TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ ፦ የብፁዕ አቡነ ሰላማ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያምና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ተፈፀመ።
የብፁዕነታቸው ስርዓተ ቀብር የተፈፀመው በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጸሎተኛው ፣ ደጉ፣ ርህሩሁና ታጋሹ አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ሰላማ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በአዲስ አበባ ሀሌሉያ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንዳሉ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ማሳወቋ ይታወሳል።
የፎቶ ባለቤት ፡ የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት
@tikvahethiopia
የብፁዕነታቸው ስርዓተ ቀብር የተፈፀመው በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጸሎተኛው ፣ ደጉ፣ ርህሩሁና ታጋሹ አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ሰላማ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በአዲስ አበባ ሀሌሉያ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንዳሉ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ማሳወቋ ይታወሳል።
የፎቶ ባለቤት ፡ የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት
@tikvahethiopia
ይቆጥቡ፤ ይጓዙ!
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ
==============
ደንበኞች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ አስቀድመው መቆጠብ እንዲችሉ የተዘጋጀ የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ ከብር 1,000 ጀምሮ ይከፈታል፡፡
የቁጠባ ሂሳቡ የተለያዩ ጥቅሞች ያስገኛል፡፡
• ቆጣቢዎች በሀገር ወስጥ ጉዟቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ተጠቅመው ለአየር ትኬት፣ ለቱሪስት መዳረሻዎች መግቢያ፣ ለሆቴል አገልግሎት እና ለመሳሰሉት ክፍያ በሚፈፅሙበት ወቅት ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ዳያስፖራ ወይም የውጭ ሀገር ዜጎች የሲቢኢ ቱሪስት ካርድን ሲጠቀሙ እስከ 7 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ ፤
• ለሀይማኖታዊ ጉዳይ ወደ ውጭ ሀገራት የሚጓዙ ደንበኞች ከአየር ትኬት ክፍያቸው እስከ 3 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችንም ያስገኛል፡፡
ሂሳቡን በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ፤ ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ይደውሉ!
https://t.iss.one/combankethofficial
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ
==============
ደንበኞች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ አስቀድመው መቆጠብ እንዲችሉ የተዘጋጀ የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ ከብር 1,000 ጀምሮ ይከፈታል፡፡
የቁጠባ ሂሳቡ የተለያዩ ጥቅሞች ያስገኛል፡፡
• ቆጣቢዎች በሀገር ወስጥ ጉዟቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ተጠቅመው ለአየር ትኬት፣ ለቱሪስት መዳረሻዎች መግቢያ፣ ለሆቴል አገልግሎት እና ለመሳሰሉት ክፍያ በሚፈፅሙበት ወቅት ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ዳያስፖራ ወይም የውጭ ሀገር ዜጎች የሲቢኢ ቱሪስት ካርድን ሲጠቀሙ እስከ 7 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ ፤
• ለሀይማኖታዊ ጉዳይ ወደ ውጭ ሀገራት የሚጓዙ ደንበኞች ከአየር ትኬት ክፍያቸው እስከ 3 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችንም ያስገኛል፡፡
ሂሳቡን በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ፤ ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ይደውሉ!
