረዳ በድንገተኛ ውኃ ሙላት የሁለት ሕጻናት ሕይወት አልፏል። #ኤፍቢሲ @tikvahethiopia
#Sidama

በሲዳማ ክልል፣ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት እና የውሀ ሙላት አደጋ የሞቱ ዜጎች 11 መሆኑን የሲዳማ ክልል አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አበራ ዊላ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ከዚህ ውስጥ ዘጠኙ የሁለት አባወራ ቤተሰቦች ሲሆኑ አንዱ 5 አንዱ ደግሞ 3 ቤተሰቦቻቸዉን ማጣታቸውን ገልጸዋል።

አንድ ግለሰብ ከገበያ ሲመለስ ከተራራ የወረደ ናዳ ላዩ ላይ በማረፉ ለህልፈት እንደዳረገው ገልጸዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ደግሞ በቡራ ወረዳ ወንዝ ሞልቶ ከአቅጣጫው ውጭ በመፍሰስ በአካባቢዉ ያለ ቤት ውስጥ በመግባት 2 ልጆችን ህይወት መቅጠፉን ተናግረዋል።


ከአካባቢው ተራራማነትና ያለማቋረጥ ከዘነበው ዝናብ ጋር ተያይዞ አሁን ላይ ተጨማሪ አደጋዎች ይከሰታሉ ተብሎ ስጋት አለ።

ይህንንም ተከትሎ ከክልሉ የጸጥታ ቢሮ ፣ የጤና ቢሮና ሌሎች ተቋማት የተወጣጣ ግብረሀይል ተቋቁሞ ወደስራ ተገብቷል ብለዋል።

" ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች ናቸው " ተብለው ከተለዩ ስድስት ወረዳዎች የሚኖሩ ዜጎችን የማውጣት ስራ መጀመሩን ጠቁመዋል።

ከቀያቸዉ ከተነሱትን ራቅ ያለ ቦታ ዘመድ ያለው ወደዛ ሲሄድ ሌሎች በት/ቤቶች ፣ በቤተእምነቶችና መሰል ቦታዎች እየተጠለሉ መሆኑን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ስንት ነው ? 💵 US Dollar #CASH Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 #TRANSACTION Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 💷 Pound Sterling #CASH Buying ➡️ 91.8787 Selling ➡️ 93.7162 #TRANSACTION Buying ➡️ 96.2081 Selling ➡️ 98.1322 💶 Euro #CASH…
#ዕለታዊ

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ስንት ነው ?

💵 US Dollar
#CASH
Buying ➡️ 74.7364
Selling ➡️ 76.2311

#TRANSACTION
Buying ➡️ 74.7364
Selling ➡️ 76.2311

💷 Pound Sterling
#CASH
Buying ➡️ 91.5537
Selling ➡️ 93.3848

#TRANSACTION
Buying ➡️ 96.0811
Selling ➡️ 98.0027

💶 Euro
#CASH
Buying ➡️ 80.8797
Selling ➡️ 82.4973

#TRANSACTION
Buying ➡️ 80.8797
Selling ➡️ 82.4973

ተጨማሪ ከላይ ይመልከቱ።

@tikvahethiopia
ግብር ለመክፈል መጉላላት ሳይጠበቅብዎ በቴሌብር ሱፐርአፕ onelink.to/fpgu4m ወይም *127# ባሉበት ቦታ ሆነው በስልክዎ ይክፈሉ!

ሁለቱን የከተማ መስተዳድሮች ጨምሮ የአብዛኛዎቹ የክልል ገቢዎች ግብር በቴሌብር መክፈል ተችሏል፡፡

ሥራን በክብር
ግብርዎን በቴሌብር !

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ !

ለማንኛውም ጥያቄ ወይም አስተያየት በ https://t.iss.one/EthiotelecomChatBot 24/7 ያግኙን!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀደም ሲል በ38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ መነሳቱን በዛሬው ዕለት አሳውቋል። ወደ ውጭ የሚደረግ የካፒታል ሂሳብ ፍስት እንደ በፊቱ የተገደበ እንደሆነ የውጭ ምንዛሪ ገበያው ለገቢ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ነጻ መሆኑንም ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም " ቅድሚያ የማይሰጣቸው " ተብለው የተለዩ 38 ዓይነት ምርቶች ወደ ሀገር…
#Ethiopia : የውጭ ምንዛሬ ገደብ !

" የቤት አውቶሞቢል እና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው እገዳ እንደተጠበቀ ነው " - ገንዘብ ሚኒስቴር

መንግስት ከዚህ ቀደም ባሳለፈው ውሳኔ በተወሰኑ ዕቃዎች ላይ የባንክ የውጭ ምንዛሪ ገደብ እንዲጣል ማድረጉ ይታወሳል፡፡

አሁንም ሙሉ በሙሉ በነዳጅ የሚሰሩ በታሪፍ መፅሐፉ አንቀፅ 87.03 የሚመደቡ ሙሉ በሙሉ ተገጣጥመው የቀረቡ የቤት አውቶሞቢል እና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው እገዳ እንደተጠበቀ ነው ብሏል።

በተቀሩት ዕቃዎች ላይ የተጣለው የውጭ ምንዛሪ ገደብ ውሳኔ ግን ከነማሻሻያው ከሐምሌ 21 ቀን 2016 ጀምሮ የተሻረ መሆኑን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ይህን ያሳወቀው ፦
- ለብሔራዊ ባንክ
- ለገቢዎች ሚኒስቴር
- ለጉምሩክ ኮሚሽን በጻፈው ሰርኩላር ነው።

ትላንትና ብሔራዊ ባንክ በነዳጅ የሚሰሩ ሙሉ በሙሉ ተገጣጥመው የቀረቡ የቤት አውቶሞቢል እና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ያሉበት 38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ መነሳቱን አሳውቆ ነበር።

ብሔራዊ ባንክ ወደ ውጭ የሚደረግ የካፒታል ሂሳብ ፍስት እንደ በፊቱ የተገደበ እንደሆነ የውጭ ምንዛሪ ገበያው ለገቢ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ነጻ መሆኑንም ነበር የገለጸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ተግባራዊ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ መሰረት የግል ባንኮች ዕለታዊ የውጪ ምንዛሬ ተመናቸውን ይፋ እያደረጉ ይገኛሉ። ከላይ የተወሰኑ ባንኮች የዛሬ ዕለታዊ ምንዛሬ ተያይዟል። ከላይ ከተያያዙት የአብዛኞቹ ቀደም ብሎ ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የምንዛሬ ተመን ጋር ተመሳሳይ ነው። በአንጻሩ ሲዳማ ባንክ የውጭ ምንዛሬው ከሌላው ከፍ ያለ ነው። ሲዳማ ባንክ አንዱን የአሜሪካ ዶላር…
በግል ባንኮች ዛሬ የነበረው የውጭ ምንዛሬ ምን ይመስላል ?

ከላይ የተወሰኑ ባንኮች የዛሬ ዕለታዊ የውጭ ምንዛሬ ተያይዟል።

የአብዛኞቹ ባንኮች ጥዋት ንግድ ባንክ ካወጣው ጋር ተመሳሳይ ነው።

አዋሽ ባንክ ከሌሎች ባንኮች በመለየት አንዱን የአሜሪካን ዶላር የ76 ብር ከ2351 ሳንቲም መግዣ የ77 ብር ከ7598 ሳንቲም መሸጫ ቆርጦ ነው የዋለው።

ለዩሮ ደግሞ መግዣው 82 ብር ከ6619 ሳንቲም መሸጫውን ደግሞ 84 ብር ከ3151 ሳንቲም ነው ቆርጦለት የዋለው።


ከትላንት ጀምሮ ተግባራዊ በተደረገው በገበያ ላይ የተስመረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን / Floating exchange rate ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር በሚያደርጉ ነጻ ድርድር የውጭ ምንዛሬ መግዛት እና መሸጥ እንዲችሉ ይፈቅዳል።

