TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ኦዲት በ11 መስሪያ ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ብር #ምንም ማስረጃ ሳይኖር ወጪ ተደርጓል። በ2015 የበጀት ዓመት መ/ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ወጪ ማድረጋቸውን / በአግባቡ መጠቀማቸውን ፣ ተገቢ ማስረጃ መቅረቡንና ሂሳቡ በትክክል መመዝገቡን ለማጣራት ኦዲት ተደርጓል። በዚህም ፥ ምንም አይነት ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገበ ክፍያ / ሂሳብ ተገኝቷል። በ11 መ/ቤቶች 43.5…
#ኦዲት #ኢትዮጵያ
(ከ2015 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት)
➡️ የበጀት አጠቃቀም ፦
ኦዲት በተደረጉ መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በስራ ላይ ያዋሉት ሂሳብ ሲነጻጸር ከበጀት በላይ ወጪ የተደረገበት ፣ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል።
በ20 መ/ቤቶች በልዩ ልዩ የሂሳብ መደቦች በደንቡ መሰረት #ሳያስፈቅዱ ለእያንዳንዱ የበጀት ኮድ ከተደለደለው በላይ ወጪ የሆነ ሂሳብ ከመደበኛው በጀት ብር 524. 7 ሚሊዮን ፣ ከውስጥ ገቢ 288.9 ሚሊዮን ፣ ከካፒታል በጀት 489.4 ሚሊዮን በድምሩ 1.3 ቢሊዮን ብር ተገኝቷል።
በኮድ ከተደለደለው በጀት በላይ ውጭ ያደረጉ ዋና ዋና መ/ቤቶች ፦
🟠 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 322.5 ሚሊዮን
🟠 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ተጠሪ ተቋማቱ 267.9 ሚሊዮን
🟠 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 173.2 ሚሊዮን
🟠 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 125.1 ሚሊዮን
🟠 የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 109.5 ሚሊዮን
🟠 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ 91.3 ሚሊዮን
🟠 አምቦ ዩኒቨርሲቲ 83.3 ሚሊዮን
🟠 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 75.1 ሚሊዮን
ሁለት መስሪያ ቤቶች ደግሞ 9.7 ሚሊዮን ብር በጀት ስለመኖሩ ሳይረጋገጥ / ሳይፈቀድ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኘቷል።
➡️ ከደንብ እና መመሪያ ውጭ የተከፈለ ፦
በ30 መ/ቤቶች ብር 16 ሚሊዮን 470 ሺህ ከደንብና መመሪያ ውጭ አላግባብ ተከፍሏል።
ዋና ዋናዎቹ መ/ቤቶች ፦
🔴 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን
🔴 የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት 2 ሚሊዮን 889 ሺህ
🔴 ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2 ሚሊዮን 42 ሺህ
🔴 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ 1 ሚሊዮን 156 ሺህ
➡️ በመስሪያ ቤት ለሌሉና ከስራ ገበታ ለተሰናበቱ ሰራተኞች የተከፈለ ደመወዝ ፦
በ16 መስሪያ ቤቶች በመስሪያ ቤት ለሌሉ እና ከስራ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ብር 485 ሺህ 183 ከ56 ሳንቲም ደመወዝ ተከፍሎ ተገኝቷል።
➡️ በበልጫ አላግባብ የተከፈለ ወጪ ፦
በ32 መ/ቤቶች እና በ9 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በተለያዩ የግንባታና ግዥዎች 4.9 ሚሊዮንና ለውሎ አበልና ሌሎች ክፍያዎች 57.6 ሚሊዮን በድምር 62.6 በብልጫ ተከፍሎ ተገኝቷል።
➡️ የግዥ አዋጅ ደንብና መመሪያ ያልተከተሉ ግዥዎች ፦
በ73 መ/ቤቶች እና በ15 ቅ/ጽቤቶች ብር 2 ቢሊዮን 199 ሚሊዮን የመንግስት ግዥ አዋጅ ደንብ እና መመሪያን ሳይከተል ግዥ ተፈጽሟል።
° በጨረታ መግዛት ሲገባው ያለጨረታ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 1.8 ቢሊዮን ብር
° መስፈርት ሳይሟላ በውስን ጨረታ የተገዛ 104.3 ሚሊዮን ብር
° ግልጽ ጨረታ መውጣት ሲገባው በዋጋ ማወዳደሪያ የተፈጸመ 96.1 ሚሊዮን ብር
° የዋጋ ማወዳደሪያ ሳይሰበሰብ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 13.8 ሚሊዮን ብር
° ሌሎች የግዥ ሂደት ያልተከተሉ 134.6 ሚሊዮን ዋና ዋና ናቸው።
ዋና ዋና መስሪያ ቤቶች (ደንብና መመሪያ ሳይከተሉ ግዥ የፈጸሙ)፦
⚫ ገቢዎች ሚኒስቴር በዋናው መ/ቤትና በቅርንጫፍ ፅ/ቤት 1.4 ቢሊዮን
⚫ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት 91 ሚሊዮን
⚫ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 65.5 ሚሊዮን
⚫ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 62.9 ሚሊዮን
⚫ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ 57.1 ሚሊዮን
⚫ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 37.4 ሚሊዮን
⚫ የጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት እና በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት 34 ሚሊዮን
➡️ በአማካሪ መሃንዲሳ ሳይረጋገጥ የተከፈለ ክፍያ ፦
የግንባታ ክፍያ #በአማካሪ_መሃንዲስ ተረጋግጠው መከፈላቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ኦዲት በ2 መ/ቤቶች 170 ሚሊዮን 394 ሺህ በአማካሪ መሃንዲስ የክፍያ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሳይቀርብ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኝቷል።
👉 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 169.7 ሚሊዮን ብር ከፍሎ ተገኝቷል።
➡️ የተከፋይ ሂሳብ ፦
በ14 መ/ቤቶች 1.7 ቢሊዮን ብር በተከፋይ ሂሳብ ተይዞ ተገኝቷል። ለማን እንደሚከፈል እንኳን ተለይቶ አይታወቅም።
የተከፋይ ሂሳብ ለባለመብት መለየት ካልቻሉ መስሪያ ቤቶች ፦
🔵 የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 1.5 ቢሊዮን
🔵 የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 131.8 ሚሊዮን
🔵 ማዕድን ሚኒስቴር 29.9 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
(ከ2015 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት)
ኦዲት በተደረጉ መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በስራ ላይ ያዋሉት ሂሳብ ሲነጻጸር ከበጀት በላይ ወጪ የተደረገበት ፣ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል።
በ20 መ/ቤቶች በልዩ ልዩ የሂሳብ መደቦች በደንቡ መሰረት #ሳያስፈቅዱ ለእያንዳንዱ የበጀት ኮድ ከተደለደለው በላይ ወጪ የሆነ ሂሳብ ከመደበኛው በጀት ብር 524. 7 ሚሊዮን ፣ ከውስጥ ገቢ 288.9 ሚሊዮን ፣ ከካፒታል በጀት 489.4 ሚሊዮን በድምሩ 1.3 ቢሊዮን ብር ተገኝቷል።
በኮድ ከተደለደለው በጀት በላይ ውጭ ያደረጉ ዋና ዋና መ/ቤቶች ፦
🟠 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 322.5 ሚሊዮን
🟠 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ተጠሪ ተቋማቱ 267.9 ሚሊዮን
🟠 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 173.2 ሚሊዮን
🟠 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 125.1 ሚሊዮን
🟠 የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 109.5 ሚሊዮን
🟠 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ 91.3 ሚሊዮን
🟠 አምቦ ዩኒቨርሲቲ 83.3 ሚሊዮን
🟠 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 75.1 ሚሊዮን
ሁለት መስሪያ ቤቶች ደግሞ 9.7 ሚሊዮን ብር በጀት ስለመኖሩ ሳይረጋገጥ / ሳይፈቀድ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኘቷል።
በ30 መ/ቤቶች ብር 16 ሚሊዮን 470 ሺህ ከደንብና መመሪያ ውጭ አላግባብ ተከፍሏል።
ዋና ዋናዎቹ መ/ቤቶች ፦
🔴 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን
🔴 የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት 2 ሚሊዮን 889 ሺህ
🔴 ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2 ሚሊዮን 42 ሺህ
🔴 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ 1 ሚሊዮን 156 ሺህ
በ16 መስሪያ ቤቶች በመስሪያ ቤት ለሌሉ እና ከስራ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ብር 485 ሺህ 183 ከ56 ሳንቲም ደመወዝ ተከፍሎ ተገኝቷል።
በ32 መ/ቤቶች እና በ9 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በተለያዩ የግንባታና ግዥዎች 4.9 ሚሊዮንና ለውሎ አበልና ሌሎች ክፍያዎች 57.6 ሚሊዮን በድምር 62.6 በብልጫ ተከፍሎ ተገኝቷል።
በ73 መ/ቤቶች እና በ15 ቅ/ጽቤቶች ብር 2 ቢሊዮን 199 ሚሊዮን የመንግስት ግዥ አዋጅ ደንብ እና መመሪያን ሳይከተል ግዥ ተፈጽሟል።
° በጨረታ መግዛት ሲገባው ያለጨረታ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 1.8 ቢሊዮን ብር
° መስፈርት ሳይሟላ በውስን ጨረታ የተገዛ 104.3 ሚሊዮን ብር
° ግልጽ ጨረታ መውጣት ሲገባው በዋጋ ማወዳደሪያ የተፈጸመ 96.1 ሚሊዮን ብር
° የዋጋ ማወዳደሪያ ሳይሰበሰብ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 13.8 ሚሊዮን ብር
° ሌሎች የግዥ ሂደት ያልተከተሉ 134.6 ሚሊዮን ዋና ዋና ናቸው።
ዋና ዋና መስሪያ ቤቶች (ደንብና መመሪያ ሳይከተሉ ግዥ የፈጸሙ)፦
⚫ ገቢዎች ሚኒስቴር በዋናው መ/ቤትና በቅርንጫፍ ፅ/ቤት 1.4 ቢሊዮን
⚫ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት 91 ሚሊዮን
⚫ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 65.5 ሚሊዮን
⚫ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 62.9 ሚሊዮን
⚫ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ 57.1 ሚሊዮን
⚫ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 37.4 ሚሊዮን
⚫ የጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት እና በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት 34 ሚሊዮን
የግንባታ ክፍያ #በአማካሪ_መሃንዲስ ተረጋግጠው መከፈላቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ኦዲት በ2 መ/ቤቶች 170 ሚሊዮን 394 ሺህ በአማካሪ መሃንዲስ የክፍያ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሳይቀርብ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኝቷል።
👉 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 169.7 ሚሊዮን ብር ከፍሎ ተገኝቷል።
በ14 መ/ቤቶች 1.7 ቢሊዮን ብር በተከፋይ ሂሳብ ተይዞ ተገኝቷል። ለማን እንደሚከፈል እንኳን ተለይቶ አይታወቅም።
የተከፋይ ሂሳብ ለባለመብት መለየት ካልቻሉ መስሪያ ቤቶች ፦
🔵 የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 1.5 ቢሊዮን
🔵 የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 131.8 ሚሊዮን
🔵 ማዕድን ሚኒስቴር 29.9 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ኢትዮ_ቴሌኮም
ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠባበቂያ በ 39% ቅናሽ!
እስከ 12 ወራት ድረስ በተራዘመ የክፍያ አማራጭ እጅግ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠባበቂያ ለማግኘት ወደ ድርጅት አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን ጎራ ይበሉ!
ለበለጠ መረጃ፡ https://bit.ly/48btdOJ ይጎብኙ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠባበቂያ በ 39% ቅናሽ!
እስከ 12 ወራት ድረስ በተራዘመ የክፍያ አማራጭ እጅግ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠባበቂያ ለማግኘት ወደ ድርጅት አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን ጎራ ይበሉ!
ለበለጠ መረጃ፡ https://bit.ly/48btdOJ ይጎብኙ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#Mekelle
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የመቐለ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገልጿል።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ዛሬ ነው።
በዚህም በጊዜያዊነት የጀመራቸው አገልግሎቶች ፦
☑️ ፓስፖርት ማደስ፣
☑️ የጠፋ ፓስፖርት መተካት፣
☑ የተበላሸ ወይ እርማት የመስጠት አገልግሎቶች እንደሆነም ተገልጿል።
የመቐለ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ፅህፈት ቤት ተወካይ ክንፈሚካኤል ረዳሀኝ ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ከጦርነቱ በፊት በፅህፈት ቤቱ በርካታ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር አመልክተዋል።
በጦርነቱ ሁሉም አገልግሎት ተቋርጦ እንደነበር አስታውሰዋል።
ከፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት በኃላ ቢዘገይም የፓስፓርት እድሳት አገልግሎት አሁም መሰጠት እንደተጀመረ ገልጸው ፤ " በመላ ትግራይ የሚገኙ የፓስፓርት እድሳት ፈላጊዎች በአካል መምጣት ሳይስፈልጋቸው ባሉበት ሆኖው በኦንላይን መገለግል ይችላሉ " ብለዋል።
ተገልጋዮች ወደ (መቐለ) ፅ/ቤቱ መምጣት ያለባቸው ሁሉም ነገር ጨርሰው ማህተም ለማስመታት ብቻ እንደሆነ ጠቁመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የመቐለ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገልጿል።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ዛሬ ነው።
በዚህም በጊዜያዊነት የጀመራቸው አገልግሎቶች ፦
☑️ ፓስፖርት ማደስ፣
☑️ የጠፋ ፓስፖርት መተካት፣
☑ የተበላሸ ወይ እርማት የመስጠት አገልግሎቶች እንደሆነም ተገልጿል።
የመቐለ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ፅህፈት ቤት ተወካይ ክንፈሚካኤል ረዳሀኝ ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ከጦርነቱ በፊት በፅህፈት ቤቱ በርካታ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር አመልክተዋል።
በጦርነቱ ሁሉም አገልግሎት ተቋርጦ እንደነበር አስታውሰዋል።
ከፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት በኃላ ቢዘገይም የፓስፓርት እድሳት አገልግሎት አሁም መሰጠት እንደተጀመረ ገልጸው ፤ " በመላ ትግራይ የሚገኙ የፓስፓርት እድሳት ፈላጊዎች በአካል መምጣት ሳይስፈልጋቸው ባሉበት ሆኖው በኦንላይን መገለግል ይችላሉ " ብለዋል።
ተገልጋዮች ወደ (መቐለ) ፅ/ቤቱ መምጣት ያለባቸው ሁሉም ነገር ጨርሰው ማህተም ለማስመታት ብቻ እንደሆነ ጠቁመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኦዲት #ኢትዮጵያ (ከ2015 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት) ➡️ የበጀት አጠቃቀም ፦ ኦዲት በተደረጉ መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በስራ ላይ ያዋሉት ሂሳብ ሲነጻጸር ከበጀት በላይ ወጪ የተደረገበት ፣ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል። በ20 መ/ቤቶች በልዩ ልዩ የሂሳብ መደቦች በደንቡ መሰረት #ሳያስፈቅዱ ለእያንዳንዱ የበጀት ኮድ ከተደለደለው በላይ…
#ኦዲት
ያልተሰራበት በጀት !
ገንዘብ ሚኒስቴር እና ጤና ሚኒስቴር የተመደበላቸውን በቢሊዮን የሚቆጠር በጀት ስራ ላይ ካላዋሉ ተቋማት ዋነኞቹ መሆናቸው ተሰምቷል።
በ2015 በጀት መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ስራ ላይ ማዋላቸውንና መጠቀማቸውን ለማጣራት ኦዲት ሲደረግ በሂሳብ ኮዶች ከተደለደለው በጀት ከ10% በላይ #ያልተጠቀሙበትን ብቻ ተወስዶ 101 መስሪያ ቤቶች ፦
° መደበኛ በጀት 5.3 ቢሊዮን
° ከውስጥ ገቢ 207.6 ሚሊዮን
° ከካፒታል ብር 13.7 ቢሊዮን
በድምሩ 19.2 ቢሊዮን ብር #ያልተሰራበት_በጀት ተገኝቷል።
የተደለደለው በጀት ስራ ላይ እንዲውል #ካላደረጉት መስሪያ ቤቶች መካከል ፦
🔴 የገንዘብ ሚኒስቴር 8 ቢሊዮን ብር
🔴 ጤና ሚኒስቴር 1.9 ቢሊዮን ብር
🔴 የግብርና ሚኒስቴር 1.2 ቢሊዮን ብር
🔴 የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 818.4 ሚሊዮን
🔴 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 727 ሚሊዮን ብር
🔴 ትምህርት ሚኒስቴር 724.2 ሚሊዮን ብር
🔴 የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 613.6 ሚሊዮን ብር ... ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
#በጀት_ተፈቅዶ እያለ አለመጠቀም የታሰቡ ስራዎች እንዳይሰሩ ፤ መስሪያ ቤቱ አላማውን እንዳያሳካ ሊያደርግ ስለሚችል በበጀት ዝግጅት እና አጠቃቀም ላይ ጥንቃቄ እንዲደረግ ሲል የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት አሳስቧል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ያልተሰራበት በጀት !
ገንዘብ ሚኒስቴር እና ጤና ሚኒስቴር የተመደበላቸውን በቢሊዮን የሚቆጠር በጀት ስራ ላይ ካላዋሉ ተቋማት ዋነኞቹ መሆናቸው ተሰምቷል።
በ2015 በጀት መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ስራ ላይ ማዋላቸውንና መጠቀማቸውን ለማጣራት ኦዲት ሲደረግ በሂሳብ ኮዶች ከተደለደለው በጀት ከ10% በላይ #ያልተጠቀሙበትን ብቻ ተወስዶ 101 መስሪያ ቤቶች ፦
° መደበኛ በጀት 5.3 ቢሊዮን
° ከውስጥ ገቢ 207.6 ሚሊዮን
° ከካፒታል ብር 13.7 ቢሊዮን
በድምሩ 19.2 ቢሊዮን ብር #ያልተሰራበት_በጀት ተገኝቷል።
የተደለደለው በጀት ስራ ላይ እንዲውል #ካላደረጉት መስሪያ ቤቶች መካከል ፦
🔴 የገንዘብ ሚኒስቴር 8 ቢሊዮን ብር
🔴 ጤና ሚኒስቴር 1.9 ቢሊዮን ብር
🔴 የግብርና ሚኒስቴር 1.2 ቢሊዮን ብር
🔴 የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 818.4 ሚሊዮን
🔴 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 727 ሚሊዮን ብር
🔴 ትምህርት ሚኒስቴር 724.2 ሚሊዮን ብር
🔴 የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 613.6 ሚሊዮን ብር ... ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
#በጀት_ተፈቅዶ እያለ አለመጠቀም የታሰቡ ስራዎች እንዳይሰሩ ፤ መስሪያ ቤቱ አላማውን እንዳያሳካ ሊያደርግ ስለሚችል በበጀት ዝግጅት እና አጠቃቀም ላይ ጥንቃቄ እንዲደረግ ሲል የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት አሳስቧል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#Amahra
በአማራ ክልል ፤ ምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህናን ወረዳ ፤ ጅጋ ከተማ እሁድ እለት ከቀኑ 11:30 ገደማ ሲቪል ሰዎች ላይ ግድያ ተፈጽሟል ሲሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
የአካባቢዎች ነዋሪዎች በርካታ ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይል መገደላቸውን ከሟቾቹ ውስጥ ከባንክ ሰራተኞች እንዳሉበት ጠቁመዋል።
እንደ ነዋሪዎቹ ቃል ፥ አንድ ባለ አንድ ጋቢና መኪና የመንግስት የጸጥታ ኃይሎችን ጭኖ ከደምበጫ ወደ ፍኖተሰላም ሲጓዝ ጅጋ ፀደይ ባንክ አካባቢ በ ' ፋኖ ' ታጣቂዎች የደፈጣ ጥቃት ተፈጽሞበታል።
ታጣቂዎቹ ጥቃቱን አድርሰው ወደጫካ ካፈገፈጉ በኃላ ከጥቃቱ በኃላ የደረዱ ሌሎች የጸጥታ ኃይሎች የሲቪል ሰዎች ግድያ መፈጸቸውን ነዋሪዎች አመልክተዋል።
አንድ ነዋሪ ፥ " ድንገት ምንም ሳናስበው ነው አካባቢው በተኩስ የተናወጠው ፤ ከጫካ የመጡ የፋኖ ኃይሎች ናቸው፤ አንደኛውን ፓትሮል ላይ ጥቃት ፈጸሙ ከኋላ የሚከተል ፓትሮል ነበር ' ጎህ ' የሚባል መናፈሻ ነገር አለ እዛ ተኩስ ነበር። ብዙ ሰው ተገደለ። አንድ የአቢሲንያ ማናጀር፣ አንድ የአዋሽ ባንክ አካውንታት ፤ አንድ ምንም የማትናገር ዝናሽ የምትባል ሴት አጠቃላይ 13 ሰዎች መጠጥ የሚጠጣ፣ በቦታው የነበረ ተመቷል የመዝናኛ / የእረፍት ቀን ነበር። የሞቱት ከጫካው ኃይል ወይም ከተማው ውስጥ ካለው የጸጥታ ኃይል ገለልተኛ የስራ ሰው ነው " ብለዋል።
ሌላ ነዋሪ ፥ " የተኩስ ልውውጥ ነበር። መጀመሪያ ' ፋኖ ' ነበር የተኮሰው ፤ አጋጣሚ ሆኖ በፓትሮሉ ላይ ከነበሩት የሰራዊት አባላት አንድ ስናይፐር ተኳሽ አንድ ጥቁር ክላሽ የያዘ ልጅ ከመኪናው ፈጥነው ዘለው እነሱ ብቻ ነው የቀሩት ፤ ከዛ ከኃላ ሲመጣ የነበረ ሌላ የጸጥታ ኃይል ' ጎህ ' የሚባል የመዝናኛ አካባቢ የመንግሥት ሰራተኞች፣ የባንክ ሰራተኞች ፣ መምህራን የነበሩበት እዛ ያገኙትን በአሰቃቂ ሁኔታ በብሬን ገድለዋል። የሟቾች ቁጥር ከ20 ይበልጣል ነው እንደሰማነው። የአብዛኞቹ በየአካባቢያቸው ስርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል " ሲሉ ተናግረዋል።
የጅጋ ከተማን እና የአካባቢውን ህዝብ ወክለው የተመረጡት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ አበባው ደሳለው ፥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተጠናቋል በተባለበት በሲቪል ሰዎች ላይ ግድያ መፈጸሙ የሚያሳዝን ነው ብለዋል።
ከዚህ ቀደምም በሌሎችም ከተማዎች በሲቪል ሰዎች ላይ ስለሚደረስ ግድያ በተለያዩ መድረኮች መናገራቸውን አስታውሰው " ግን ሃሳባችን ሳይሰማ ቀርቶ ይሄ ሆኗል " ብለዋል።
" በጣም የሚያሳዝነው አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተጠናቋል የሽግግር ፍትህ ይኖራል ምክክር ኮሚሽን ስራውን ይሰራል ከታጣቂዎች ጋር ድርድር እና ውይይት ይደረጋል በተባለበት ሰዓት ይህ መፈጠሩ ያሳዝናል " ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ አበባ በዕለቱ ተገድለዋል ያሏቸውን የ13 ሰዎች ስም ዝርዝር በእጃቸው እንዳለ ይህን ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ መላካቸውን አሳውቀዋል።
የም/ቤት አባሉ ፥ " በክልሉ በመንግስት የጸጥታ ኃይል እና በፋኖ መካከል የሚደረገው ውጊያ ህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ ሁለቱም ኃይሎች ወደ ድርድር ሊመጡ ይገባል " ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የባህር ዳር ቅርንጫፍ ሁኔታው እየተጣራ ነው ብሏል።
የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ስለ ጉዳዩ አስተያየታቸውን ለማድመጥ በተደጋጋሚ ስልክ ቢደወለም አላነሱም።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል ፤ ምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህናን ወረዳ ፤ ጅጋ ከተማ እሁድ እለት ከቀኑ 11:30 ገደማ ሲቪል ሰዎች ላይ ግድያ ተፈጽሟል ሲሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
የአካባቢዎች ነዋሪዎች በርካታ ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይል መገደላቸውን ከሟቾቹ ውስጥ ከባንክ ሰራተኞች እንዳሉበት ጠቁመዋል።
እንደ ነዋሪዎቹ ቃል ፥ አንድ ባለ አንድ ጋቢና መኪና የመንግስት የጸጥታ ኃይሎችን ጭኖ ከደምበጫ ወደ ፍኖተሰላም ሲጓዝ ጅጋ ፀደይ ባንክ አካባቢ በ ' ፋኖ ' ታጣቂዎች የደፈጣ ጥቃት ተፈጽሞበታል።
ታጣቂዎቹ ጥቃቱን አድርሰው ወደጫካ ካፈገፈጉ በኃላ ከጥቃቱ በኃላ የደረዱ ሌሎች የጸጥታ ኃይሎች የሲቪል ሰዎች ግድያ መፈጸቸውን ነዋሪዎች አመልክተዋል።
አንድ ነዋሪ ፥ " ድንገት ምንም ሳናስበው ነው አካባቢው በተኩስ የተናወጠው ፤ ከጫካ የመጡ የፋኖ ኃይሎች ናቸው፤ አንደኛውን ፓትሮል ላይ ጥቃት ፈጸሙ ከኋላ የሚከተል ፓትሮል ነበር ' ጎህ ' የሚባል መናፈሻ ነገር አለ እዛ ተኩስ ነበር። ብዙ ሰው ተገደለ። አንድ የአቢሲንያ ማናጀር፣ አንድ የአዋሽ ባንክ አካውንታት ፤ አንድ ምንም የማትናገር ዝናሽ የምትባል ሴት አጠቃላይ 13 ሰዎች መጠጥ የሚጠጣ፣ በቦታው የነበረ ተመቷል የመዝናኛ / የእረፍት ቀን ነበር። የሞቱት ከጫካው ኃይል ወይም ከተማው ውስጥ ካለው የጸጥታ ኃይል ገለልተኛ የስራ ሰው ነው " ብለዋል።
ሌላ ነዋሪ ፥ " የተኩስ ልውውጥ ነበር። መጀመሪያ ' ፋኖ ' ነበር የተኮሰው ፤ አጋጣሚ ሆኖ በፓትሮሉ ላይ ከነበሩት የሰራዊት አባላት አንድ ስናይፐር ተኳሽ አንድ ጥቁር ክላሽ የያዘ ልጅ ከመኪናው ፈጥነው ዘለው እነሱ ብቻ ነው የቀሩት ፤ ከዛ ከኃላ ሲመጣ የነበረ ሌላ የጸጥታ ኃይል ' ጎህ ' የሚባል የመዝናኛ አካባቢ የመንግሥት ሰራተኞች፣ የባንክ ሰራተኞች ፣ መምህራን የነበሩበት እዛ ያገኙትን በአሰቃቂ ሁኔታ በብሬን ገድለዋል። የሟቾች ቁጥር ከ20 ይበልጣል ነው እንደሰማነው። የአብዛኞቹ በየአካባቢያቸው ስርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል " ሲሉ ተናግረዋል።
የጅጋ ከተማን እና የአካባቢውን ህዝብ ወክለው የተመረጡት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ አበባው ደሳለው ፥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተጠናቋል በተባለበት በሲቪል ሰዎች ላይ ግድያ መፈጸሙ የሚያሳዝን ነው ብለዋል።
ከዚህ ቀደምም በሌሎችም ከተማዎች በሲቪል ሰዎች ላይ ስለሚደረስ ግድያ በተለያዩ መድረኮች መናገራቸውን አስታውሰው " ግን ሃሳባችን ሳይሰማ ቀርቶ ይሄ ሆኗል " ብለዋል።
" በጣም የሚያሳዝነው አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተጠናቋል የሽግግር ፍትህ ይኖራል ምክክር ኮሚሽን ስራውን ይሰራል ከታጣቂዎች ጋር ድርድር እና ውይይት ይደረጋል በተባለበት ሰዓት ይህ መፈጠሩ ያሳዝናል " ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ አበባ በዕለቱ ተገድለዋል ያሏቸውን የ13 ሰዎች ስም ዝርዝር በእጃቸው እንዳለ ይህን ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ መላካቸውን አሳውቀዋል።
የም/ቤት አባሉ ፥ " በክልሉ በመንግስት የጸጥታ ኃይል እና በፋኖ መካከል የሚደረገው ውጊያ ህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ ሁለቱም ኃይሎች ወደ ድርድር ሊመጡ ይገባል " ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የባህር ዳር ቅርንጫፍ ሁኔታው እየተጣራ ነው ብሏል።
የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ስለ ጉዳዩ አስተያየታቸውን ለማድመጥ በተደጋጋሚ ስልክ ቢደወለም አላነሱም።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
ከዳሰነች ወረዳ ታማሚ አሳፍሮ ለተሻለ ሕክምና ወደ ጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሲጓዝ የነበረ አምቡላንስ ተገልብጦ የ3 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ 4 ሰዎች ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው፡፡
አደጋው የደረሰው በደቡብ ኦሞ ዞን በና ፀማይ ወረዳ አርጎ ቀበሌ " አርጎ ቁልቁለት " አካባቢ ነው።
ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታ የሕክምና ዕርዳታ እያገኙ ይገኛሉ።
የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
መረጃው የዳሰነች ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ነው።
@tikvahethiopia
አደጋው የደረሰው በደቡብ ኦሞ ዞን በና ፀማይ ወረዳ አርጎ ቀበሌ " አርጎ ቁልቁለት " አካባቢ ነው።
ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታ የሕክምና ዕርዳታ እያገኙ ይገኛሉ።
የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
መረጃው የዳሰነች ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የታገተችው ታዳጊ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ታግታ ከተወሰደች በኃላ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት የታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ እስከአሁን እንቆቅልሽ ሆኖ ቀጥሏል። መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታው " ዓዲ ማሕለኻ " ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች ዛሬ ግንቦት 10/2016 ዓ.ም 60 ቀናት አስቆጥራለች። ታጋች…
#Update
ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተገድላ ተገኘች።
ለ91 ቀናት ታግታ የተሰወረችው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተገድላ ተገኝታለች።
ለወላጆችዋ ዛሬ መርዶ ተነግሯቸዋል።
የአስከሬን የአሸኛነት ስነ-ሰርዓት ዛሬ በአቡነ አረጋዊ ቤተክርስትያን ዓድዋ እንደሚፈፀም ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
በተማሪ ማህሌት ተኽላይ ግድያ ዙሪያ ፓሊስ የሚሰጠው መረጃ ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል።
በተማሪ ማህሌት ተኽላይ እገታና ስወራ ጉደይ የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ለወራት ተከታታይ መረጃ ሲያቀርብ እንደነበር አይዘነጋም።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተገድላ ተገኘች።
ለ91 ቀናት ታግታ የተሰወረችው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተገድላ ተገኝታለች።
ለወላጆችዋ ዛሬ መርዶ ተነግሯቸዋል።
የአስከሬን የአሸኛነት ስነ-ሰርዓት ዛሬ በአቡነ አረጋዊ ቤተክርስትያን ዓድዋ እንደሚፈፀም ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
በተማሪ ማህሌት ተኽላይ ግድያ ዙሪያ ፓሊስ የሚሰጠው መረጃ ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል።
በተማሪ ማህሌት ተኽላይ እገታና ስወራ ጉደይ የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ለወራት ተከታታይ መረጃ ሲያቀርብ እንደነበር አይዘነጋም።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተገድላ ተገኘች። ለ91 ቀናት ታግታ የተሰወረችው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተገድላ ተገኝታለች። ለወላጆችዋ ዛሬ መርዶ ተነግሯቸዋል። የአስከሬን የአሸኛነት ስነ-ሰርዓት ዛሬ በአቡነ አረጋዊ ቤተክርስትያን ዓድዋ እንደሚፈፀም ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በተማሪ ማህሌት ተኽላይ ግድያ ዙሪያ ፓሊስ የሚሰጠው መረጃ ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል። በተማሪ ማህሌት…
ማህሌት ተኽላይ !
መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ " ዓዲ ማሕለኻ " ከሚባል ስፍራ ነው ታግታ የተሰወረችው።
የታገተችው ቋንቋ ወደምትማርበት ትምህርት ቤት ስትሄድ ነው።
ባጃጅ ይዘው በመጡ ሰዎች ነበር የታገተችው።
ማህሌት ተኽላይ ታግታ ከተወሰደች በኃላ አጋቾች ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ ወላጅ አባቷ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረው ነበር።
የዓድዋ ከተማ ፓሊስም ፥ ከሳምንታት በኃላ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎች እንዳሉ ገልጾ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ አድዋ ድረስ ተጉዞ የማህሌት ወላጅ አባት ተኽላይ ግርማይን አነጋግሮ በነበረበት ወቅት ቤተሰቦች ምን ያህል የከፋ ሀዘን እና ጭንቀት ላይ እንደወደቁ መመልከት ችሎ ነበር።
አባት ተኽላይና መላ ቤተሰብ ላለፉት ወራት እንቅልፍ ሚባል አላዩም።
የወለደ ሰው የልጅ ፍቅር በወላጅ የሚያሳደረው ነገር ያውቀዋልና 3 ወር ያህል እንቅልፍ ሳያገኙ ነው የቆዩት።
አቶ ተኽላይ ግርማይ እና መላው ቤተሰቦች ከዛሬ ነገ የልጃቸውን በህይወት ቤት መምጣት ሲጠብቁ ዛሬ ጥዋት ግን ልጃቸው በህይወት እንደሌለች መርዶ ተነግሯቸዋል።
#ዓድዋ
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ " ዓዲ ማሕለኻ " ከሚባል ስፍራ ነው ታግታ የተሰወረችው።
የታገተችው ቋንቋ ወደምትማርበት ትምህርት ቤት ስትሄድ ነው።
ባጃጅ ይዘው በመጡ ሰዎች ነበር የታገተችው።
ማህሌት ተኽላይ ታግታ ከተወሰደች በኃላ አጋቾች ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ ወላጅ አባቷ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረው ነበር።
የዓድዋ ከተማ ፓሊስም ፥ ከሳምንታት በኃላ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎች እንዳሉ ገልጾ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ አድዋ ድረስ ተጉዞ የማህሌት ወላጅ አባት ተኽላይ ግርማይን አነጋግሮ በነበረበት ወቅት ቤተሰቦች ምን ያህል የከፋ ሀዘን እና ጭንቀት ላይ እንደወደቁ መመልከት ችሎ ነበር።
አባት ተኽላይና መላ ቤተሰብ ላለፉት ወራት እንቅልፍ ሚባል አላዩም።
የወለደ ሰው የልጅ ፍቅር በወላጅ የሚያሳደረው ነገር ያውቀዋልና 3 ወር ያህል እንቅልፍ ሳያገኙ ነው የቆዩት።
አቶ ተኽላይ ግርማይ እና መላው ቤተሰቦች ከዛሬ ነገ የልጃቸውን በህይወት ቤት መምጣት ሲጠብቁ ዛሬ ጥዋት ግን ልጃቸው በህይወት እንደሌለች መርዶ ተነግሯቸዋል።
#ዓድዋ
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ማህሌት ተኽላይ ! መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ " ዓዲ ማሕለኻ " ከሚባል ስፍራ ነው ታግታ የተሰወረችው። የታገተችው ቋንቋ ወደምትማርበት ትምህርት ቤት ስትሄድ ነው። ባጃጅ ይዘው በመጡ ሰዎች ነበር የታገተችው። ማህሌት ተኽላይ ታግታ ከተወሰደች በኃላ አጋቾች ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ ወላጅ አባቷ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረው ነበር። የዓድዋ ከተማ ፓሊስም ፥ ከሳምንታት…
#Update #Adwa
ከ3 ወር በላይ ታግታ አድራሻዋ ጠፍቶ ዛሬ በግፍ መገደለዋ የተረጋገጠው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ አጋቾችዋ ገድለው እንደቀበሯት ማመናቸውን ፓሊስ አስታወቀ።
የትግራይ ማእከላይ ዞን ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ሃላፊ ኮማንደር ፀጋይ ኣስፍሃ ዛሬ ለ104.4 የመቐለ ኤፍኤም በስልክ በሰጡት ቃል ፥ በእገታው እና ግድያው የተጠረጠሩ መያዛቸውን ገልጸዋል።
ግለሰቦቹ ለፓሊስ በሰጡት ቃል ተማሪ ማህሌትን ገድለው በዓድዋ የፓንአፍሪካ ዩኒቨርስቲ ሊገነባበት የመሰረተ ደንጋይ የተጣለበት ቦታ መቅበራቸውን ቦታው ድረስ በመምራት አሳይተዋል ፤ አምነዋል ብለዋል።
ተጠርጣሪዎቹ ማህሌትን እንዴት እንዳገቷት ፣ አግተው ወዴት እንደወሰዱዋት ፣ እንዴት ገድለው እንደቀበርዋትና አስከሬንዋ የተቀበረበት ቦታ ጭምር በዝርዝር ለፓሊስ ማሰየታቸውን ኮማንደሩ በሰጡት መረጃ አረጋግጠዋል።
የተማሪ ማህሌት ተኽላይ አስከሬን ከተቀበረበት ጉድጓድ የማውጣት ስነ-ሰርዓት በመከናወን ላይ መሆኑ የገለፁት ኮማንደር ፀጋይ ፤ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ተጨማሪ ምርመራ ይደረግበታል ብለዋል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
@TikvahEthiopiaTigrigna
ከ3 ወር በላይ ታግታ አድራሻዋ ጠፍቶ ዛሬ በግፍ መገደለዋ የተረጋገጠው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ አጋቾችዋ ገድለው እንደቀበሯት ማመናቸውን ፓሊስ አስታወቀ።
የትግራይ ማእከላይ ዞን ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ሃላፊ ኮማንደር ፀጋይ ኣስፍሃ ዛሬ ለ104.4 የመቐለ ኤፍኤም በስልክ በሰጡት ቃል ፥ በእገታው እና ግድያው የተጠረጠሩ መያዛቸውን ገልጸዋል።
ግለሰቦቹ ለፓሊስ በሰጡት ቃል ተማሪ ማህሌትን ገድለው በዓድዋ የፓንአፍሪካ ዩኒቨርስቲ ሊገነባበት የመሰረተ ደንጋይ የተጣለበት ቦታ መቅበራቸውን ቦታው ድረስ በመምራት አሳይተዋል ፤ አምነዋል ብለዋል።
ተጠርጣሪዎቹ ማህሌትን እንዴት እንዳገቷት ፣ አግተው ወዴት እንደወሰዱዋት ፣ እንዴት ገድለው እንደቀበርዋትና አስከሬንዋ የተቀበረበት ቦታ ጭምር በዝርዝር ለፓሊስ ማሰየታቸውን ኮማንደሩ በሰጡት መረጃ አረጋግጠዋል።
የተማሪ ማህሌት ተኽላይ አስከሬን ከተቀበረበት ጉድጓድ የማውጣት ስነ-ሰርዓት በመከናወን ላይ መሆኑ የገለፁት ኮማንደር ፀጋይ ፤ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ተጨማሪ ምርመራ ይደረግበታል ብለዋል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
@TikvahEthiopiaTigrigna