TIKVAH-ETHIOPIA
" በተለያዩ አጋጣሚዎች ለእስር እና ለእንግልት ቢዳረግም የበቀል ሰው አልነበረም " - አቶ ጃዋር መሀመድ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከፍተኛ አመራር አቶ ጃዋር መሀመድ በአቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ ዙሪያ ምን አሉ ? " የትኛው እጅ ነው ጨክኖ በቴ ኡርጌሳን በለሊት ከእንቅልፋቸው አስነስቶ የሚረሽነው ? እንዴትስ በቴን የሚያውቅ ሆዱ አስችሎት አይኑ እያያ ሊገድለው ቻለ ? ወገኖች ይህ ምን ይባላል…
#Update
በአቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ ላይ አፋጣኝ፣ ገለልተኛና ሙሉ ምርመራ እንዲደረግ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጥሪ አቀረበ።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፥ " ኮሚሽኑ ከተቃዋሚው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ አባል በቴ ኡርጌሳ ግድያ ጋር ተያይዞ ወንጀለኞቹ በህግ እንዲጠየቁ በሁለቱም በኦሮሚያ ክልል እና በኢትዮጵያ ፌዴራል ባለስልጣናት #አፋጣኝ፣ #ገለልተኛ እና #ሙሉ_ምርመራ እንዲደረግ ይጠይቃል " ብለዋል።
አቶ በቴ ኡርጌሳ ትላንት ማክሰኞ ለሊት በትውልድ ከተማቸው መቂ ካረፉበት ሆቴል እንዲወጡ ተደርገው ተገድለው አስክሬናቸው መንገድ ላይ ተገኝቷል።
@tikvahethiopia
በአቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ ላይ አፋጣኝ፣ ገለልተኛና ሙሉ ምርመራ እንዲደረግ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጥሪ አቀረበ።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፥ " ኮሚሽኑ ከተቃዋሚው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ አባል በቴ ኡርጌሳ ግድያ ጋር ተያይዞ ወንጀለኞቹ በህግ እንዲጠየቁ በሁለቱም በኦሮሚያ ክልል እና በኢትዮጵያ ፌዴራል ባለስልጣናት #አፋጣኝ፣ #ገለልተኛ እና #ሙሉ_ምርመራ እንዲደረግ ይጠይቃል " ብለዋል።
አቶ በቴ ኡርጌሳ ትላንት ማክሰኞ ለሊት በትውልድ ከተማቸው መቂ ካረፉበት ሆቴል እንዲወጡ ተደርገው ተገድለው አስክሬናቸው መንገድ ላይ ተገኝቷል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ዛሬ የብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት ፤ በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መምከሩን አሳውቋል። ይህ ተከትሎ ዘለግ ያለ መግለጫ አውጥቷል። በዚህ መግለጫ ፦ - ስለ ሀገራዊ ምክክር - ስለ ሽግግር ፍትሕ - ከመንግሥት ውጭ ታጥቀው ስለሚንቀሳቀሱ ኃይሎች - ስለ ተሃድሶ ኮሚሽን - ስለ ፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት - ስለ ህወሓት ታጣቂዎች - ስለ ተፈናቃዮች መመለስ …
" ... ትጥቅ ሙሉ በሙሉ የማስፈታት ሁኔታ የሚፈጠረው ለትግራይ ሰላማዊ ሁኔታ ሲፈጠር ነው " - አቶ ኢያሱ ተስፋይ
ከቀናት በፊት የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ፥ በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነት እና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ከመከረ በኃላ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።
በመግለጫው የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ብዙ ውጤቶች እና እፎይታን ያስገኘ ቢሆንም አሁንም ቀሪ ስራዎች እንዳሉ ገልጾ ነበር።
ከነዚህ ቀሪ ስራዎች አንዱ የ ' ህወሓት ' ትጥቅ መፍታት እንደሆነ ጠቁሞ ፤ " በሰላም ስምምነቱ መሰረት ህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው ፤ በብሄራዉ ተሃድሶ ኮሚሽን እቅድ መሰረት በፍጥነት መተግበር አለበት " ብሎ ነበር።
በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጠው ህወሓት በስምምነቱ መሰረት " ከኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ / የፌዴራል ጸጥታ ኃይል ውጭ ያሉ ማንኛውም ኃይሎች ከትግራይ የአስተዳደር ወሰን እንዲወጡ መደረግ አለበት " ብሏል።
የህወሓት የፕሮፖጋንዳ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ ኢያሱ ተስፋይ ከሰሞኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥ " ' ለዘላቂ ሰላም ትጥቅ መፍታት አለባቸው የሚለው ችግር የለውም ትክክል ነው " ያሉ ሲሆን " እንደ ትግራይ ህዝብ ፖለቲካዊ ጥያቄዎቻችን ከተመለሱልን ወደ ልማትና ወደ ዴሞክራሲ ግንባታ ስራችን መሸጋገር እንፈልጋለን " ብለዋል።
" ለሰላም ከማንም በላይ ጥብቅና እንቆማለን ስትራቴጃካዊ ፍላጎታችንም ነው ግን ደግሞ ያ ሰላም ከጥያቄዎቻችን መመለስ ጋር በቀጥታ መያያዝ አለበት እንጂ ጥያቄዎቻችን ሳይመለሱ መብታችን ሳይከበር ዝም ብሎ ሰላም የሚመጣ ነገር አይደለም " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ለሰላም ብለን ቀደም ብለን ትጥቅ ማስፈታት ጀምረናል። የከባድ ማሳሪያም ርክክብም ከአመት በፊት አድርገናል፣ ከዛ አልፎ ከነበረን ሰራዊት በርካታውን demobilize አድርገናል ፤ " ሲሉ አክለዋል።
" ትጥቅ #ሙሉ_በሙሉ_የማስፈታት_ሁኔታ የሚፈጠረው ለትግራይ ሰላማዊ ሁኔታ ሲፈጠር ነው። ከፌዴራል ኃይል ውጭ ያሉ የተለያዩ ታጣቂ ኃይሎች በምዕራብ ትግራይ አሉ ህዝባችንን ለብዙ መከራ እየዳረጉ ያሉ በጸለምትም ፣ በደቡብ ትግራይም ስለዚህ አሁን ፌዴራል በጀመረው ነገር እነዚህን ኃይሎች ትጥቃቸውን እንዲፈቱና ወደ ሌላ ስራቸው እንዲሄዱ የማድረግ ኃላፊነት አለበት " ብለዋል።
ለDDR የሚያስፈልገው ሁሉ በጀትም መመደብ አለበት ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
ከቀናት በፊት የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ፥ በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነት እና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ከመከረ በኃላ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።
በመግለጫው የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ብዙ ውጤቶች እና እፎይታን ያስገኘ ቢሆንም አሁንም ቀሪ ስራዎች እንዳሉ ገልጾ ነበር።
ከነዚህ ቀሪ ስራዎች አንዱ የ ' ህወሓት ' ትጥቅ መፍታት እንደሆነ ጠቁሞ ፤ " በሰላም ስምምነቱ መሰረት ህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው ፤ በብሄራዉ ተሃድሶ ኮሚሽን እቅድ መሰረት በፍጥነት መተግበር አለበት " ብሎ ነበር።
በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጠው ህወሓት በስምምነቱ መሰረት " ከኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ / የፌዴራል ጸጥታ ኃይል ውጭ ያሉ ማንኛውም ኃይሎች ከትግራይ የአስተዳደር ወሰን እንዲወጡ መደረግ አለበት " ብሏል።
የህወሓት የፕሮፖጋንዳ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ ኢያሱ ተስፋይ ከሰሞኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥ " ' ለዘላቂ ሰላም ትጥቅ መፍታት አለባቸው የሚለው ችግር የለውም ትክክል ነው " ያሉ ሲሆን " እንደ ትግራይ ህዝብ ፖለቲካዊ ጥያቄዎቻችን ከተመለሱልን ወደ ልማትና ወደ ዴሞክራሲ ግንባታ ስራችን መሸጋገር እንፈልጋለን " ብለዋል።
" ለሰላም ከማንም በላይ ጥብቅና እንቆማለን ስትራቴጃካዊ ፍላጎታችንም ነው ግን ደግሞ ያ ሰላም ከጥያቄዎቻችን መመለስ ጋር በቀጥታ መያያዝ አለበት እንጂ ጥያቄዎቻችን ሳይመለሱ መብታችን ሳይከበር ዝም ብሎ ሰላም የሚመጣ ነገር አይደለም " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ለሰላም ብለን ቀደም ብለን ትጥቅ ማስፈታት ጀምረናል። የከባድ ማሳሪያም ርክክብም ከአመት በፊት አድርገናል፣ ከዛ አልፎ ከነበረን ሰራዊት በርካታውን demobilize አድርገናል ፤ " ሲሉ አክለዋል።
