TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Live stream started
#ቀጥታ

የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ።

ከላይ " Join " የሚለውን በመንካትና በመግባት በቀጥታ ይከታታሉ።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቀጥታ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ። ከላይ " Join " የሚለውን በመንካትና በመግባት በቀጥታ ይከታታሉ። #TikvahEthiopia @tikvahethiopia
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦

" ፈተናው ካለፈው በተሻለ ከኩረጃ እና ሌብነት የፀዳ ነበር። "

የትምህርት ሚኒስትሩ የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አስመልክተው መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ ከላይ " Join " ብለው በቀጥታ ያድምጡ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ፈተናው ካለፈው በተሻለ ከኩረጃ እና ሌብነት የፀዳ ነበር። " የትምህርት ሚኒስትሩ የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አስመልክተው መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ ከላይ " Join " ብለው በቀጥታ ያድምጡ። @tikvahethiopia
ውጤቱ እንዴት ነው ?

ከፍተኛ ውጤት ተፈጥሮ ሳይንስ 649 ፤ የማህበራዊ ሳይንስ 533 ሆኖ ተመዝግቧል።

649 ያመጣችው የአዲስ አበባ ልደታ ክሩዝ ትምህርት ቤት ስትሆን 533 ያመጣው ከደ/ማርቆስ አዲስ አለማየሁ ትምህርት ቤት ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአጠቃላይ በ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑ ተማሪዎች 3.2 በመቶ ብቻ ናቸው 50 በመቶ እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡት። @tikvahethiopia
#Update

ትምህርት ሚኒስቴር ዘንድሮም የሬሜዲያል ፕሮግራም እንደሚኖር አስታወቀ።

በቀጥታ ያለፉ ተማሪዎች ውስን ስለሆኑ ዘንድሮም የሬሜዲያል ፕሮግራም ይኖራል ተብሏል።

ፕ/ር ብርሃኑ አምና የገባሁትን ቃሌን በማጠፌ ይቅርታ ብለዋል።

ሚኒስትሩ አምና የሬሜዲያል ፕሮግራም ለአንድ ጊዜ የተሰጠ እድል ብቻ እንደሆነ መግለቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#Update

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በመግለጫቸው " 5 ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ አሳልፈዋል፡፡ " ብለዋል።

ሌሎች 5 ትምህርት ቤቶች ድግሞ ካስፈተኗቸው ውስጥ 95 ከመቶ ተማሪዎቻቸውን እንዳሳለፉ ገልጸዋል።

ከፍተኛ አፈጻጻም ያሳዩ አስር ትምህርት ቤቶች (በደረጃ)፦

1. አዲስ አለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት (ደብረማርቆስ)
2. ደሴ አዳሪ ትምህርት ቤት
3. ባህርዳር ስቴም ትምህርት ቤት
4. ሀይራንዚ አዳሪ ትምህርት ቤት (ስልጤ ዞን)
5. ሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት (ሀድያ)
6. ኦዳ አዳሪ ትምህርት ቤት (አዳማ)
7. ኮተቤ ሼርድ ካምፓስ
8. የኔታ አካዳሚ
9. ወላይታሊቃ አዳሪ ትምህርት ቤት
10. ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት

Via @tikvahuniversity
Live stream finished (1 hour)
ውጤት በምን ይታያል ?

" ነገ ጥዋት 12 ሰዓት ላይ በዌብሳይት እና በSMS ተማሪዎች ውጤታቸውን ማየት ይቻላሉ። " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ውጤት በምን ይታያል ? " ነገ ጥዋት 12 ሰዓት ላይ በዌብሳይት እና በSMS ተማሪዎች ውጤታቸውን ማየት ይቻላሉ። " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ @tikvahethiopia
#ሙሉ_መግለጫ

የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ የሰጠው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጥዋት 12 ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተከታትሎ መረጃዎችን ያደርሳል።

More - @tikvahuniversity @tikvahethmagazine

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#MoE

ሚኒስትሩን ያስደናገጣቸው ቁጥር ?

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦

" ከዚህ ፈተና አንድ #ሊያስደነግጠን የሚገባ ነገር ከተፈተኑት ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 50 ከመቶ የሚሆኑት እና ከዛ በላይ 26 ከመቶ ነው ያገኙት።

ከ845 ሺህ ፤ 422,500 ሺህ ተማሪ ከ26 በታች ነው ያገኘው። እንደው ዝም ብሎ አንድ ተማሪ ፈተናውን በግምት ቢሞላ እንኳን ሊያገኘው የሚችለው ውጤት ነው።

ለዚህ ነው ከታች ጀምሮ በደንብ አጥርተን መስራት አለብን የምንለው። "

ስለ 2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ቁጥሮች ምን ይላሉ ?