https://t.iss.one/combankethofficial
#የመንገድ_ጥያቄ
ከሀላባ-ደንቦያ-ዱራሜ-አንጋጫ-ዋቶ ያለው የ65 ኪሎ ሜትር የመንገድ ኘሮጀክት ባለመሰራቱና ባለመጠናቀቁ ህዝቡ ክፉኛ እየተቸገረ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ቅሬታ አቅርበዋል።
አስተያየታቸው የላኩን አንድ ነዋሪ ፤ ለከምባታ ህዝብ ብቸኛ መተንፈሻ የሆነው ከሀላባ - ደንቦያ - ዱራሜ - አንጋጫ-ዋቶ ያለው የ65 ኪሎ ሜትር የመንገድ ኘሮጀክት ባለመጠናወቁ ህዝቡ እየተቸገረ ነው ብለዋል።
" የመንገዱን ስራ ለመስራትና ለማጠናቀቅ በየዓመቱ ሙከራ ከማድረግ ውጪ የረባ ተግባራዊ ጥረት አልተደረገም " ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
ሌላ አስተያየይ የተቀበልናቸው አንድ ነዋሪ በዚህ መንገድ አለመሰራት ሳቢያ ህዝቡ ክፉኛ እየተሰቃየ ነው ብለዋል።
በመንገዱ አለመሰራት ምክንያት የሚደርሰውን ችግር እንዲሁ በቃላት ለመግለፅ እንደሚያዳግት አስረድተዋል።
የሚመለከተው አካል መንገዱን ለመስራት እና ለማጠናቀቅ ያልተቻለበትን ምክንያት በዝርዝር በመፈተሽ ፈጣን መፍትሄ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ህዝብ በሚንገላታበት የመንገድ ፕሮጀክት ዙሪያ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ጥረት ያደርጋል።
@tikvahethiopia
ከሀላባ-ደንቦያ-ዱራሜ-አንጋጫ-ዋቶ ያለው የ65 ኪሎ ሜትር የመንገድ ኘሮጀክት ባለመሰራቱና ባለመጠናቀቁ ህዝቡ ክፉኛ እየተቸገረ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ቅሬታ አቅርበዋል።
አስተያየታቸው የላኩን አንድ ነዋሪ ፤ ለከምባታ ህዝብ ብቸኛ መተንፈሻ የሆነው ከሀላባ - ደንቦያ - ዱራሜ - አንጋጫ-ዋቶ ያለው የ65 ኪሎ ሜትር የመንገድ ኘሮጀክት ባለመጠናወቁ ህዝቡ እየተቸገረ ነው ብለዋል።
" የመንገዱን ስራ ለመስራትና ለማጠናቀቅ በየዓመቱ ሙከራ ከማድረግ ውጪ የረባ ተግባራዊ ጥረት አልተደረገም " ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
ሌላ አስተያየይ የተቀበልናቸው አንድ ነዋሪ በዚህ መንገድ አለመሰራት ሳቢያ ህዝቡ ክፉኛ እየተሰቃየ ነው ብለዋል።
በመንገዱ አለመሰራት ምክንያት የሚደርሰውን ችግር እንዲሁ በቃላት ለመግለፅ እንደሚያዳግት አስረድተዋል።
የሚመለከተው አካል መንገዱን ለመስራት እና ለማጠናቀቅ ያልተቻለበትን ምክንያት በዝርዝር በመፈተሽ ፈጣን መፍትሄ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ህዝብ በሚንገላታበት የመንገድ ፕሮጀክት ዙሪያ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ጥረት ያደርጋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ማስታወሻ
ብሔራዊ የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና / Graduate Admission Test ከመስከረም 28 እስከ 30/2016 ዓ.ም በበይነ-መረብ ይሰጣል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምርምር ኢንስቲትዩት- የፈተና ማዕከል ጋር በመተባበር የሚሰጠው ፈተና በተጠቀሱት ቀናት በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ይከናወናል።
ለፈተናው የተመረጡ ተፈታኞች ከመስከረም 21 እስከ 25/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው የGAT መመዝገቢያ ፖርታል https://portal.aau.edu.et ላይ ምዝገባ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
ከመስከረም 23 እስከ 25/2016 ዓ.ም ባሉት ቀናት የሙከራ ፈተና ይሰጣል።
(ለመመዝገብ እና ፈተናውን ለመውሰድ የይለፍ ቲኬት ለማግኘት ሊከተሏቸው የሚገቡ ቅደም-ተከተሎች ከላይ ተያይዟል።)
Via @tikvahuniversity
ብሔራዊ የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና / Graduate Admission Test ከመስከረም 28 እስከ 30/2016 ዓ.ም በበይነ-መረብ ይሰጣል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምርምር ኢንስቲትዩት- የፈተና ማዕከል ጋር በመተባበር የሚሰጠው ፈተና በተጠቀሱት ቀናት በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ይከናወናል።
ለፈተናው የተመረጡ ተፈታኞች ከመስከረም 21 እስከ 25/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው የGAT መመዝገቢያ ፖርታል https://portal.aau.edu.et ላይ ምዝገባ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
ከመስከረም 23 እስከ 25/2016 ዓ.ም ባሉት ቀናት የሙከራ ፈተና ይሰጣል።
(ለመመዝገብ እና ፈተናውን ለመውሰድ የይለፍ ቲኬት ለማግኘት ሊከተሏቸው የሚገቡ ቅደም-ተከተሎች ከላይ ተያይዟል።)
Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