" ትጥቅ #ሙሉ_በሙሉ_የማስፈታት_ሁኔታ የሚፈጠረው ለትግራይ ሰላማዊ ሁኔታ ሲፈጠር ነው። ከፌዴራል ኃይል ውጭ ያሉ የተለያዩ ታጣቂ ኃይሎች በምዕራብ ትግራይ አሉ ህዝባችንን ለብዙ መከራ እየዳረጉ ያሉ በጸለምትም ፣ በደቡብ ትግራይም ስለዚህ አሁን ፌዴራል በጀመረው ነገር እነዚህን ኃይሎች ትጥቃቸውን እንዲፈቱና ወደ ሌላ ስራቸው እንዲሄዱ የማድረግ ኃላፊነት አለበት " ብለዋል።
ለDDR የሚያስፈልገው ሁሉ በጀትም መመደብ አለበት ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IRAN🇮🇷 የኢራኑ ፕሬዝዳንት እና አብረዋቸው የነበሩ ከፍተኛ ባለስልጣናት (የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ጨምሮ) እየተፈለጉ ነው። ህዝቡ መሪዎቹ ምንም ሳይሆኑ በህይወት ተርፈው ይመለሱ ዘንድ ፈጣሪውን እየለመነ ይገኛል። ፕ/ት ኢብራሂም ራኢሲ እና ሌሎች ባለስልጣናት ኢራን ከአዘርባጀን ጋር በምትዋሰንበት አካባቢ ላይ የተገነቡ 2 ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ በሂሊኮፕተር ወደ ታብሪዝ ከተማ ሲያመሩ ነው…
#ኢራን
የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ተሳፍረውባት በነበረው ሄሊኮፕተር በደረሰው አደጋ ህይወታቸው አልፏል።
ይህንንም የሀገሪቱ የመንግሥት አረጋግጧል።
ከሳቸው በተጨማሪ በሂሊኮፕተር ውስጥ አብረው የነበሩት የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴይን አሚር አብዶላሂያን እና ሌሎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል።
ሮይተርስ በአደጋው ፕሬዚዳንቱ ሲጓዙባት የነበረችው ሄሊኮፕተር #ሙሉ_በሙሉ መቃጠሏን " አንድ የኢራን ባለስልጣንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
" የፕሬዜዳንት ኢብራሂም ራይሲ ሄሊኮፕተር በአደጋው ሙሉ በሙሉ ተቃጥላለች። በሚያሳዝን ሁኔታ ሁሉም ተሳፋሪዎች ሳይሞቱ አልቀሩም " ብለዋል ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን።
#ሮይተርስ
@tikvahethiopia
የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ተሳፍረውባት በነበረው ሄሊኮፕተር በደረሰው አደጋ ህይወታቸው አልፏል።
ይህንንም የሀገሪቱ የመንግሥት አረጋግጧል።
ከሳቸው በተጨማሪ በሂሊኮፕተር ውስጥ አብረው የነበሩት የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴይን አሚር አብዶላሂያን እና ሌሎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል።
ሮይተርስ በአደጋው ፕሬዚዳንቱ ሲጓዙባት የነበረችው ሄሊኮፕተር #ሙሉ_በሙሉ መቃጠሏን " አንድ የኢራን ባለስልጣንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
" የፕሬዜዳንት ኢብራሂም ራይሲ ሄሊኮፕተር በአደጋው ሙሉ በሙሉ ተቃጥላለች። በሚያሳዝን ሁኔታ ሁሉም ተሳፋሪዎች ሳይሞቱ አልቀሩም " ብለዋል ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን።
#ሮይተርስ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ? በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል። አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል። ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ…
#Update
" በሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ " ላይ የመጨረሻ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩም የሃይማኖት ተቋማት ቅሬታ ማቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።
ተቋማቱ ረቂቅ አዋጁ ከመፅደቁ በፊት የሁሉንም የሃይማኖት ተቋማት መብትና ክብር የሚጠብቅ መሆኑ ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።
በአብዛኛው ተከብሮ የቆየው የሃይማኖቶች ነፃነት ላይ ገደቦችን እንዳይጥል ሥጋት እንዳላቸው ገልጸዋል።
የቀረቡ ቅሬታዎች ምንድናቸው ?
1ኛ. ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች የተነሳው ቅሬት፦
በረቂቁ አዋጁ ላይ የአደባባይ በዓላትን በሚመለከት " የአደባባይ ኩነት " ተብሎ መቀመጡን በማንሳት ይህ ትክክለኛ ትርጉም አይደለም ብለዋል፡፡
ለዚህ በማሳያ " የአደባባይ ኩነት በተፈቀደው ቦታ ብቻ መደረግ አለበት " በሚል በረቂቁ ላይ የተቀመጠውን ነው።
ለአብነት #የጥምቀት_በዓል የአደባባይ ሃይማኖታዊ በዓል ቢሆንም ፤" ከተፈቀደለት አደባባይ ውጪ መንገዶች ላይ መካሄድ አይፈቀድም " የሚል ትርጓሜ እንዳይሰጠው #ያሠጋል ብለዋል፡፡
ሌላው " የሃይማኖት ተቋም የሚይዘው ስያሜ፣ ዓርማ ወይም ምልክት ቀድሞ ከተቋቋመ ተቋም ስም፣ ዓርማ ወይም ምልክት ጋር ተመሳሳይ መሆን የለበትም " በሚል ረቂቁ ላይ የተቀመጠው ነው።
ይህ ፤ " #በከፊልም ሆነ #ሙሉ_በሙሉ ተመሳሳይ መሆን የለበትም " በሚል ሊስተካከል እንደሚገባው ገልጸዋል።
ለዚህ ምክንያቱ " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሚለውን ስያሜ የኢትዮጵያ የሚለውን ብቻ በማውጣትና የራሳቸውን በመተካት አገልግሎት ላይ ሲያውሉ የሚታዩ አካላትን ስለተመለከትን ነው " በማለት አስረድተዋል፡፡
2ኛ. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ ቤትን በመወከል የተገኙ ተሳታፊዎች ያቀረቡት ቅሬት ፦
ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሚከለክለው የረቂቅ አዋጁ ክፍል " በአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎች መፈጸም የተከለከለ ነው " በሚል የቀረበው ሊስተካከል ይገባል ብለዋል።
#ሶላት_የደረሰበት_ሙስሊም በአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎች እንዳይሰግድ መከልከል እንደማይቻል ገልጸዋል፡፡
" በከተሞች ውስጥ ለአምልኮና መቃብር የሚሰጥ ቦታ የከተማውን የዕድገትና የልማት ዕቅድ ወይም ማስተር ፕላን የማይቃረን መሆን አለበት " በሚለው ረቂቁ ላይ ይህ ወደ ተግባራዊነቱ ሲገባ አስቸጋሪ እንደሚሆን ገልጸዋል።
መጀመሪያ የተገነባ ቤተ እምነት " ከከተማው ማስተር ፕላን ጋር የሚቃረን ነው " በሚል እንዳይፈርስ ዋስትና የማይሰጥ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በመንግሥት ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች ሁሉ እምነት እንዳላቸው፣ ለአብነትም አንድ ሙስሊም በመንግሥት ተቋም ተቀጥሮ ሲሠራ ሶላቱን በሚሰግድበት ወቅት፣ በተቋሙ ውስጥ ሃይማኖታዊ ክንውን አድርጓል ሊባል መሆኑንና ረቂቁ ይህን እንዴት ማስታረቅ እንደሚችል ጥያቄ አስነስቷል፡፡
3ኛ. የወንጌል አማኞች ካውንስል ተወካዮች ቅሬታ ፦
ረቂቅ አዋጁ በወንጌላውያን ሃይማኖት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
" በተለይ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ የሚከለክሉ የረቂቁ ክፍሎች፣ ወንጌል መስበክ መሠረታዊ አስተምሯችን ለሆነው ለወንጌላውያን ተቀባይነት ሊኖረው የማይችል ነው " በማለት ተናግረዋል፡፡
ይህ ' መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ' በሚል የተቀመጠውን መርህ የጣሰ እንዳይሆን ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡
Credit ➡️ Reporter Newspaper
@tikvahethiopia
" በሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ " ላይ የመጨረሻ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩም የሃይማኖት ተቋማት ቅሬታ ማቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።
ተቋማቱ ረቂቅ አዋጁ ከመፅደቁ በፊት የሁሉንም የሃይማኖት ተቋማት መብትና ክብር የሚጠብቅ መሆኑ ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።
በአብዛኛው ተከብሮ የቆየው የሃይማኖቶች ነፃነት ላይ ገደቦችን እንዳይጥል ሥጋት እንዳላቸው ገልጸዋል።
የቀረቡ ቅሬታዎች ምንድናቸው ?
1ኛ. ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች የተነሳው ቅሬት፦
በረቂቁ አዋጁ ላይ የአደባባይ በዓላትን በሚመለከት " የአደባባይ ኩነት " ተብሎ መቀመጡን በማንሳት ይህ ትክክለኛ ትርጉም አይደለም ብለዋል፡፡
ለዚህ በማሳያ " የአደባባይ ኩነት በተፈቀደው ቦታ ብቻ መደረግ አለበት " በሚል በረቂቁ ላይ የተቀመጠውን ነው።
ለአብነት #የጥምቀት_በዓል የአደባባይ ሃይማኖታዊ በዓል ቢሆንም ፤" ከተፈቀደለት አደባባይ ውጪ መንገዶች ላይ መካሄድ አይፈቀድም " የሚል ትርጓሜ እንዳይሰጠው #ያሠጋል ብለዋል፡፡
ሌላው " የሃይማኖት ተቋም የሚይዘው ስያሜ፣ ዓርማ ወይም ምልክት ቀድሞ ከተቋቋመ ተቋም ስም፣ ዓርማ ወይም ምልክት ጋር ተመሳሳይ መሆን የለበትም " በሚል ረቂቁ ላይ የተቀመጠው ነው።
ይህ ፤ " #በከፊልም ሆነ #ሙሉ_በሙሉ ተመሳሳይ መሆን የለበትም " በሚል ሊስተካከል እንደሚገባው ገልጸዋል።
ለዚህ ምክንያቱ " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሚለውን ስያሜ የኢትዮጵያ የሚለውን ብቻ በማውጣትና የራሳቸውን በመተካት አገልግሎት ላይ ሲያውሉ የሚታዩ አካላትን ስለተመለከትን ነው " በማለት አስረድተዋል፡፡
2ኛ. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ ቤትን በመወከል የተገኙ ተሳታፊዎች ያቀረቡት ቅሬት ፦
ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሚከለክለው የረቂቅ አዋጁ ክፍል " በአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎች መፈጸም የተከለከለ ነው " በሚል የቀረበው ሊስተካከል ይገባል ብለዋል።
#ሶላት_የደረሰበት_ሙስሊም በአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎች እንዳይሰግድ መከልከል እንደማይቻል ገልጸዋል፡፡
" በከተሞች ውስጥ ለአምልኮና መቃብር የሚሰጥ ቦታ የከተማውን የዕድገትና የልማት ዕቅድ ወይም ማስተር ፕላን የማይቃረን መሆን አለበት " በሚለው ረቂቁ ላይ ይህ ወደ ተግባራዊነቱ ሲገባ አስቸጋሪ እንደሚሆን ገልጸዋል።
መጀመሪያ የተገነባ ቤተ እምነት " ከከተማው ማስተር ፕላን ጋር የሚቃረን ነው " በሚል እንዳይፈርስ ዋስትና የማይሰጥ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በመንግሥት ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች ሁሉ እምነት እንዳላቸው፣ ለአብነትም አንድ ሙስሊም በመንግሥት ተቋም ተቀጥሮ ሲሠራ ሶላቱን በሚሰግድበት ወቅት፣ በተቋሙ ውስጥ ሃይማኖታዊ ክንውን አድርጓል ሊባል መሆኑንና ረቂቁ ይህን እንዴት ማስታረቅ እንደሚችል ጥያቄ አስነስቷል፡፡
3ኛ. የወንጌል አማኞች ካውንስል ተወካዮች ቅሬታ ፦
ረቂቅ አዋጁ በወንጌላውያን ሃይማኖት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
" በተለይ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ የሚከለክሉ የረቂቁ ክፍሎች፣ ወንጌል መስበክ መሠረታዊ አስተምሯችን ለሆነው ለወንጌላውያን ተቀባይነት ሊኖረው የማይችል ነው " በማለት ተናግረዋል፡፡
ይህ ' መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ' በሚል የተቀመጠውን መርህ የጣሰ እንዳይሆን ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡
Credit ➡️ Reporter Newspaper
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ቅዱስ ሲኖዶስ በምልዓተ ጉባኤው የብፁዕ አቡነ ልቃስን የአውደምህረት ንግግር ከቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና አስተምህሮት ውጭ የሆነ ፣ ቅዱስ ሲኖዶስንም ሆነ ቤተክርስቲያንን የማይወክል ነው ሲል ውሳኔ አሳለፈ። ንግግራቸው ቤተክርስቲያንን #ዋጋ_እያስከፈላት መሆኑና በቤተክርስቲያንና መንግሥት መካከል የነበረውን ግንኙነት እንዳሻከረው ተመላክቷል። ቅዱስ ሲኖዶስ ፥ ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ…
#ሙሉ_ቃል
ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ ምን አለ ?
" ' ግደሉ ብሎ ' ማወጅ ቤተክርስቲያኒቱን የማይወክል እና ቅዱስ ሲኖዶስን የማይመጥን ንግግር ነው " - ቅዱስ ሲኖዶስ
ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳለፈውን ውሳኔ ያቀረቡት ብፁዕ አቡነ አብርሃም ናቸው።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በንባብ ያሰሙት ፦
" በአሁኑ ሰዓት ላይ ትልቅ ተግዳሮትና የፈተና ምንጭ በመሆን ቤተክርስቲያናችንን ዋጋ እያስከፈሏት ያሉትን የአንዳንድ አባቶች መግለጫ እና የአውደ ምህረት ትምህርቶች እንደ አብነት በመጥቀስ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሰፊው ተወያይቷል።
በውይይቱ የተለዩ ዋና ዋና ነጥቦች ፦
- አብዛኛው የአውደ ምህረት ስብከቶቻችን ከትምህርተ ወንጌል ይልቅ የነገር እና የደረቅ ትችት መድረክ እየሆኑ መምጣታቸው ፤
- በተለይም በመዋቅር ውስጥ የስራ መደብ የሌላቸው ተዘዋዋሪ " #ሰባኪ_ነን_ባዮች " የወገንተኝነት እና የፖለቲካ ትችትን እንደ ተከታይ ማፍሪያ በመቁጠር በሚዘሩት ፍጹም ከቃለ ወንጌል የራቀ ዘር ቅድስት ቤተክርስቲያንን ዋጋ እያስከፈላት መሆኑ ፤ ይህን ለመከላከል ጥረት በሚያደርጉ አህጉረ ስብከት ላይ ትልቅ የመልካም አስተዳደር ችግር እየተፈጠረ መሆኑ ፤
- በተለይም ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ፅ/ቤት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስ ታህሳስ 19 / 2016 ዓ/ም በሀገረ አሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሜሪላንድ ከተማ ሐመረብርሃን ቅዱስ ዮሐንስ ወቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በዓለ ንግስ ላይ ታቦተ ህጉ በቆመበትና ምእመናንም በተሰበሰቡበት እንደ ቀኖና ቤተክርስቲያን ዕለቱን አስመልክቶ ተገቢውን ትምህርተ ወንጌል ከመስጠት ይልቅ ቤተክርስቲያንን የማይመጥን እና የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ብሎም የአባትነትን ክብር ዝቅ በሚያደርግ ሁኔታ አንድን የተከበረ ጠቅላይ ሚኒስትር ፦
° " #ግድሉ "
° " #ዘርህ_ይጥፋ "
° " #የአድማ_ብተና_ይበትንህ " የሚሉ ህገወጥ እና ክብረነክ የሆኑ ንግግሮች በመናገር በፈጸሙት ያልተገባ ተግባር በቤተክርስቲያኒቱ እና በመንግስት መካከል የነበረውን ግንኙነት በማሻከር ቤተክርስቲያንን ብዙ ዋጋ እያስከፈላት ከመሆኑ በላይ ለዘመናት ጸንቶ የቆየውን የአባቶችን ክብር እና የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ዝቅ ያደረገ ተገቢነት የሌለው አድርጎት መሆኑን፤
- ክብር ይግባውና ጌታችን፣ አምላካችን መድሃኒታችን ኢያሱስ ክርስቶስ በማትዮስ ወንጌል ምዕራፍ አምስት ቁጥር ሰላሳዘጠኝ ላይ እንደተናገረው " እኔ ግን እላችኋለሁ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግመህ አዙርለት " ብሎ ያስተማረውን አብነት አድርጋ አትግደል የሚለውን ህገ ኦሪት አጽንታ እያስተማረች እስካሁን ድረስ ጸንታ በቆየችው እናት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አውደምህረት ላይ " ግደሉ " ብሎ ማወጅ ቤተክርስቲያኒቱን የማይወክልና ቅዱስ ሲኖዱስን የማይመጥን ንግግር መሆኑን ፤
- ልክ እንደ አቡነ ሉቃስ ፈጽሞ ጫፍ የረገጠ ባይሆንም ሌሎችም #አንዳንድ_አባቶች በተለያዩ ቦታዎች ያስተላለፏቸው መልዕክቶች አግባብነት የሌላቸውና ቤተክርስቲያንን ለትችት የዳረጉ መሆናቸውን ምልዓተ ጉባኤው በዝርዝር ገምግሟል።
ውሳኔ ፦