#Ethiopia #Floatingexchangerate

@tikvahethiopia
#Amhara

“ የሰዎች ህይወት ላይ ጉዳት አልደረሰም ”- የደሴ ከተማ አስተዳደር

በአማራ ክልል ፣ በደሴ ከተማ አስተዳደር ፣ በአራዳ ክ/ከተማ በተለምዶ “ ጀሜ ” ተብሎ በሚጠራው ሰፈር የመሬት መንሸራተት አደጋ መከሰቱን ከተማው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የከተማ አስተዳደሩ ምን አለ ?

- የመሬት መንሸራተት መጠነኛ የሆነ ጉዳት አድርሷል።

- አደጋው  የተከሰተው ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ/ም ሌሊት በዘነበው ዝናብ አማካኝነት ነው።

- በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ባይኖርም በመተላለፊያ መንገዶች፣ አስፓልት እና በመኖሪያ ቤቶች ላይ የመሰንጠቅ አደጋ ደርሷል።

- አንድ መስጂድ ጉዳት ደርሶበታል። የመሰንጠቅ አደጋ፤ የመፍረስ አደጋ አጋጥሞታል ማለት ነው።

- አስፓልቱ መንገዱ ጉዳት ስለደረሰበት ለጊዜው ለተሽከርካሪዎች ተለዋጭ መንገድ እንዲጠቀሙ ተደርጓል።

- አሁን አደጋ በተከሰበት በአካባቢ ላይ ኮሚቴዎች እና የክፍለ ከተማው አመራሮች ስምሪት ተሰጥቷቸው ክትትል እያደረጉ ነው።

- ለአደጋ ተጋላጭ የአካባቢው ማህበረሰቦች መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው የከተማ አስተዳደሩ ባዘጋጀው ጊዜያዊ ካምፕ እንዲያርፉ ተደርጓል።

- ችግሩ ከዚህ የበለጠ እንዳይከፋ የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም የከተማ አስተዳደሩ ሥራ እየሰራ ነው። የአካባቢው ማህበረሰቡ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሳተፈ ነው።

- አሁን አደጋው በተከሰተበት ቦታ ላይ ባይሆንም፣ በከተማው አቅራቢያ በሚገኝ ሌላ ቦታ ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ አደጋ ተከስቶ ነበር።

ከክረምቱ ጋር ተያይዞ በጎፋ ዞን በደረሰ የመሬት ናዳ በርካቶች መሞታቸው፣ በሌሎች ቦታዎችም በደረሰ ተመሳሳይ ችግር የሰው ህይወት ማለፉ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION🔈 " ከሕጋዊው አካዉንት ውጭ በመጠቀም ድጋፍ የምታሰባስቡ አካላት ከድርጊታችሁ ተቆጠቡ !! " - የጎፋ ዞን አስተዳዳሪ በጎፋ ዞን፣ በገዜ ጎፋ ወረዳ የመሬት ናዳ ከተከሰተ ዛሬ 6ኛ ቀኑን ይዟል። በዚህ የመሬት ናዳ አደጋ የበርካታ ወገኖቻችን ህይወት ማለፉ ይታወሳል። የጠፉ ሰዎችን ፍለጋና አስከሬን በቁፋሮ የማውጣቱ ስራ አሁንም የቀጠለ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተረድቷል። እስካሁንም…
" የ6 ሰዎችን ማግኘት አልተቻለም  "- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል

በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ ኪንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ የደረሰዉን የመሬት መንሸራተት አደጋ በተመለከተ ክልሉ ዛሬ ወቅታዊ መረጃ ሰጥቶ ነበር።