" በቁጥጥር ሥር የዋሉት ታርጋ በሌለው መኪና እና ምንም ዓይነት የእሥር ማዘዣ ወረቀት ባልቀረበበት ሁኔታ ነው " - ኢዜማ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሊቀመንበሩ ዶ/ር ጫኔ ከበደ ትላንት መስከረም 13/2016 ዓ.ም በፀጥታ አካላት ቁጥጥር ስር እንደዋሉ አሳወቀ። ፓርቲው ዶ/ር ጫኔ ፤ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ታርጋ በሌለው መኪና እና ምንም ዓይነት የእሥር ማዘዣ ወረቀት ባልቀረበበት ሁኔታ…
" የሊቀ-መንበሬ እስር በፓርቲው ባላቸው ኃላፊነት አይደለም " - ኢዜማ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የፖርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ጫኔ ከበደ በቁጥጥር ስር የዋሉት በፓርቲው ባላቸው ኃላፊነት ሳይሆን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በኮማንድ ፖስቱ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉ መሆኑን ገልጿል።
ከሊቀመንበሩ እስር በኋላ የብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚው ኮሚቴው መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ማድረጉን የጠቀሰው መግለጫው "ከድርጅቱ ዓላማ እና የትግል መስመር ባፈነገጠ መንገድ በሚንቀሳቀሱ አባላቱ ላይ የፀና አቋም ይይዛል።" ሲል አስታውቋል።
"ኢዜማ ከሰላማዊ የትግል ስልት ውጪ በዘውጌ ብሔርተኝነትም ሆነ አፈሙዝ በታከለበት የትግል መንገድ መንቀሳቀስን ድርጅቱ የቆመበትን መርኅ መቃረን አድርጎ ያየዋል። ማንኛውም የኢዜማ አባል ብሎም ከወረዳ እስከ ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ድረስ የሚሳተፍ አመራር ከዚህ የድርጅቱ ፅኑ ዕምነት ውጭ የተንቀሳቀሰ እንደሆነ ድርጅቱን ለማፍረስ እንደሚሰራ ተደርጎ እንደሚቆጠር መታወቅ አለበት።" ሲል መግለጫው ይጠቅሳል።
የፖርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ጫኔ ከበደ ከሰላማዊ ትግል እና ከዜግነት ፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ውጭ ያለን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከመደገፍ፣ በሀሳብም ሆነ የተግባር ተሳትፎም ሆነ ትብብር ማድረግ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁሟል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የፖርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ጫኔ ከበደ በቁጥጥር ስር የዋሉት በፓርቲው ባላቸው ኃላፊነት ሳይሆን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በኮማንድ ፖስቱ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉ መሆኑን ገልጿል።
ከሊቀመንበሩ እስር በኋላ የብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚው ኮሚቴው መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ማድረጉን የጠቀሰው መግለጫው "ከድርጅቱ ዓላማ እና የትግል መስመር ባፈነገጠ መንገድ በሚንቀሳቀሱ አባላቱ ላይ የፀና አቋም ይይዛል።" ሲል አስታውቋል።
"ኢዜማ ከሰላማዊ የትግል ስልት ውጪ በዘውጌ ብሔርተኝነትም ሆነ አፈሙዝ በታከለበት የትግል መንገድ መንቀሳቀስን ድርጅቱ የቆመበትን መርኅ መቃረን አድርጎ ያየዋል። ማንኛውም የኢዜማ አባል ብሎም ከወረዳ እስከ ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ድረስ የሚሳተፍ አመራር ከዚህ የድርጅቱ ፅኑ ዕምነት ውጭ የተንቀሳቀሰ እንደሆነ ድርጅቱን ለማፍረስ እንደሚሰራ ተደርጎ እንደሚቆጠር መታወቅ አለበት።" ሲል መግለጫው ይጠቅሳል።
የፖርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ጫኔ ከበደ ከሰላማዊ ትግል እና ከዜግነት ፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ውጭ ያለን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከመደገፍ፣ በሀሳብም ሆነ የተግባር ተሳትፎም ሆነ ትብብር ማድረግ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁሟል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#ሲዳማ
የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ባወጣው መግለጫ ማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም ህብረተሰቡ የሚረብሹ አካላትን ሲያስጠነቅቅ ተቃዋሚው የሲዳማ ፊደራሊስት ፓርቲ በበኩሉ የቢሮው ሰሞነኛ መግለጫ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመሸፋፈን በር የሚከፍት ነዉ ብሎታል።
የሲዳማ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ምንድነው ያለው ?
ቢሮው ፤ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታ ግብረሃይል ወቅታዊ ክልላዊና የሀገራዊ ፀጥታ በተመለከተ ውይይት ማድረጉን ገልጿል።
ግብረኃይሉ በክልሉ አንዳንድ ግለሰቦች በክልሉ መንግሥትና በሕብረተሰቡ መካከል ጥርጣሬ ለመፈጠር፣ በተለያዩ ማህበራዊ ሚድያዎችን በመጠቀም፣ ሀሰተኛ መረጃዎች በማሰራጨት ላይ ናቸው ብሏል።
የክልሉ መንግሥት በተለያዩ ጊዜ እንዲህ አይነት ድርጊት ውስጥ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ተሳታፊ የሆኑ አካላት ከድርጊታቸው እንዲመለሱ ቢነገራቸውም መመለስ ባለመቻላቸው የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ ሲባል በየደረጃው የሚገኙ ፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ህግ የማስከበር ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አሳስቧል።
መንግሥት ህግን ለማሰከር በሚወስደው እርምጃ ጣልቃ ለመግባት የሚሞክሩ አካላት ከወዲሁ መጠንቀቅ ይገባቸዋል ብሏል።
ከፀጥታ ቢሮው በተጨማሪ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ትላንት አንድነትን በሰበኩ አፋቸው ዛሬ ጎሰኝነት እየሰበኩ በማህበራዊ ሚድያ ሀሰተኛ ወሬ እያሰራጩ ህብረተሰቡ ሳይወክላቸው ለግል ጥቅማቸው ከውጭና ከውስጥ ተልዕኮ ተቀብሎ እኩይ ተግባራቸው ለመፈጸም የሚንቀሳቀሱ አካላት አሉ ያለ ሲሆን እነዚህን አካላት የክልሉ መንግሥት አይታገሳቸውም ብሏል።
የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ፤ የክልሉ ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ ያወጣው መግለጫ ልክ እንዳልሆነና በክልሉ ዉስጥ ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመሸፋፈን በር የሚከፍት ነዉ ብሏል።
ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸዉን የሰጡት የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊዉ አቶ ገነነ ሀሳና ፤ ይህ የክልሉ መንግስት አካሄድ በሶሻል ሚዲያ የሚታገሉትን ወጣቶች ድምጽ በማፈን በመንግስት ስር ሆነዉ የህዝብን ሀብት የሚዘርፉ አካላትን ከለላ የሚሰጥ ነዉ ብለዋል።
አቶ ገነነ አክለዉም ካሁን በፊት በክልሉ የሚከሰቱ በርካታ ችግሮችን አስመልክተን ለሰላም ሚኒስትር ለፌደራል ፖሊስና ለምርጫ ቦርድ የተለያዩ ደብዳቤዎችን ፅፈናል ያሉ ሲሆን አሁንም የክልሉ መንግስት እየሄደበት ያለዉን መንገድ ለማስተካከል እንደሚጥሩ ገልጸዋል።
ካሁን በፊት ለሚጽፉት የቅሬታ ደብዳቤዎች ፈጣን ምላሽ የሚያገኙት ከምርጫ ቦርድ መሆኑን የሚያነሱት ሀላፊዉ አሁን ላይ ከሌሎችም ሚኒስትር መስሪያቤቶች ጋር በመነጋገር ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።
@tikvahethiopia
የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ባወጣው መግለጫ ማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም ህብረተሰቡ የሚረብሹ አካላትን ሲያስጠነቅቅ ተቃዋሚው የሲዳማ ፊደራሊስት ፓርቲ በበኩሉ የቢሮው ሰሞነኛ መግለጫ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመሸፋፈን በር የሚከፍት ነዉ ብሎታል።
የሲዳማ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ምንድነው ያለው ?
ቢሮው ፤ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታ ግብረሃይል ወቅታዊ ክልላዊና የሀገራዊ ፀጥታ በተመለከተ ውይይት ማድረጉን ገልጿል።
ግብረኃይሉ በክልሉ አንዳንድ ግለሰቦች በክልሉ መንግሥትና በሕብረተሰቡ መካከል ጥርጣሬ ለመፈጠር፣ በተለያዩ ማህበራዊ ሚድያዎችን በመጠቀም፣ ሀሰተኛ መረጃዎች በማሰራጨት ላይ ናቸው ብሏል።
የክልሉ መንግሥት በተለያዩ ጊዜ እንዲህ አይነት ድርጊት ውስጥ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ተሳታፊ የሆኑ አካላት ከድርጊታቸው እንዲመለሱ ቢነገራቸውም መመለስ ባለመቻላቸው የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ ሲባል በየደረጃው የሚገኙ ፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ህግ የማስከበር ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አሳስቧል።
መንግሥት ህግን ለማሰከር በሚወስደው እርምጃ ጣልቃ ለመግባት የሚሞክሩ አካላት ከወዲሁ መጠንቀቅ ይገባቸዋል ብሏል።
ከፀጥታ ቢሮው በተጨማሪ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ትላንት አንድነትን በሰበኩ አፋቸው ዛሬ ጎሰኝነት እየሰበኩ በማህበራዊ ሚድያ ሀሰተኛ ወሬ እያሰራጩ ህብረተሰቡ ሳይወክላቸው ለግል ጥቅማቸው ከውጭና ከውስጥ ተልዕኮ ተቀብሎ እኩይ ተግባራቸው ለመፈጸም የሚንቀሳቀሱ አካላት አሉ ያለ ሲሆን እነዚህን አካላት የክልሉ መንግሥት አይታገሳቸውም ብሏል።
የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ፤ የክልሉ ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ ያወጣው መግለጫ ልክ እንዳልሆነና በክልሉ ዉስጥ ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመሸፋፈን በር የሚከፍት ነዉ ብሏል።
ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸዉን የሰጡት የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊዉ አቶ ገነነ ሀሳና ፤ ይህ የክልሉ መንግስት አካሄድ በሶሻል ሚዲያ የሚታገሉትን ወጣቶች ድምጽ በማፈን በመንግስት ስር ሆነዉ የህዝብን ሀብት የሚዘርፉ አካላትን ከለላ የሚሰጥ ነዉ ብለዋል።
አቶ ገነነ አክለዉም ካሁን በፊት በክልሉ የሚከሰቱ በርካታ ችግሮችን አስመልክተን ለሰላም ሚኒስትር ለፌደራል ፖሊስና ለምርጫ ቦርድ የተለያዩ ደብዳቤዎችን ፅፈናል ያሉ ሲሆን አሁንም የክልሉ መንግስት እየሄደበት ያለዉን መንገድ ለማስተካከል እንደሚጥሩ ገልጸዋል።
ካሁን በፊት ለሚጽፉት የቅሬታ ደብዳቤዎች ፈጣን ምላሽ የሚያገኙት ከምርጫ ቦርድ መሆኑን የሚያነሱት ሀላፊዉ አሁን ላይ ከሌሎችም ሚኒስትር መስሪያቤቶች ጋር በመነጋገር ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።
@tikvahethiopia