- በ2015 የተፈተኑ ተማሪዎች ብዛት 845,099 ፤ 50 በመቶና በላይ ያመጡ 27,267 ተማሪዎች (3.2%) ብቻ ናቸው።

ከነዚህ ውስጥ ፦
• ከተፈጥሮ ሳይንስ ያለፉ 19,017 ተማሪዎች
• ከማህበራዊ ሳይንስ ያለፉ 8,250 ተማሪዎች

- በማታ የተፈተኑ 16,541 ያለፉ 12 ተማሪዎች ብቻ

- በግል የተፈተኑ 169,502 ያለፉ 498 ተማሪዎች ብቻ

- በመደበኛ የተፈተኑ 659,056 ያለፉ 26,757 ተማሪዎች ብቻ

- የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 ት/ቤቶች፤ 1,328 ትምህርት ቤቶች #አንድም_ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም / ምንም ተማሪ አላሳለፉም።

- በሀገሪቱ ካሉትና የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑት ትምህርት ቤቶች 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም እንኳን ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።

- 27 ሺህ 267 ተማሪዎች በቀጥታ ፍሬሽ ማን ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ 160 ሺህ ገደማ ተማሪ በሬሜዲያል ይገባሉ።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#ቤኒሻንጉል_ጉሙዝ

" በጸጥታ ችግር በሙሉና በከፊል የወደሙ 287 ትምህርት ቤቶች ለ2016 የትምህርት ዘመን ጥገና ያስፈልጋቸዋል" ሲል የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ዘነበ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ "በጸጥታ ችግር በሙሉና በከፊል የወደሙ 287 ትምህርት ቤቶች ለ2016 የትምህርት ዘመን ጥገና ያስፈልጋቸዋል" ብለዋል።

"እንደሚታወቀው ክልሉ ከዚህ በፊት መተከልና ከማሽ ዞኖች አካባቢ የነበረውን የጸጥታ ችግር ተከትሎ በሙሉና በከፊል የወደሙ ትምህርት ቤቶች አሉ" ያሉት አቶ ምትኩ፣ "እነዚህን ትምህርት ቤቶች መልሶ የመገንባት አሁን ማኅበረሰቡ የጀመረው ሥራ አለ። መንግሥትም ደግሞ ራሱን አስችሎ ከባለ ሃብቶች፣ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ገንዘብ በማሰባሰብ ትምህርት ቤቶችን የመጠገን ሁኔታ አለ" ሲሉ ተናግረዋል።

ወደሙ የተባሉት ተቋማት የት አካባቢ እንደሆነ እንዲያብራሩ ሲጠየቁም፣ በከማሽ፣ መተከል ዞኖች እዲሁም በማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ መሆኑን ገልጸው፣ የወደሙት ትምህርት ቤቶች ብላክ ብርድ፣ ወንበር፣ ቤተ መጻሕፍት፣ አጋዥ መጻሕፍት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ውድመቱን ተከትሎ ምን ያህል ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ እንደሆኑ እንዲገልጹ ላቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ምትኩ፣ "ወደ 50ሺሕ ገደማ ሕፃናት ናቸው በዚህ ችግር ከትምህርት ገበታ ውጭ የሆኑት" ብለዋል።
50 ሺሕ ገደማ ሕፃናት ሲባል በተለያዩ ምክንያቶች ለምሳሌ ቤተሰቦቻቸው በኢኮኖሚ ችግር ላይ በመሆናቸውና አብዛኛዎቹ ግን በአካባቢው ተፈጥሮ በነበረው የጸጥታ ችግር ከትምህርት ገበታ ውጭ የሆኑ ናቸው ሲሉ አክለዋል።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በጸጥታ ችግር ደረሰ ከተባለው የትምህርት ቤቶች ውድመት በተጨማሪ በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በትግራይ ክልል ትምህርት ቤቶች በመውደማቸው 2.4 ሚሊዮን ሕጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸውን፣ 1,218 ትምህርት ቤቶች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ቢከፈቱም 722ቱ እንዳልተከፈቱ መረጃዎች የክልሉ ትምህርት ቢሮ በተለያዩ ወቅቶች ሲገልጽ ተስተውሏል።

በአፋር ክልል ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዘ ሙሉ ለሙሉ ከወደሙ 65 ትምህርት ቤቶች አምስቱ መልሶ ግንባታ እንደተደረገላቸው፣ በከፊል ከወደሙት 694 ትምህርት ቤቶች መካከል 34ቱ እንደተጠገኑ እንዲሁም በ2016 የትምህርት ዘመን ይመዘገባሉ ተብሎ ከታቀደው 245 ሺሕ ተማሪዎች እስከ ባለፈው ሳምንት ድረስ የተመዘገቡት 126 ሺሕ ተማሪዎች መሆናቸው ተመላክቶ ነበር።

ያንብቡ - https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-10-09

@tikvahethiopia