በዚህም መግለጫ " የቀበሌዉን ማህበረሰብ ቁጥር ለመለየት በተደረገ የቤት ለቤት ቆጠራ ስድስት ሰዎች አልተገኙም " ብሏል።

አሁንም አስክሬን ፍለጋዉን እንደቀጠለ ጠቁሟል።

በሌላ በኩል ፤ እስካሁን ከተለያዩ አካላት የተደረገዉ ድጋፍ በገንዘብ 50 ሚሊዮን በአይነት ደግሞ 70 ሚሊዮን እንደደረሰ አመልክቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የዓለም ባንክ የፕሬስ መግለጫ ፦ ዛሬ የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ እና ብድር አጽድቋል። 1 ቢሊየን ዶላሩ ድጋፍ ነው። 500 ሚሊየን ዶላሩ ብድር ነው።

#Ethiopia #WorldBank

@tikvahethiopia
🔈#የወላጆችድምጽ #AddisGlobalAcademy

“ ልጆቻችንን የት እናስመዝግባቸው ? ” - ወላጆች

በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 የሚገኘው “ አዲስ ግሎባል አካዳሚ ‘ለኮሪደር ልማት ያስፈልጋል ’ ” በመባሉ ልጆቻቸውን ሌላ ት/ቤትም ማስመዝገብ እንዳልቻሉ ወላጆችና ትምህርት ቤቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

ሌላ ት/ቤቶች እንዲያስመዘግቡ የተነገራቸው ሰሞኑን እንደሆነ፣ ሌሎች ት/ቤቶች ምዝገባ በማጠናቀቃቸው ልጆቻቸውን ማስመዝገብ እንዳልቻሉ የተማሪ ወላጆች ተናግረዋል።

“ ልጆቻችንን የት እናስመዝግባቸው ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

ውሳኔውን ቀድመው ማወቅ እንደነበረባቸው ገልጸው፣ ምዝገባ እየተገባደደ ባለበት ወቅት ልጆቻቸውን ማስመዝገብ ስላልቻሉ መፍትሄ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገረው የትምህርት ቤቱ በበኩሉ፣ ልማቱን ባይቃወምም ቢያንስ የአንድ ዓመት ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቆ፣ የወላጆች ቅሬታ ትክክል መሆኑን ገልጿል።

አንድ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር አካሌ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ/ም የቦሌ ክፍለ ከተማ አካላት ትምህርት ቤቱ እንደ ት/ቤት እንደማይቀጥል ገልጸው፣ ውሳኔውን ለወላጆች እንዲያሳውቁ ማሳሰቢያ እንደሰጧቸው አስረድተዋል።

ት/ቤቱም ለወላጆች ጥሪ አድርጎ ‘ት/ቤቱ ለልማት ይፈለጋል ባዮቹ’ ራሳቸው ማብራሪያ እንዲሰጧቸው ማድረጉን፣ የተማሪ ወላጆችም ውሳኔው ዱብእዳ ሆኖባቸው ብዙ ጥያቄዎች እንዳነሱ ገልጸዋል።

የወላጆችም ቅሬታ ውሳኔው የአጭር ጊዜ በመሆኑ ልጆቻቸውን ማስመዝገብ ስለማይችሉ እንጂ ልማቱን መቃወም እንዳልተቃወሙ ያስረዱት እኝሁ አካል፣ “ ብዙ ወላጆች እያቀሱና እያዘኑ ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው” ብለዋል።

“ እውነትም ብዙ ትምህርት ቤቶች ምዝገባ ጨርሰዋል። በጥራት ችግርም ፈቃዳቸው የተወሰደባቸው ብዙ ትምህርት ቤቶች ስላሉ ጫናዎች አሉ ” ሲሉም ተናግረዋል።

“ ለምሳሌ ዛሬ አንዷ ወላጅ አንድ ት/ቤት ልጇን ልታስመዘግብ ሂዳ ስታለቅስ አይቷት ዳይሬክተሩ ደወለልኝ። እጅግ ልብ የሚሰብር ነገር ነው የሆነው ” ነው ያሉት።

