TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ትግራይ - ያልመከኑ የጦር መሣሪያዎች !

" መቐለ ወደ #ስድስት_ቦታዎች አሁን ራሱ ያልመከኑ ቦንቦች አሉብን። … እስካሁን ድረስ ሞትና አደጋ 1,038 ነው በቢሯችን የያዝነው " - የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ

ባለፉት 2 አመታት የነበረው ከፍተኛ ጦርነት በግንባር ብቻ ሳይሆን በትግራይ ክልል ውስጥ ባሉ የተለያዩ ቦታዎች ላይም ስለተካሄደ አርሶ አደሮችን ጨምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህፃናትና የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ባልመከኑ የጦር መሣሪያዎች ሞትና የአካል ጉዳት አደጋዎች እየደረሱባቸው መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትግራይ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ ሰምቷል።

የትግራይ ጤና ቢሮ ፤ የድንገተኛ ሕክምና አስተባባሪ አቤንዘር እፀድንግል (ዶ/ር) ስለ ጉዳዩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ፣ " በትምህርት ቤቶች፣ በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች፣ መቀሌ ወደ ስድስት ቦታዎች አሁን ራሱ ያልፈነዱ ቦንቦች አሉብን፣ ያልተነሱ ማለት ነው " ያሉ ሲሆን፣ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረቡላቸው የተለያዩ ጥያቄዎችም ማብራሪያዎች ሰጥተዋል።

ያልመከኑት የጦር መሣሪያዎች #መቐለ የት የት ቦታዎች ይገኛሉ ?

- አንደኛው #ከፕላኔት_ጀርባ አካባቢ ነው።

- ሁለተኛው ቦታ የህፃናት መጫወቻ ስፍራ የተመታበት #የአፄ_ዮሐንስ_ቤተመንግሥት_ጀርባ በኩል ነው።

- ሦስተኛው #05 አካባቢ ነው።

- ሌሎቹ ደግሞ መቐለ ውስጥ ሆነው ግን #እርሻ ቦታ ላይ ነው ያሉት።

በርግጥ በኅብረተሰቡ ላይ #አደጋን_እንደሚያደርሱ የሚገልፅ ምልክት (አጥር) ተደርጓል ግን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና በባለሙያ መነሳት አለባቸው " ብለዋል።

ባልመከኑ የጦር መሣሪያዎች ምን ያህል ሰዎች ላይ ሞትና የአካል ጉዳት ደረሰ ?

" ሁሉንም ወደ ጤና ተቋማት አምጥተን ለማከም ሁኔታው አልተመቸም ነበር። ስለዚህ ሙሉ ዳታ የለንም።

ሙሉ ዳታ አባባሌ አንዳንዶቹ አደጋ ደርሶባቸው የሞቱ አሉ፣ ሌሎች መምጣት ያልቻሉ ብዙ ሰዎችም እንዳሉ ግምት ውስጥ ማስገባት አለብን። ባልፈነዱ የጦር መሣሪያዎች ፣ በተጣሉ ተተኳሽ እና የተቀበሩ ቦንቦች አደጋ የደረሰባቸው ባለን ዳታ መሠረት ፦

- እስካሁን ሞትና አደጋ በአጠቃላይ 1,038 ነው ያለን በእኛ በቢሯችን የያዝነው። #163 ሞት፣ 875 ደግሞ ከባድ ጉዳት ማለት ነው።

- ከ163ቱ መካከል 84ቱ ዕድሜአቸው ከ17 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት፣ 79ኙ ደግሞ ዕድሜአቸው ከ18 በላይ የሆኑ አዋቂዎች ናቸው።

- ከ84 #ህፃናት ውስጥ 75ቱ ወንዶች፣ 9ኙ ደግሞ #ሴቶች ናቸው ብለዋል።

ችግሩ አሁንም እንደቀጠለ ነው ? አሁንም የሚመጡ አሉ ?

- አዎ አሁንም ድረስ ይመጣሉ። በተለይ ክረምት ላይ በእርሻ ሥራ መቀሳቀስ ስለሚኖር፣ በመነካካትም ሳያውቁ እያረሱ እያለ መፈዳት ያጋጥማቸው ስለነበሩ ቁጥሩ እየቀነሰ ቢሄድም አልፎ አልፎ እየመጡ ነው። ምክንያቱም በተጠናከረ ደረጃ አልተጠረገም። 

- ፈንጅ ነገሮችን የማጥራት ሥራ ካልሰራን ትልቅ ችግር ነው ያለው። የመንግሥት ተዋጊ አካሎች ትምህርት ቤቶችን እንደ አውደ ማቆያ ሲጠቀሙባቸው ስለነበር እዛ ላይ የተጣሉ ጦር መሳሪያዎች አሁን ትምህርት ሲጀምሩ #ህፃናት በተለያየ ጊዜ አደጋ ይደርስባቸዋል።

- በተለያዩ መንገዶች ሰው ተሸክሟቸው ፣ በጋሪ ፣ በፈረስ ፣ በበቅሎ ሕክምና ቦታ መድረስ የቻሉ ሰዎች እንኳ (በተለይ ደግሞ ሽረ አካባቢ የመጡ ብዙ ታካሚዎች) መድኃኒት በበቂ ሁኔታ ስላልነበረ የጤና ተቋማት በቂ ሕክምና ሊሰጧቸው ባለመቻላቸው ብዙ ያጣናቸው አሉ።

- አካል ጉዳተኞችም ሆነዋል ሕክምና ቢደረግላቸው መትረፍ እየቻሉ ግን የሰርጀሪ እቃዎች እጥረት ስለነበረ አካል ጉዳተኛ የሆኑት በርከት ያሉ ሰዎች ናቸው። በአጠቃላይ በነበረው ሁኔታ ከባድ ነበር ግን አሁን ባለዉ ሁኔታ በተቻለ መጠን ባለን አቅም አገልግሎት እየሰጠን ነው።

ከመድኃኒት እጥረቱ ጋር በተያያዘ የአካል ጉዳተኛ የሆኑ ሰዎችን በቁጥር ደረጃ መግለፅ እችላለን ?

- በቁጥር እንኳ ያስቸግራል፣ ግን እኔ የማስታውሳቸው ወደ ሦስት #ህፃናት በአንድ ወቅት ገብተው የሕክምና እቃዎችን ማግኘት ስላልተቻለ ለአካል ጉዳት ተጋልጠዋል። ይህ በአንድ ወቅት ብቻ ነው። በተጠና መልኩ ግን ብዙ ሊሆኑ ይችላሉ በቁጥር ደረጃ አጋጣሚ አልያዝነውም።

ምን ተሻለ ?

- አንደኛ ከሁሉ በላይ በመጀመሪያ እንዲህ አይነት መሣሪያዎችን መነካካት እንደሌለባቸው ህፃናት፣ ማኅበረሰቡ ማወቅ እንዳለባቸው ትምህርት መሰጠት አለበት።

- የፈንጅ #አምካኝ ባለሙያዎች በስፋት በማሰማራት በእያንዳንዱ ቦታዎች ተሰብስበው ያልመከኑ የጦር መሣሪያዎች መወገድ አለባቸው ፤ በየአካባቢው በጣም በርከት ያሉ #ያልተነሱ ፈንጂዎች አሉብን።

- ከተነሱ ነው በዘላቂነት መፍትሄ የሚገኘው። ሕዝብ ባለበት ቦታ ምንም አይነት ጦርነት አለማካሄድ ላለማካሄድ የሚደነግጉ መርሆዎችም መከበር አለባቸው። የህዝብ መገልገያ ቦታዎች ለወታደራዊ አላማ አለማዋል እንሰ እሪኮመዴሽንም መወሰድ አለበት።

ዘገባው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የተላከ ነው።

@tikvahethiopia
የተሽከርካሪ አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት ቀጠፈ።

ዛሬ ከቀኑ 6 ሰዓት ተኩል አካባቢ በደቡብ ወሎ ዞን ፤ ደሴ ዙሪያ ወረዳ 013 ቀበሌ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት ማለፉን የወረዳው ፖሊስ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ከደሴ ወደ አቀስታ ከተማ 20 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ " ኮድ3-46660 አማ " የሆነ አነስተኛ የህዝብ ማመላለኛ ተሽከርካሪ ገደል ውስጥ በመግባቱ ነው የ14 ሰዎች ህይወት ያለፈው።

ከሟቾቹ መካከል የ12ቱ ሰዎች ህይወታቸው ወዲያውኑ ሲያልፍ አንዱ ወደ ሆስፒታል እየተወሰደ ባለበት ወቅትና ሌላው ተሳፋሪ ደግሞ ደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ህይወቱ አልፏል።

ከአጠቃላይ ሟቾች ውስጥም ስድስቱ #ሴቶች ናቸው።

አሽከርካሪውን ጨምሮ ሌሎች በአደጋው ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 6 ሰዎች በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው።

የሟቾች አስከሬን ለቤተሰቦቻቸው ተሰጥቷል።

ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ እያጣራ መሆኑን ፅ/ቤቱ መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል።

ከዚህ አደጋ ጋር በተያያዘ አንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በላከችው መልዕክት ፤ ከሟቾቹ ሁለቱ የቅርብ ጓደኞቿ እንደሆኑ ተናግራለች።

ሌሎች ሁለቱ ደግሞ እህትማማቾች እንደሆኑ ገልጻለች።

" በጣም ከባድ ሀዘን ላይ ነን ፤ መላው የአቀስታ ህዝብም ከባድ ሃዘን ላይ ነው " ብላለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ደማቁ የዓድዋ የድል መታሰብያ በዓልን በእርስ በርስ ግጭት ማቆሸሽ አይገባም " - ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መልእክት አስተለልፈዋል። ከ3 ዓመት ተኩል በኃላ በትግራይ ታሪካዊትዋ የዓድዋ ከተማ በመገኘት በዓሉን ለማክበር በመቻላቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል። ፕረዚደንትዋ #እንባ_እየተናነቃቸው ያለፈውን አስከፊ ጦርነት በማስታወስ ፣ ተፈናቃዮች ያሉበትን አስከፊ ሁኔታ…
#ትግራይ

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ 😢

" ጠላት ሊወረን ሲመጣ የኢትዮጵያ ህዝብ በዘር ፣ በሃይማኖት ፣ በፆታ ሳይለያይ የመሪውን ዳግማዊ አጼ ሚኒሊክን ጥሪ በመቀበል ተሰባስቦ በመዝመት በነዚህ ተራሮች እና ኮረብታዎች ታሪክ እንዳልሰራ ሁሉ ለራሱ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ፤ ለአፍሪካ አህጉራችን እንዲሁም ለመላው የተጨቆነ ህዝብ ተስፋ የሰጠ ሳለ በዚህች መሬት፦
- ወንድም በወንድሙ ላይ ቃታ የሳበበት የተጋደለበት
- ንፁሃን የተገደሉበት
- ብዙዎች የተሰደዱበት
- በርካቶች በገዛ ሀገራቸው የተንከራተቱበት፣ የተፈናቀሉበት
- ንብረት የወደመበት
- #ሴቶች_የተደፈሩበት ሁኔታ ታሪክ ጅብዱ በተሰራበት ምድር እንዲያይ ያደረግነው። እነዚህ ተራራዎች ለዚህም እማኝ እንዲሆኑ ያደረግነው።

እነዚህ ተራሮች መናገር ቢችሉ እንዲነግሩን የምንፈልገው ግን የህዝባችንን ጀግንነት፣ ታሪክ ሰሪነት፣ አንድነት ነው፤ ምስክሮቻችን ናቸው።

በትግራይ ጦርነቱ እንደጀመረ ሰሞን መጥቼ ነበር። ከጦርነቱ ሁለት ወር በፊት እዚህ ነበርኩ። የጦርነት ደህና ገፅታ የለውም እጅግ አስከፊውን ግን አላየሁም ብዬ ነው የማስበው። "

#TikvahFamilyAdawa

@tikvahethiopia