1ኛ. ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ፅህፈት ቤት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስ ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ/ም በሀገረ አሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሜሪላንድ ከተማ ሐመረብርሃን ቅዱስ ዮሐንስ ወ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አውደምህረት ላይ " ግደሉ ፣ ዘርህ ይጥፋ፣ የአድማ ብተና ይበትንህ " ... ሌሎች ከቀኖና ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ ንግግሮች ቤተክርስቲያኒቱንም ሆነ ቅዱስ ሲኖዶስን የማይወክል ከቤተክርስቲያኒቱ አስተምህሮ እና ቀኖና ውጭ የሆነ ከህገ ኦሪትም ሆነ ከቃለ ወንጌል ያፈነገጠ ንግግር መሆኑ ፤
2ኛ. በቀጣይም እንዲህ አይነት ተመሳሳይ ስህተት #በብዑጽነታቸው ሆነ በአንዳንድ አባቶች ሰባክያን ወንጌል እንዳይደገም ተፈጽሞም ቢገኝ ተገቢው የእርምት ውሳኔ ለመስጠት ይቻል ዘንድ የመግለጫ አሰጣጥ እና የትምህርተ ወንጌል አሰጣጥ አስመልክቶ ገዢ የሆነ ህገ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት አገልግሎት መምሪያ እና በሊቃውንት ጉባኤ በኩል ተዘጋጅቶ ለጥቅምት 2017 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ፤
3ኛ. ይህ ውሳኔ ከተወሰነበት ዕለት ጀምሮ በመላው ዓለም የሚገኙ አህጉረ ስብከት ተመሳሳይ ስህተት እንዳይፈጸም ተገቢውን ቁጥጥር እና ክትትል እንዲያደርጉ ፤ ከክትትል እና ከቁጥጥር ጉድለት ምክንያት በየትኛውም የቤተክርስቲያኒቱ አውደምህረት ላይ ለሚተላለፉ የተሳሳቱና ከቀኖና ቤተክርስቲያን ያፈነገጡ ትምህርቶች እና ንግግሮች በኃላፊነት የሚያስጠይቅ መሆኑን ለሁሉም ሀገረ ስብከት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ጥብቅ መመሪያ እንዲተላለፍ በማለት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል።
ይህ ሙሉ ቃል የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ነው። "
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ ምን አለ ?
" ' ግደሉ ብሎ ' ማወጅ ቤተክርስቲያኒቱን የማይወክል እና ቅዱስ ሲኖዶስን የማይመጥን ንግግር ነው " - ቅዱስ ሲኖዶስ
ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳለፈውን ውሳኔ ያቀረቡት ብፁዕ አቡነ አብርሃም ናቸው።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በንባብ ያሰሙት ፦
" በአሁኑ ሰዓት ላይ ትልቅ ተግዳሮትና የፈተና ምንጭ በመሆን ቤተክርስቲያናችንን ዋጋ እያስከፈሏት ያሉትን የአንዳንድ አባቶች መግለጫ እና የአውደ ምህረት ትምህርቶች እንደ አብነት በመጥቀስ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሰፊው ተወያይቷል።
በውይይቱ የተለዩ ዋና ዋና ነጥቦች ፦
- አብዛኛው የአውደ ምህረት ስብከቶቻችን ከትምህርተ ወንጌል ይልቅ የነገር እና የደረቅ ትችት መድረክ እየሆኑ መምጣታቸው ፤
- በተለይም በመዋቅር ውስጥ የስራ መደብ የሌላቸው ተዘዋዋሪ " #ሰባኪ_ነን_ባዮች " የወገንተኝነት እና የፖለቲካ ትችትን እንደ ተከታይ ማፍሪያ በመቁጠር በሚዘሩት ፍጹም ከቃለ ወንጌል የራቀ ዘር ቅድስት ቤተክርስቲያንን ዋጋ እያስከፈላት መሆኑ ፤ ይህን ለመከላከል ጥረት በሚያደርጉ አህጉረ ስብከት ላይ ትልቅ የመልካም አስተዳደር ችግር እየተፈጠረ መሆኑ ፤
- በተለይም ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ፅ/ቤት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስ ታህሳስ 19 / 2016 ዓ/ም በሀገረ አሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሜሪላንድ ከተማ ሐመረብርሃን ቅዱስ ዮሐንስ ወቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በዓለ ንግስ ላይ ታቦተ ህጉ በቆመበትና ምእመናንም በተሰበሰቡበት እንደ ቀኖና ቤተክርስቲያን ዕለቱን አስመልክቶ ተገቢውን ትምህርተ ወንጌል ከመስጠት ይልቅ ቤተክርስቲያንን የማይመጥን እና የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ብሎም የአባትነትን ክብር ዝቅ በሚያደርግ ሁኔታ አንድን የተከበረ ጠቅላይ ሚኒስትር ፦