“ በትምህርት ቤቱ ወደ 1,300 የሚሆኑ ተማሪዎች፣ ከ200 በላይ ሠራተኞች አሉ ” ብለው፣ መንግስት ወደ ሌላ ትምህርት ቤት እንደሚበተኑ ቢገልጽም በተለይ ተማሪዎቹ ላይ የሚያሳድረው የሥነ ልቦና ጉዳት ሊጠን እንደሚገባ አሳስበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባለፉት ቀናት ከመንግስት አካላት ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም። ሙከራው ይቀጥላል።

(ክፍለ ከተማው ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ ምላሹን በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የመጽሐፍ ምረቃ ግብዣ!

የአጫር ታሪኮች ሰብስብ የሆነው የደራሲ የሕይወት እምሻው "ለእርቃን ሩብ ጉዳይ" የተሰኘው #አዲስመጽሐፍ ሐሙስ ሐምሌ 25/ 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11 ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ ከቱሪስት ሆቴል ወረድ ብሎ የሚገኘው ኢክላስ ሕንጻ፣ ዋልያ መጽሐፍት መደብር ይመረቃል።

ባለመኪና ታዳሚዎቻችን መኪናችሁን በአብርሆት ቤተ መጽሐፍት ወይም አምባሳደር የገበያ ማእከል እንድታቆሙ እንመክራለን::

በሰዓት ስለምንጀምር በሰዓት ይገኙልን!

[ ሕይወት እምሻው ]
🔈#የእገዛጥሪ

" ወንድማችንን ታደጉልን ! " - ጓደኞቹ

አቤል ተሾመ (ናቲ ) ከ1 አመት በፊት ( 2015 ሀምሌ ) በClinical Pharmacy ከሐረር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በከፍተኛ መዓረግ መመረቁን ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ይናገራሉ።

ከዛሬ 7 ወር በፊት በድንገኛ  አጣዳፊ የኩላሊት ጉዳት (Acute kidney injury) እና የደም ግፊት ፣ ገለምሶ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ወዲያው ወደ ጥቁር አንበሳ ሪፈር ይባላል።

በጥቁር አንበሳ የውስጥ ደዌ ፣ የኩላሊት ስፔሻሊቲ ንዑስ ክፍል (Nephrology Department ) ላለፉት 7 ወራት የህክምና ክትትል ሲያረግ ጎን ለጎንም ላለፉት 3 ወራት በመቻራ ( ዳሮ ለቡ ) ሆስፒታል በተመረቀበት ሞያ ህዝቡን እያገለገለ ነበር።

ከወር በፊት ግን ህመሙ ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ ክትትል በሚያረግበት ክፍል፣ የኩላሊቶቹ ጉዳት የመጨረሻ ደረጃ End stage renal disease እንደደረሰ እናም የኩላሊት እጥበትና ንቅለ-ተከላ እንደሚያስፈልገው እንደተረገረው አስረድተዋል።

ለዚህም ህክምና ቢያንስ እስከ 2 ሚሊየን እና ከዚያም በላይ እንደሚያስፈልገው ተገልጾለታል።

" አሁን ላይ ወደ ቅዱስ ጷውሎስ ተዘዋውሮ የቅድመ ንቅለ ተከላ ሂደት ጀምሯል " ያሉት ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ " ሆኖም የዚህ ህክምና ወጪ ከአንድ ፋርማሲስት ( Pharmacist ) እና መንግስት ሰራተኛ ቤተሰቡ አቅም በላይ ስለሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በቻለው አቅም እንዲደግፈው " ሲል ተማጽነዋል።

የሒሳብ ቁጥር የአባቱ 1000055784772 Teshome Nigusse (CBE)  እንዲሁም የራሱ 1000055874895 Abel Teshome (CBE) እንደሆነ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM