TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፎቶ፦ " አልታወቁም " በተባሉ የታጣቂ ኃይሎች በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ፤ በቦሰት ወረዳ ቤተ ክህነት የመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን መቃጠሉን የተዋሕዶ ሚዲያ አገልግሎት አሳውቋል።

" ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች  " ተፈፅሟል የተባለው ይህ የመቃጠል ተግባር ትናንት ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ መፈፀሙ ተመላክቷል።

" በቦታው ላይ የተለያዩ አካላት በተደጋጋሚ ጊዜ ዛቻና ማስፈራሪያ ሲያደርጉ ቆይቷል " ያለው ዘገባው ትላንንት ሙሉ በሙሉ ንዋዬ ቅድሳቱ የተቃጠለ ሲሆን የቤተ መቅደሱ የውስጥና የውጭ ክፍል ጉዳት ያደረሰ ከፍተኛ ቃጠሎ መድረሱ ተገልጿል።

ጉዳዩ ላይ ሀገረ ስብከቱ አስፈላጊውን የማጣራት ሥራ እየሠራ ይገኛል ተብሏል።

#TMC

@tikvahethiopia
#Canada #StudentVisa

ካናዳ በእ.ኤ.አ. 2024 የዓለም አቀፍ ተማሪዎች ቪዛን (የምትቀበላቸውን ተማሪዎች ቁጥር) ትቀንሳለች። ይህም ለሁለት ዓመታት ይቀጥላል።

ሀገሪቱ በ2024 ዕድገቷን ለማረጋጋት ስትል የምትቀበለው 360,000 ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን ብቻ እንደሆነ ይፋ አድርጋለች።

የካናዳ ኢሚግሬሽን ስደተኞችና ዜግነት ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የዓለም አቀፍ ተማሪዎች ቁጥር እየጨመረ ነው ብሏል።

አንዳንድ ተቋሞች ገቢያቸውን ለማሳደግ በሚል የቅበላ መጠናቸው በከፍተኛ ሁኔታ ጨምረዋል እንዲሁም ብዙ ተማሪዎች ለስኬታማነት ተገቢውን ድጋፍ ሳያገኙ ወደ ካናዳ እየመጡ ነው ሲል አስረድቷል።

ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ለካናዳ ማኀበራዊ፣ ኢኮኖሚያና ባህላዊ ለውጥ አንድ አካል ናቸው ሲል ገልጿል።

ይሁን እንጂ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች ወደ ካናዳ መምጣት ፦
* በጤና አገልግሎት
* በቤት አቅርቦት ላይ #ጫና እየፈጠረ መጥቷል ነው የተባለው።

በመሆኑም፣ " ተማሪዎችን ከሕገ ወጦች ለመከላከልና የሀገሪቱን የሕዝብ ቁጥር ተመጣጣኝ ለማድረግ አዲስ ሕግ አስፈልጓል " ነው ያለው፡፡

የካናዳ ኢሚግሬሽን ስደተኞችና ዜግነት ሚኒስትር ማርክ ሚለር፣ " አዲሱ ሕግ ለሁለት ዓመት ይቆያል። በ2024 የ360,000 ማመልከቻ ብቻ እንቀበላለን " ብለዋል፡፡

" ይህም ከባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በ35% ይቀንሳል" ብለዋል ሚለር፡፡

" ከመጠን በላይ እየጨመረ የመጣው የዓለም አቀፍ ተማሪዎች ቁጥር በካናዳ ያልተረጋጋ እድገት እያሳዬ " ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ይህን ችግር ለመቅረፍም ከየግዛት አስተዳዳሪዎች ጋር መምከራቸውን አስታውቀዋል፡፡

ካናዳ እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያን ለትምህርት እንዲሁም ለስራ ከሚመርጧትና ለመሄድም ጥረት ከሚያደርጉባት ሀገራት አንዷ እንደሆነች ይታወቃል።

More : https://t.iss.one/ThiqaMediaEth/185

@tikvahethiopia @thiqamediaeth
#Gebeya #Mastercard

መስራት በገበያ ኩባንያና በማስተርካርድ ፋውንዴሽን ትብብር የተጀመረ የሥራ ፈጠራ ፕሮግራም ነው።

ቢዝነስ ኖሯችሁ እገዛ የምትፈልጉ ካላችሁ መስራት የሚባለውን ፕሮግራም በመቀላቀል ዘርፈ ብዙ ድጋፍ ማግኘት ትችላላችሁ።

በተለይ ቢዝነሳችሁ ችግር ፈቺ ሀሳብ ካለው ፣ ለብዙ ሰው የስራ እድል መፍጠር የሚችል ከሆነ ወይም አሰሪ እና ሰራተኛ የሚያገናኝ ከሆነ ዛሬውኑ ይቀላቀሉን።

ፕሮግራሙን በመቀላቀል የፋይናንስ ፣ የህግ ፣ የገበያ ትስስር ፣ እና ተጨማሪ ድጋፎችን በማግኘት ቢዝነስዎን ወደ ላቀ ከፍታ ይውሰዱ።

ከጥር 22 በፊት በማመልከት መስራትን ይቀላቀሉ https://mesirat.org/apply/
#CBE
ግብርዎን በሲቢኢ ብር መተግበሪያ እንዴት ይከፍላሉ?
=======
ለአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ እና ሶማሌ ክልል ግብር ከፋዮች

ከግብር ሰብሳቢው ተቋም
• የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣
• የገንዘብ መጠን እና
• የክፍያ ማዘዣ ቁጥር የያዘ መልእክት ሲደርስዎት

የሲቢኢ ብር መተግበሪያዎን በመክፈት ቅደም ተከተሉን ጠብቀው ግብርዎን በቀላሉ ይክፈሉ፡፡

የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለማውረድ፡

• Android፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• IOS፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
***
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!  
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh  
• Telegram፡- https://t.iss.one/combankethofficial
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#DStv

የተለያዩ ምርጥ የልጆች ቻናሎችን እና ሌሎች መዝናኛዎችን ከ290 ብር ጀምሮ በዲኤሲቲቪ

የዲኤስቲቪ ዲኮደር በ1,199 ብር ከ1 ወር ነፃ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የዲኤስቲቪ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
#ኮኮሜሎን

ካለፈው የታሕሳስ ወር አንስቶ በተለያዩ የውጭ ሀገራት ያሉ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች እና የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴን የሚቃወሙ አካላት "ኔትፍሊክስ" እንዳይታይ የአድማ ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።

"ኔትፍሊክስ" ላይ የአድማ ጥሪ እያደረጉ ያሉት ባለፈው ዓመት (እኤአ) መጨረሻ ለእይታ በበቃ በአንድ የልጆች ፊልም ላይ #ግብረሰዶምን ለማስፋፋት ዓላማ ያለው ትዕይንት አለበት በሚል ነው።

ኮኮሜሎን ሌን (CoComelon Lane) በተሰኘው የልጆች ፊልም ኢፒሶድ ላይ አንድ ህፃን ልጅ የዳንሰኛ አጭር ቀሚስ ለብሶ ሲጨፍር መታየቱ ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን ተቺዎች ይህ የተደረገበትን መንገድ "መጥፎና ሰይጣናዊ" ሲሉ ነው የገለጹት።

CoComelon lane ለልጆች የተሰራ የNetflix ተከታታይ ፊልም ነው። በኃላም ከ1 ወር በፊት በዩትዩብ ላይ ተጭሮ በሚሊዮኖች ታይቷል።

በዚሁ ፊልም በሲዝን 1፤ ኢፒሶድ 8 ላይ አንድ ኒኮ የተባለ ህፃን ልጅ (2 አባቶች እንዳሉት ተደርጎ የተገለፀ-ይህ ግብረሰዶማውያን አባቶች እንዳሉት የሚያሳይ ተደርጎ ተወስዷል) ከቤተሰቦቹ ጋር ለሚነሳው ፎቶ ምን መልበስ እንዳለበት ለመወሰን ተቸግሮ ይታያል።

በዚህም ወቅት የኒኮ አባቶች ተደርገው የተሳሉት ሁለቱ ገፀባህርያት " ስለ አንተ የምናውቀው ነገር ቢኖር ተነስተህ መደነስ እንደምትወድ ነው " እያሉ ይዘፍናሉ።

ከዚያም ኒኮ የዳንሰኛ አጭር ቀሚስ ለብሶ እና ዘውድ ከአናቱ ላይ አድርጎ መደነስ ይጀምራል።

የኒኮ አባት ተብሎ ከተገለፁት አንዱ፤ " ምን መምረጥ እንዳለብህ እርግጠኛ ካልሆንክ ማድረግ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ አስብ። አንተ እራስህን ብቻ ሁን " እያለ ይዘፍንለታል።

ከዚያም ኒኮ "እኔ ራሴን ብቻ ልሁን?" ብሎ ይጠይቃል ካዛም አባት ተብየው ገፀባህሪ " አዎ! " ሲል ይመልስለታል።

ይህ ንግግር ህፃኑ ልጅ "የማንም ተፅእኖ ሳይኖርብህ #በፈለከው_መንገድ እራስህን ሁን" የሚል ይዘት ያለው መልዕክት ለማስተላለፍ እንደሆነ ጉዳዩ ያሳሰባቸው ተቆርቋሪች ይገልጻሉ።

ትዕይቱን "ጥፎና ሰይጣናዊ" ሲሉም ገልጸው ዋነኛው አላማው ህፃናትን ማበላሸት፣ ምንም በማያውቁ ህፃናት ላይ ግብረሰዶምን ማስፋፋት ነው ብለዋል።

የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴና ሰዎቹን አጥብቀው የሚያወግዙት እነዚህ ተቆርቃሪዎች፤ "ትዕይንቱ ህፃናት በለጋ እድሜያቸው ስለግብረሰዶም እና ስለፆታ ማስቀየር "እንዲዘጋጁ" እያደረገ የሚሄድ ነው ብለውታል።

በዚህ ምክንያት ይህንን ለህፃናት እንዲታይ እያሰራጨው "ኔትፍሊክስ"ን ሰዎች እንዳያዩ የአድማ ጥሪ እያቀረቡ ናቸው።

ምንም እንኳን ፊልሙ በህዳር ወር ውስጥ የወጣ ቢሆን ከወጣበት ጊዜ አንስቶ ተቆርቋሪዎች ወላጆች ልጆቻቸውን ከመሰል አደገኛ ይዘት ካላቸው መልዕክቶች እንዲጠብቁ ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።

ይህ "CoComelon" የተባለውና ለህፃናት በተለያዩ ርዕሶች እየተዘጋጀ የሚቀርበው ካርቱን ፊልም በዓለም አቅፍ ደረጃ ብዙ እይታ ያለው ነው። ብዙ ወላጆችም ለልጆቻቸው ይከፍቱላቸዋል።

ወላጆች ዘመኑ ያለበትን ሁኔታ በመረዳት ልጆች እንዲያዩ የሚያደርጉትን ማንኛውንም ነገር በቅድሚያ መገምገም፣ ጥሩነው መጥፎ፣ ከጀርባ ምን ይዟል የሚለው መመርመር አለባቸው። ዝም ብሎ ልጅ ስላስቸገረ ስልክ መስጠትንም ተገቢ አይደለም።

ከዚህ ባለፈ ልጆች በሃይማኖት ተኮትኩተው ፣ የማህበረሰቡን ባህል፣ ስርዓት አክብረው በትምህርታቸው፣ በሃይማኖታቸው ጠንካራ ሆነው እንዲያድጉና እንዲኖሩ በተገቢው አቃጣጫ መምራት ይጠበቅባቸዋል።

ኢትዮጵጵያውያን የቴክ ሰዎችም የሀገራችን ህፃናት ወደሌላ እንዳይሳቡ በሀገር ባህል፣ ስርዓት የተቀረፁ የማስተማሪያ ካርቱን ፊልሞችን በብዛት ማዘጋጀት አለባቸው። #ቲክቫህ

@tikvahethiopia
#ትግራይ #ኢሮብ

በትግራይ ክልልና ኤርትራ አዋሳኝ ድንበር ላይ የሚኖረው የኢሮብ ብሔረሰብ ተወላጆች ፣ የሚኖሩባቸው አካባቢዎች ለሁለት በመከፈላቸው ማኅበረሰቡ ለድርቅ ፣ ለስደትና ለተለያዩ በደሎች እየታገለጠ ይገኛል።

ነዋሪዎች ምን አሉ ?

- ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ አሁንም ድረስ ከብሔረሰቡ 8 ቀበሌዎች ውስጥ ፦
* እንዳልገዳ፣
* ወርዓትስ፣
* ዓገረለኩማና ዳያዓሊቴና በተባሉ 4 ቀበሌዎች የኤርትራ ሠራዊት ይገኛል።

- ኢሮብን በዓዲግራት በኩል ከተቀሩት የትግራይ ክልል ከተሞች ጋር የሚያገናኘው መንገድ አገልግሎት አይሰጥም።

- በወረዳው ከባድ ረሃብ ነው ያለው። የዕርዳታ እህል ለማግኘት ምዝገባ አለ። ግን በስንት አንዴ የምግብ ድጋፍ ቢገኝም የተወሰነ እንጂ የሰውን ሕይወት ሊያተርፍ የሚችል ነገር አይገኝም።

- በጊዜያዊ አስተዳደሩ ሥር በሚገኙት 4 ቀበሌዎች ትምህርት ተቋርጧል። በተቀሩት የኤርትራ ሠራዊት ተቆጣጥሯቸው ባሉት አራቱ ደግሞ ሕፃናት #በኤርትራ_ካሪኩለም እንዲማሩ እየተደረገ ነው።

- ከጦርነቱ በፊት የብሔረሰቡ ቁጥር 32 ሺሕ ነበር። አሁን ኅብረተሰቡ በተለይ ወጣቱ ወደ ስደት እየሄደና ብሔረሰቡም በተደራረቡበት ችግሮች ምክንያት ቁጥሩ እየተመናመነ እየጠፋ ነው።

የኢሮብ ወረዳ አስታዳዳሪ ኢያሱ ምስግና ምን አሉ ?

* ወደ 60 በመቶ የሚሆነው የብሔረሰቡ ግዛት በኤርትራ ሠራዊት ሥር ነው። ሁለቱን ቀበሌዎች ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሯቸው ይገኛል። የተቀሩት ሁለቱ ውስጥ ደግሞ በከፊል ሰፍሮ ይገኛል።

* ከዓዲግራት ወደ ኢሮብ የሚወስደው መንገድ በኤርትራ ሠራዊት ወድሟል። አሁንም በሠራዊቱ ተዘግቶ ይገኛል። ይህ ዋና መንገድ በመዘጋቱ ትራንስፖርት ችግር ነው። ቀበሌዎችን ውስጥ ለውስጥ ለማገናኘት ከጦርነቱ አራት ዓመታት በፊት ቀድሞ ግንባታቸው ተጀምሮ ባልተጠናቀቁ መስመሮች ነበር የሚኬደው አሁን ይኼም አስቸጋሪ እየሆነ ነው።

* ኢሮብ ወረዳ ዘንድሮ ከባድ ድርቅ ያጋጠመው አጋጥሞታል። እስካሁን ድረስም ምንም ዓይነት ዝናብ አልተገኘም። የምግብና የውኃ እጥረት በሰውና በእንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ነው።

* ዕርዳታ በሰብዓዊ ድርጅቶችና አልፎ አልፎ በመንግሥት ይቀርብ ነበር። በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅት የምግብ ዕርዳታ ካቀረበ ከአንድ ዓመት በላይ ሆኖታል። በወቅቱ ድጋፉ ለአራት ሺሕ ሰዎች ነበር የቀረበው።

* መንግሥትም አልፎ አልፎ የሚልክልን የአደጋ ጊዜ የምግብ ድጋፍ ነበር፡፡ እሱም ከጊዜው ቆይታ አንፃርና ከሕዝቡ ቁጥር ጋር የሚመጣጠን አልነበረም።

* የመድኃኒት እጥረት ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ነው። በረሃብ አደጋ ውስጥ ወድቀው ያሉ ብዙ ታማሚዎች የመድኃኒት ዕጦቱ ተደምሮ ሕይወታቸውን እያሳጣቸው ነው።

* የኢሮብ ብሔረሰብ የድርቅ ሁኔታ ብቻ ሳይሆን እንደ ብሔረሰብ እየጠፋ ነው። ቋንቋው፣ ባህሉና ወጉ ተጠብቆ በራሱ አካባቢ መኖር ሲገባው በስደት፣ በረሃብ፣ በድርቅና በጠላት ተበታትኖ እንዳይጠፋ ዓለም አቀፍ ሕግጋት መተግበር አለባቸው፣ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትም መከበር አለበት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሪፖርተር ጋዜጣ መውሰዱን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
#FoodandAgricultureOrganization #UN

የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ  የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያ ተሸለሙ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ ሽልማት የተሰጣቸው ዛሬ በጣልያን፤ ሮም ከተማ ነው።

በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት (FAO) ፤ ሮም ውስጥ ባሰናዳው ዝግጅት ዶ/ር ዐቢይ ፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያደረጉ ላለው ጥረት የከበረውን አግሪኮላ ሜዳልያ እንዳበረከተላቸው ተነግሯል።

የፋኦ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ኩ ዶግዩ ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፋኦ ከፍተኛ ሽልማት ለሆነው አግሪኮላ ሜዳልያ ሽልማት በመብቃታቸውን " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።

ይህ ሽልማት መሪዎች እና ሌሎችም የዓለማችን እውቅ ሰዎች የምግብ ዋስትናናን ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ድህነትን ለመቀነስ ለሚያደርጉት የተሳካ ጥረት የሚሰጥ እንደሆነ ጠቁመዋል።

በዚህም የአግሪኮላ ሜዳሊያ ለጠ/ ሚኒስትሩ እየተበረከተው ፦
* በኢትዮጵያ ገጠርና ኢኮኖሚ ልማት ላይ ላበረከቱት አስተዋፅኦ
* በተለይም " በስንዴ፤ ምግብ እራስን መቻል ፕሮግራም " ባደረጉት የግል ድጋፍ
* በኢትዮጵያ አረንጓዴ ሌጋሲ (Green Legacy) ስራ መሆኑን አስረድተዋል።

ከዚህ ባለፈ ዋና ዳይሬክተሩ " ባለፉት 5 አመታት ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለችውን አስደናቂ እድገት ተመልክቻለሁ " ማለታቸው ተነግሯል።

ይህ ሊሆን የቻለው " በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጡ ውጤታማ፣ ተጠያቂነት ያለውና የተረጋጋ አመራር ነው " ያሉት የፋኦ ዋና ዳይሬክተር ፤ ተመልክቼዋለሁ ያሉት እድገት የተመዘገበው " ባለፉት ዓመታት በነበሩ አስቸጋሪ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ውስጥ ነው ፤... ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን እንደ አህጉር ለአፍሪካም ይልቅ መልዕክት ነው " ማለታቸው ተሰምቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በበኩላቸው የተሰጣቸውን ሽልማትና እና እውቅናን ተከትሎ ባሰራጩት መልዕክት ምስጋና አቅርበው ፤ " ከፍ ያለ ጠቀሜታ ባላቸውና የኢንደስትሪ ግብዓት በሆኑ የግብርና ምርቶች ላይ ማተኮራችን ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እያስገኘልን ይገኛል። የምግብ ሉዓላዊነት ጉዟችንን በፅናት እናስቀጥላለን " ብለዋል።

የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያን በተሸለሙበት ወቅት የፋኦ አመራሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ እና የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተው ነበር ተብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከፋኦ ድረገፅ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
Africa-Italy

የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ጣልያን፣ ሮም ገብተዋል።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድም ሮም ይገኛሉ።

የሀገራት መሪዎች ፣ እና የመንግሥታት ተወካዮች በሮም እየተሳብሰቡ የሚገኙ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ ዛሬ እና ነገ ለሚካሄድ የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ነው።

የኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ ግንኙነታቸው ሻክሯል የተባለው ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መሪዎቻቸው በአንድ መድረክ በአካል ሲገኙ ይህ የመጀመሪያው ይሆናል።

ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ እና ሶማሌለንድ መካከል ከተፈረመው ስምምነት ጋር በተያያዘ ስለ " ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ " ግንኙነት እንዲሁም ስለ " ሱዳን ጦርነት " ለመምከር በኡጋንዳ ፤ ኢንቴቤ በተሰባሰበው የኢጋድ አስቸኳይ የመሪዎች ስብሰባ ላይ ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ተገኝተው የነበረ ቢሆንም ዶ/ር ዐቢይ ሳይገኙ ቀርተዋል።

ከአንድ ቀን በኃላ ደግሞ በዛው በኡጋንዳ ፣ ካምፓላ ትላንት በተካሄደው የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (NAM) ርዕሳነ ብሔር እና ርዕሳነ መንግሥታት 19ኛው ጉባኤ ላይ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በአካል ሲገኙ ፤ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ አልተገኙም ነበር።

የአሁኑ የሮም የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ሁለቱንም መሪዎች በአካል በአንድ መድረክ እንዲገኙ ያደርጋል።

መሪዎቹ ከጉባኤው ጎን ለጎን ስለሁለቱ ሀገራት ግኝኑነት የተናጠል ውይይት ያዳርጉ እንደሆነ የሚታወቅ ነገር የለም።

@tikvahethiopia