#Somaliland #US
ዛሬ በሶማሊያ የአሜሪካ አምባሳደር ሶማሌላንድ፣ ሀርጌሳ ነበሩ።
አምባሳደር ሪቻርስ ሪሌይ ፤ ሶማሌላንድ ሀርጌሳ ሄደው ከሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ሙሴ ባሂ አብዲ ጋር መክረዋል።
ከሌሎችም ከፍተኛ የፖለቲካ መሪዎች ፣ የሲቪል ማህበረሰብ መሪዎችና የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጋርም መወያየታቸው ተሰምቷል።
አምባሳደሩ ፤ አሜሪካ በቀጠናው ብልጽግናን እና የዴሞክራሲ ተቋማትን ለመደገፍ የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት እንዳላት አረጋግጠዋል።
ዲፕሎማሲያዊ እና የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት ቀጠናዊ ትብብር እና ውይይትን ያበረታቱም ሲሆን ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር የምርጫ ጊዜን በማክበር አስፈላጊነት ላይ ተወያይተዋል።
ከግሉ ሴክተር መሪዎች ጋር በመገናኘት ከአሜሪካ የንግድ ማህበረሰብ ጋር ግንኙነት እንዴት እንደሚጠናከር መነጋገራቸው ታውቋል።
የነቃ ሲቪል ማህበረሰብ እና ነፃና ሙያዊ ስርዓቱን ያከበረ ፕሬስ አስፈላጊነት ላይ አጽንኦት ሰጥተዋል ተብሏል።
ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂም ከአሜሪካው አምባሳደር ጋር ተገናኝተው መምከራቸውን አሳውቀዋል።
በቀጠናዊ ጉዳዮች ፣ በአፍሪካ ቀንድ ትብብርን ማጎልበት ፣ በምርጫ ጉዳይ ፣ በሶማሌላንድ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል።
በሶማሊያ፣ ሞቃዲሹ ያለው ኤምባሲ የዛሬውን የአምባሳደሩን የሀርጌሳ ጉብኝት በተመለከተ ያሰራጨውን የጽሁፍ መግለጫን አንዳንዶች ' ያልተለመደ ነው ' ብለውታል።
ሀገሪቱ " ሶማሌላንድ፣ ሀርጌሳ ፤ የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት " እያለች መጥራቷ በቋንቋ አጠቃቀም ላይ የታየ ጉልህ ለውጥ ነው ያሉ አልጠፉም።
የአምባሳደሩን ሀርጌሳ ላይ መገኘትን የኮነኑም አሉ። ገለልተኛ አይደሉም ሶማሊያን ይደግፋሉ በሚል።
ሶማሊያውያን ደግሞ በየማህበራዊ ሚዲያ ላይ አሜሪካን መቃወም ይዘዋል።
" መግላጫው ሶማሌላድ ስለ ተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ምንም ያለው ነገር የለም " በማለት እንዲሁም " ሶማሌላንድ የሶማሊያ ግዛት እንደሆነች ሳይገለጽ መቅረቡ ሌላ ነገር ከጀርባው የያዘ ነው " በሚል ነው የተቃወሙ ያሉት።
#Somaliland
#Hargeisa
@tikvahethiopia
ዛሬ በሶማሊያ የአሜሪካ አምባሳደር ሶማሌላንድ፣ ሀርጌሳ ነበሩ።
አምባሳደር ሪቻርስ ሪሌይ ፤ ሶማሌላንድ ሀርጌሳ ሄደው ከሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ሙሴ ባሂ አብዲ ጋር መክረዋል።
ከሌሎችም ከፍተኛ የፖለቲካ መሪዎች ፣ የሲቪል ማህበረሰብ መሪዎችና የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጋርም መወያየታቸው ተሰምቷል።
አምባሳደሩ ፤ አሜሪካ በቀጠናው ብልጽግናን እና የዴሞክራሲ ተቋማትን ለመደገፍ የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት እንዳላት አረጋግጠዋል።
ዲፕሎማሲያዊ እና የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት ቀጠናዊ ትብብር እና ውይይትን ያበረታቱም ሲሆን ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር የምርጫ ጊዜን በማክበር አስፈላጊነት ላይ ተወያይተዋል።
ከግሉ ሴክተር መሪዎች ጋር በመገናኘት ከአሜሪካ የንግድ ማህበረሰብ ጋር ግንኙነት እንዴት እንደሚጠናከር መነጋገራቸው ታውቋል።
የነቃ ሲቪል ማህበረሰብ እና ነፃና ሙያዊ ስርዓቱን ያከበረ ፕሬስ አስፈላጊነት ላይ አጽንኦት ሰጥተዋል ተብሏል።
ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂም ከአሜሪካው አምባሳደር ጋር ተገናኝተው መምከራቸውን አሳውቀዋል።
በቀጠናዊ ጉዳዮች ፣ በአፍሪካ ቀንድ ትብብርን ማጎልበት ፣ በምርጫ ጉዳይ ፣ በሶማሌላንድ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል።
በሶማሊያ፣ ሞቃዲሹ ያለው ኤምባሲ የዛሬውን የአምባሳደሩን የሀርጌሳ ጉብኝት በተመለከተ ያሰራጨውን የጽሁፍ መግለጫን አንዳንዶች ' ያልተለመደ ነው ' ብለውታል።
ሀገሪቱ " ሶማሌላንድ፣ ሀርጌሳ ፤ የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት " እያለች መጥራቷ በቋንቋ አጠቃቀም ላይ የታየ ጉልህ ለውጥ ነው ያሉ አልጠፉም።
የአምባሳደሩን ሀርጌሳ ላይ መገኘትን የኮነኑም አሉ። ገለልተኛ አይደሉም ሶማሊያን ይደግፋሉ በሚል።
ሶማሊያውያን ደግሞ በየማህበራዊ ሚዲያ ላይ አሜሪካን መቃወም ይዘዋል።
" መግላጫው ሶማሌላድ ስለ ተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ምንም ያለው ነገር የለም " በማለት እንዲሁም " ሶማሌላንድ የሶማሊያ ግዛት እንደሆነች ሳይገለጽ መቅረቡ ሌላ ነገር ከጀርባው የያዘ ነው " በሚል ነው የተቃወሙ ያሉት።
#Somaliland
#Hargeisa
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ዴሞክራሲ 👏 #ሶማሌላንድ
" የምርጫ ውጤቱን እንቀበላለን " - ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ
ባለፈው ሳምንት በራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ መደረጉ ይታወሳል።
በከፍተኛ ብልጫም የተቃዋሚው ዋደኒ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ " ኢሮ " ምርጫውን አሸንፈዋል።
በምርጫው የተሸነፉት ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ " የምርጫውን ውጤት እንቀበላለን " ብለዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንትንም " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።
" ባስመዘገቡት ድል እንኳን ደስ አልዎት " ያሉት ፕሬዜዳንት ቢሂ " ሰላማዊና የተረጋጋ የስልጣን ሽግግር እንዲደረግ ለማድረግ የተሟላ ድጋፌን አደጋለሁ " ሲሉ ቃል ገብተዋል።
" የአገልግሎት ዘመንዎ ሰላምን ፣ እድገትን እና ዘላቂ ስኬትን ለሀገራችን እንዲያመጣ እመኛለሁ " ብለዋል።
ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ቢሂ ለህዝቡ ባስተላለፉት መልዕክት " ፕሬዝዳንታችሁ ሆኜ እንዳገለግላችሁ ዕድሉን ስለሰጣችሁኝ አመሰግናለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
" የስልጣን ዘመኔ ማብቂያ ላይ ሆኜ የምለው ነገር ለሀገራችን እድገት ያለኝ ቁርጠኝነት ጸኑ መሆኑን ነው " ሲሉ አክለዋል።
" በአንድነት እና በጋራ ተነስተን ለሶማሌላንድ ብልፅግና እንስራ " ብለዋል።
6ኛው የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት አብዲራህማን ኢሮ " ማንም ተሸናፊ ማንም አሸናፊ የለም ያሸነፈው የሶማሌላንድ ህዝብ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ሶማሌላንድ እራሷን እንደ ሉዓላዊ ሀገር ምትቆጥር ናት። ከሶማሊያ መንግሥት ጋርም ግንኙነት የላትም። ላለፉት በርካታ ዓመታት ራሷን በራሷ እያስተዳደረች ነው።
እጅግ ሰለማዊ ፣ የተረጋጋ ፣ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማድረግ እና ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በማድረግ ትወደሳለች።
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
#Somaliland
@tikvahethiopia
" የምርጫ ውጤቱን እንቀበላለን " - ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ
ባለፈው ሳምንት በራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ መደረጉ ይታወሳል።
በከፍተኛ ብልጫም የተቃዋሚው ዋደኒ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ " ኢሮ " ምርጫውን አሸንፈዋል።
በምርጫው የተሸነፉት ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ " የምርጫውን ውጤት እንቀበላለን " ብለዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንትንም " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።
" ባስመዘገቡት ድል እንኳን ደስ አልዎት " ያሉት ፕሬዜዳንት ቢሂ " ሰላማዊና የተረጋጋ የስልጣን ሽግግር እንዲደረግ ለማድረግ የተሟላ ድጋፌን አደጋለሁ " ሲሉ ቃል ገብተዋል።
" የአገልግሎት ዘመንዎ ሰላምን ፣ እድገትን እና ዘላቂ ስኬትን ለሀገራችን እንዲያመጣ እመኛለሁ " ብለዋል።
ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ቢሂ ለህዝቡ ባስተላለፉት መልዕክት " ፕሬዝዳንታችሁ ሆኜ እንዳገለግላችሁ ዕድሉን ስለሰጣችሁኝ አመሰግናለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
" የስልጣን ዘመኔ ማብቂያ ላይ ሆኜ የምለው ነገር ለሀገራችን እድገት ያለኝ ቁርጠኝነት ጸኑ መሆኑን ነው " ሲሉ አክለዋል።
" በአንድነት እና በጋራ ተነስተን ለሶማሌላንድ ብልፅግና እንስራ " ብለዋል።
6ኛው የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት አብዲራህማን ኢሮ " ማንም ተሸናፊ ማንም አሸናፊ የለም ያሸነፈው የሶማሌላንድ ህዝብ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ሶማሌላንድ እራሷን እንደ ሉዓላዊ ሀገር ምትቆጥር ናት። ከሶማሊያ መንግሥት ጋርም ግንኙነት የላትም። ላለፉት በርካታ ዓመታት ራሷን በራሷ እያስተዳደረች ነው።
እጅግ ሰለማዊ ፣ የተረጋጋ ፣ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማድረግ እና ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በማድረግ ትወደሳለች።
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
#Somaliland
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ግብፅ ? ግብፅ፣ ሶማሊያን እያስታጠቀች ነው። ሶማሊያ የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎች ከግብፅ እንደተሰጧትና ተጨማሪ መሳሪያዎችን በቀጣይነት እንደምትጠብቅ አንድ የሶማሊያ ከፍተኛ ባለሥልጣን ተናግረዋል። ስማቸው ሳይጠቀስ ለቢቢሲ ሶማሊኛ የተናገሩ ባለሥልጣን ባለፉት ቀናት በመርከብ ተጭነው ወደ ሞቃዲሾ ወደብ የደረሱት የጦር መሳሪያዎች እንዳሉ ጠቁመዋል። እነዚህ መሳሪያዎች የሶማሊያ መንግሥት ጦር የሚታጠቃቸው…
" ... ግብፆች መርዳት ከፈለጉ ለምን ፍልስጤሞችንና ሌሎች ዓረብ አገሮችን አይረዱም ? " - አምባሳደር አብዱላሂ መሐመድ ዱአሌ
አምባሳደር አብዱላሂ መሐመድ ዱአሌ ፤ የሶማሌላንድ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ልዩ መልዕክተኛ ግብፅ በቀጣናው ስለምታደርገው እንቅስቃሴ ምን አሉ ?
(ለሪፖርተር ጋዜጣ ከተናገሩት የተወሰደ)
" የግብፅ እንቅስቃሴ በግልጽ ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ ግብፅ ወደ ሶማሊያ መሣሪያ እያሠራጨች ነው፡፡
በመሣሪያ እየታመሰ ባለ ቀጣና ውስጥ ሌላ መሣሪያ እንዲመጣ አንፈልግም፣ በሶማሊያ እያንዳንዱ ግዛት መሣሪያ ተበትኗል፡፡ ነገር ግን ሶማሊያውያን መሣሪያ የተራቡ አይደሉም፡፡
ሶማሊያን ለመጠበቅ በርካታ አገሮች ማለትም ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ኡጋንዳና ሌሎች ልጆቻቸውን ገብረዋል፣ ውድ ቤተሰቦቻቸውን፣ ገብረዋል፡፡ አሁን በድንገት ግብፅ መጥታ አለሁላችሁ ብትል አይሠራም፡፡
ሶማሊያ የምትባል አገር መጀመሪያ የራሷን የቤት ሥራ ትሥራ፣ ቤቷን ትጠብቅ፡፡
ሶማሌላንዶች ከሕዝብ ገንዘብ ሰብስበን በጀት መድበን አገር እያስተዳደርን ያለን ሰላማዊ አገር ነን፡፡ ከማንም ለምነን አይደለም አገር የምንመራው፡፡
ሶማሊያን ተመልከት ማን እንደሚደግፋቸው፡፡ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ዕርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ናቸው፡፡
የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ኢትዮጵያንም ሶማሌላንድንም ከማን ጋር ስምምነት መፈጸም እንዳለባቸው ሊነግሯቸው አይገባም፡፡
ግብፆች መርዳት ከፈለጉ ለምን ፍልስጤሞችንና ሌሎች ዓረብ አገሮችን አይረዱም ? አሁን ግብፅ መሣሪያና ወታደር በአውሮፕላን እየጫኑ እያመጡ ነው፡፡
ይህ የግብጽ ጣልቃ ገብነት ትልቅ ሥጋት ነው፡፡ ለሶማሌላንድ ጭምር አደጋ ነው፡፡ ይህን ሥጋት ለአፍሪካ ኅብረትና ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ፣ እንዲሁም ለኢጋድ አሳውቀናል፡፡ "
#Somaliland #Egypt
@tikvahethiopia
አምባሳደር አብዱላሂ መሐመድ ዱአሌ ፤ የሶማሌላንድ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ልዩ መልዕክተኛ ግብፅ በቀጣናው ስለምታደርገው እንቅስቃሴ ምን አሉ ?
(ለሪፖርተር ጋዜጣ ከተናገሩት የተወሰደ)
" የግብፅ እንቅስቃሴ በግልጽ ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ ግብፅ ወደ ሶማሊያ መሣሪያ እያሠራጨች ነው፡፡
በመሣሪያ እየታመሰ ባለ ቀጣና ውስጥ ሌላ መሣሪያ እንዲመጣ አንፈልግም፣ በሶማሊያ እያንዳንዱ ግዛት መሣሪያ ተበትኗል፡፡ ነገር ግን ሶማሊያውያን መሣሪያ የተራቡ አይደሉም፡፡
ሶማሊያን ለመጠበቅ በርካታ አገሮች ማለትም ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ኡጋንዳና ሌሎች ልጆቻቸውን ገብረዋል፣ ውድ ቤተሰቦቻቸውን፣ ገብረዋል፡፡ አሁን በድንገት ግብፅ መጥታ አለሁላችሁ ብትል አይሠራም፡፡
ሶማሊያ የምትባል አገር መጀመሪያ የራሷን የቤት ሥራ ትሥራ፣ ቤቷን ትጠብቅ፡፡
ሶማሌላንዶች ከሕዝብ ገንዘብ ሰብስበን በጀት መድበን አገር እያስተዳደርን ያለን ሰላማዊ አገር ነን፡፡ ከማንም ለምነን አይደለም አገር የምንመራው፡፡
ሶማሊያን ተመልከት ማን እንደሚደግፋቸው፡፡ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ዕርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ናቸው፡፡
የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ኢትዮጵያንም ሶማሌላንድንም ከማን ጋር ስምምነት መፈጸም እንዳለባቸው ሊነግሯቸው አይገባም፡፡
ግብፆች መርዳት ከፈለጉ ለምን ፍልስጤሞችንና ሌሎች ዓረብ አገሮችን አይረዱም ? አሁን ግብፅ መሣሪያና ወታደር በአውሮፕላን እየጫኑ እያመጡ ነው፡፡
ይህ የግብጽ ጣልቃ ገብነት ትልቅ ሥጋት ነው፡፡ ለሶማሌላንድ ጭምር አደጋ ነው፡፡ ይህን ሥጋት ለአፍሪካ ኅብረትና ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ፣ እንዲሁም ለኢጋድ አሳውቀናል፡፡ "
#Somaliland #Egypt
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somaliland
አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ሶማሊለንድ ፤ ሀርጌሳ ገብተዋል።
አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት በሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ለተመራ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ልዑክ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አቶ አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ በአቶ ሙስጠፋ የተመራውን ልዑክ በጽ/ቤታቸው ተቀብለዋቸዋል።
ልዑኩ በሀርጌሳ ቆይታው ተመራጩ አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አቶ አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ በዓለ ሲመት ላይ ይሳተፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሶማሊ ክልል ቴሌቪዥን ዘግቧል።
#Ethiopia #Somaliland
@tikvahethiopia
አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ሶማሊለንድ ፤ ሀርጌሳ ገብተዋል።
አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት በሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ለተመራ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ልዑክ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አቶ አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ በአቶ ሙስጠፋ የተመራውን ልዑክ በጽ/ቤታቸው ተቀብለዋቸዋል።
ልዑኩ በሀርጌሳ ቆይታው ተመራጩ አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አቶ አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ በዓለ ሲመት ላይ ይሳተፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሶማሊ ክልል ቴሌቪዥን ዘግቧል።
#Ethiopia #Somaliland
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Somaliland
የአዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ (ኢሮ) በዓለ ሲመት በሀርጌሳ እየተከናወነ ይገኛል።
በበዓለ ሲመቱ ላይ የቀድሞ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ፣ የቀድሞ ፕሬዜዳንት ዳሂር ሪያሌ ካሂን፣ የአሜሪካው አምባሳደር ሪቻርድ ሪሌይን ጨምሮ የሀገራት ዲፕሎማቶች ተወካዮች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት ሙስጠፋ ሙሁመድ በዚሁ የበዓለ ሲመት ስነ ስርዓት ላይ ለመገኘት ትላንት ልዑካቸውን ይዘው ሀርጌሳ መግባታቸው ይታወሳል።
ከሶማሊያ ተነጥላ ላለፉት በርካታ አመታት ራሷን የምታስተዳድረው ሶማሊላንድ በሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲሁም ደግሞ በዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ምርጫ በግንባር ቀደምነት ትታወቃለች።
ቪድዮ፦ አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሮዜዳንት እና የቀድሞው ፕሬዜዳንት በፈገግታ ተሞልተው ወደ አዳራሽ ሲገቡ።
@tikvahethiopia
የአዲሱ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዱረህማን መሀመድ አብዱላሂ (ኢሮ) በዓለ ሲመት በሀርጌሳ እየተከናወነ ይገኛል።
በበዓለ ሲመቱ ላይ የቀድሞ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ፣ የቀድሞ ፕሬዜዳንት ዳሂር ሪያሌ ካሂን፣ የአሜሪካው አምባሳደር ሪቻርድ ሪሌይን ጨምሮ የሀገራት ዲፕሎማቶች ተወካዮች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት ሙስጠፋ ሙሁመድ በዚሁ የበዓለ ሲመት ስነ ስርዓት ላይ ለመገኘት ትላንት ልዑካቸውን ይዘው ሀርጌሳ መግባታቸው ይታወሳል።
ከሶማሊያ ተነጥላ ላለፉት በርካታ አመታት ራሷን የምታስተዳድረው ሶማሊላንድ በሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲሁም ደግሞ በዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ምርጫ በግንባር ቀደምነት ትታወቃለች።
ቪድዮ፦ አዲሱ የሶማሊላንድ ፕሮዜዳንት እና የቀድሞው ፕሬዜዳንት በፈገግታ ተሞልተው ወደ አዳራሽ ሲገቡ።
@tikvahethiopia