° " #ግድሉ "
° " #ዘርህ_ይጥፋ "
° " #የአድማ_ብተና_ይበትንህ " የሚሉ ህገወጥ እና ክብረነክ የሆኑ ንግግሮች በመናገር በፈጸሙት ያልተገባ ተግባር በቤተክርስቲያኒቱ እና በመንግስት መካከል የነበረውን ግንኙነት በማሻከር ቤተክርስቲያንን ብዙ ዋጋ እያስከፈላት ከመሆኑ በላይ ለዘመናት ጸንቶ የቆየውን የአባቶችን ክብር እና የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ዝቅ ያደረገ ተገቢነት የሌለው አድርጎት መሆኑን፤
- ክብር ይግባውና ጌታችን፣ አምላካችን መድሃኒታችን ኢያሱስ ክርስቶስ በማትዮስ ወንጌል ምዕራፍ አምስት ቁጥር ሰላሳዘጠኝ ላይ እንደተናገረው " እኔ ግን እላችኋለሁ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግመህ አዙርለት " ብሎ ያስተማረውን አብነት አድርጋ አትግደል የሚለውን ህገ ኦሪት አጽንታ እያስተማረች እስካሁን ድረስ ጸንታ በቆየችው እናት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አውደምህረት ላይ " ግደሉ " ብሎ ማወጅ ቤተክርስቲያኒቱን የማይወክልና ቅዱስ ሲኖዱስን የማይመጥን ንግግር መሆኑን ፤
- ልክ እንደ አቡነ ሉቃስ ፈጽሞ ጫፍ የረገጠ ባይሆንም ሌሎችም #አንዳንድ_አባቶች በተለያዩ ቦታዎች ያስተላለፏቸው መልዕክቶች አግባብነት የሌላቸውና ቤተክርስቲያንን ለትችት የዳረጉ መሆናቸውን ምልዓተ ጉባኤው በዝርዝር ገምግሟል።
ውሳኔ ፦
1ኛ. ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ፅህፈት ቤት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስ ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ/ም በሀገረ አሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሜሪላንድ ከተማ ሐመረብርሃን ቅዱስ ዮሐንስ ወ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አውደምህረት ላይ " ግደሉ ፣ ዘርህ ይጥፋ፣ የአድማ ብተና ይበትንህ " ... ሌሎች ከቀኖና ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ ንግግሮች ቤተክርስቲያኒቱንም ሆነ ቅዱስ ሲኖዶስን የማይወክል ከቤተክርስቲያኒቱ አስተምህሮ እና ቀኖና ውጭ የሆነ ከህገ ኦሪትም ሆነ ከቃለ ወንጌል ያፈነገጠ ንግግር መሆኑ ፤
2ኛ. በቀጣይም እንዲህ አይነት ተመሳሳይ ስህተት #በብዑጽነታቸው ሆነ በአንዳንድ አባቶች ሰባክያን ወንጌል እንዳይደገም ተፈጽሞም ቢገኝ ተገቢው የእርምት ውሳኔ ለመስጠት ይቻል ዘንድ የመግለጫ አሰጣጥ እና የትምህርተ ወንጌል አሰጣጥ አስመልክቶ ገዢ የሆነ ህገ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት አገልግሎት መምሪያ እና በሊቃውንት ጉባኤ በኩል ተዘጋጅቶ ለጥቅምት 2017 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ፤
3ኛ. ይህ ውሳኔ ከተወሰነበት ዕለት ጀምሮ በመላው ዓለም የሚገኙ አህጉረ ስብከት ተመሳሳይ ስህተት እንዳይፈጸም ተገቢውን ቁጥጥር እና ክትትል እንዲያደርጉ ፤ ከክትትል እና ከቁጥጥር ጉድለት ምክንያት በየትኛውም የቤተክርስቲያኒቱ አውደምህረት ላይ ለሚተላለፉ የተሳሳቱና ከቀኖና ቤተክርስቲያን ያፈነገጡ ትምህርቶች እና ንግግሮች በኃላፊነት የሚያስጠይቅ መሆኑን ለሁሉም ሀገረ ስብከት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ጥብቅ መመሪያ እንዲተላለፍ በማለት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል።
ይህ ሙሉ ቃል የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ነው። "
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia