TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ኢትዮ ቴሌኮም 630 ሺ ደንበኞቹ ዛሬ ይፋ ያደረገውን የ5G ኔትወርኩን መጠቀም ይችላሉ ብሏል። ኢትዮ ቴሌኮም የ5ኛውን ትውልድ (5G) የሞባይል ኔትወርክ በሙከራ ደረጃ በአዲስ አበባ እንዲሁም በአዳማ ከተሞ በሙከራ ደረጃ ሲያቀርብ ቆይቶ ዛሬ በይፋ በአዲስ አበባ አገልግሎት ማስጀመሩን አስታውቋል። ኢትዮ ቴሌኮም የ5ኛውን ትውልድ (5G) የሞባይል ኔትወርክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሞከው በአዲስ አበባ…
የ5G ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎት ዋጋ ስንት ነው ?
ኢትዮ ቴሌኮም አሁን ላይ 81.8 ሚሊዮን ከኔትዎርክ የተገናኙ መሳሪያዎች መኖራቸውን ያሳወቀ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 42 በመቶ የሚሆነው ስማርት ስልኮች (Smart Phones) መሆናቸውን ገልጿል።
በተጠቃሚዎች ቁጥር ደግሞ 34.4 ሚሊዮን ሰዎች የኢንተርኔት ዳታ ተጠቃሚ ናቸው ያለው ተቋሙ፥ እነዚህ ደንበኞቹ በአማካይ በቀን 2,087 GB ዳታ ዝውውር (Average Daily data traffic) የሚፈጽሙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የ4G ተጠቃሚዎቹ 66 በመቶ የሚሆነውን እንደሚሸፍኑ አስታውቋል።
አዲሱ የኢትዮ ቴሌኮም የ5G ኔትዎርክ በአዲስ አበባ ከተማ በተወሰነ ክልል ለተጠቃሚዎች የቀረበ ሲሆን የራሱ የክፍያ ፖኬጆችም ተዘጋጅተውለታል።
ይህ የክፍያ ፖኬጅ ከዚህ በፊት ከነበሩት የኔትወርክ አገልግሎቶች (4G, 3G, 2G) የዋጋ #ጭማሪ ያለው ነው።
በዚህም ኢትዮ ቴሌኮም ወርኃዊ ያልተገደበ የ5G አገልግሎቱን በ1,199 ብር እና በ300 GB ፍትሃዊ የአጠቃቀም ፖሊሲ ባለው (FUP) እንዲሁም ፕሪሚየም የተሰኘውን ወርኃዊ ያልተገደበ ጥቅሉን በ1,299 ብር በ400 GB ፍትሃዊ የአጠቃቀም ፖሊሲ ባለው (FUP) ለተጠቃሚዎች አድርሷል።
ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮ ቴሌኮም ያልተገደበ 150 GB የ5G ኢንተርኔት በ929 ብር እንዲሁም 250 GB ደግሞ 979 በር ለተጠቃሚዎች አቅርቧል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከዚህ ቀደም በነበረው ኔትዎርክ ወርኃዊ ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎት በ999 ብር ለተጠቃሚዎች እንደሚያቀርብ ይታወሳል።
የ5G ኔትዎርክ አገልግሎት ለመጠቀም ምን ላድርግ ?
ኢትዮ ቴሌኮም አሁን ላይ 5G ኔትዎርክ መቀበል የሚችሉ መሳሪያዎችን የያዙ ደንበኞችን ልየታ አጠናቆ ወደ ኔቶርኩ እያስገባ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጸ ሲሆን በቀጣዮቹ ቀናት ይህ ሥራ እንደሚጠናቀቅም አሳውቋል።
በመሆኑም ደንበኞች ወደ ኢትዮ ቴሌኮም የሽያጭ ማዕከላት ሳይሄዱ አገልግሎቱን መጠቀም የሚችሉ መሆኑን የሚገልጽ የጹሑፍ መልዕክት የሚደርሳቸው ይሆናል ተብሏል።
ደንበኞች በራሳቸው ይህንን አገልግሎት ለመጠቀም መጀመሪያ የያዙት ስልክ ወይም ኢንተርኔት ማስጠቀም የሚችል ቁስ (Device) የ5G ኔትዎርክ መቀበል እንደሚችል መሆኑን ማረጋገጥ ይችላሉ።
NB : የፍትሃዊ አጠቃቀም ፖሊሲ (FUP) ማለት ኢንተርኔት አቅራቢዎች ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎቶችን አላግባብ የመጠቀምን ወይም የመተላለፊያ ይዘትን (Bandwidth) ከመጠን በላይ መጠቀምን ለመከላከል የሚያስችላቸውና ፍጥነትን የሚቀንሱበት አሰራር ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ይህንን ፖሊሲ ከዚህ ቀደም የሰዓት እና የቀን ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ላይ ተግባራዊ አድርጓል።
ፎቶ 1 ፦ ለተጠቃሚዎች የቀረበውን የዳታ ጥቅል የሚያሳይ
ፎቶ 2፦ የ5G አገልግሎት የተዘረጋባቸው አከባቢዎች የሚያሳይ
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም አሁን ላይ 81.8 ሚሊዮን ከኔትዎርክ የተገናኙ መሳሪያዎች መኖራቸውን ያሳወቀ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 42 በመቶ የሚሆነው ስማርት ስልኮች (Smart Phones) መሆናቸውን ገልጿል።
በተጠቃሚዎች ቁጥር ደግሞ 34.4 ሚሊዮን ሰዎች የኢንተርኔት ዳታ ተጠቃሚ ናቸው ያለው ተቋሙ፥ እነዚህ ደንበኞቹ በአማካይ በቀን 2,087 GB ዳታ ዝውውር (Average Daily data traffic) የሚፈጽሙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የ4G ተጠቃሚዎቹ 66 በመቶ የሚሆነውን እንደሚሸፍኑ አስታውቋል።
አዲሱ የኢትዮ ቴሌኮም የ5G ኔትዎርክ በአዲስ አበባ ከተማ በተወሰነ ክልል ለተጠቃሚዎች የቀረበ ሲሆን የራሱ የክፍያ ፖኬጆችም ተዘጋጅተውለታል።
ይህ የክፍያ ፖኬጅ ከዚህ በፊት ከነበሩት የኔትወርክ አገልግሎቶች (4G, 3G, 2G) የዋጋ #ጭማሪ ያለው ነው።
በዚህም ኢትዮ ቴሌኮም ወርኃዊ ያልተገደበ የ5G አገልግሎቱን በ1,199 ብር እና በ300 GB ፍትሃዊ የአጠቃቀም ፖሊሲ ባለው (FUP) እንዲሁም ፕሪሚየም የተሰኘውን ወርኃዊ ያልተገደበ ጥቅሉን በ1,299 ብር በ400 GB ፍትሃዊ የአጠቃቀም ፖሊሲ ባለው (FUP) ለተጠቃሚዎች አድርሷል።
ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮ ቴሌኮም ያልተገደበ 150 GB የ5G ኢንተርኔት በ929 ብር እንዲሁም 250 GB ደግሞ 979 በር ለተጠቃሚዎች አቅርቧል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከዚህ ቀደም በነበረው ኔትዎርክ ወርኃዊ ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎት በ999 ብር ለተጠቃሚዎች እንደሚያቀርብ ይታወሳል።
የ5G ኔትዎርክ አገልግሎት ለመጠቀም ምን ላድርግ ?
ኢትዮ ቴሌኮም አሁን ላይ 5G ኔትዎርክ መቀበል የሚችሉ መሳሪያዎችን የያዙ ደንበኞችን ልየታ አጠናቆ ወደ ኔቶርኩ እያስገባ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጸ ሲሆን በቀጣዮቹ ቀናት ይህ ሥራ እንደሚጠናቀቅም አሳውቋል።
በመሆኑም ደንበኞች ወደ ኢትዮ ቴሌኮም የሽያጭ ማዕከላት ሳይሄዱ አገልግሎቱን መጠቀም የሚችሉ መሆኑን የሚገልጽ የጹሑፍ መልዕክት የሚደርሳቸው ይሆናል ተብሏል።
ደንበኞች በራሳቸው ይህንን አገልግሎት ለመጠቀም መጀመሪያ የያዙት ስልክ ወይም ኢንተርኔት ማስጠቀም የሚችል ቁስ (Device) የ5G ኔትዎርክ መቀበል እንደሚችል መሆኑን ማረጋገጥ ይችላሉ።
NB : የፍትሃዊ አጠቃቀም ፖሊሲ (FUP) ማለት ኢንተርኔት አቅራቢዎች ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎቶችን አላግባብ የመጠቀምን ወይም የመተላለፊያ ይዘትን (Bandwidth) ከመጠን በላይ መጠቀምን ለመከላከል የሚያስችላቸውና ፍጥነትን የሚቀንሱበት አሰራር ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ይህንን ፖሊሲ ከዚህ ቀደም የሰዓት እና የቀን ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ላይ ተግባራዊ አድርጓል።
ፎቶ 1 ፦ ለተጠቃሚዎች የቀረበውን የዳታ ጥቅል የሚያሳይ
ፎቶ 2፦ የ5G አገልግሎት የተዘረጋባቸው አከባቢዎች የሚያሳይ
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
👍1.09K👎397❤165🙏31😱23🕊11😢9🥰8
#ሞሮኮ
እጅግ አስደንጋጭ ነው በተባለው የሞሮኮ መሬት መንቀጥቀጥ ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች ሞቱ።
በሞሮኮ በመሬት መንቀጥቀጥ እስካሁን ባለው 1,305 ሰዎች መሞታቸው ታውቋል።
ቢቢሲ ኒውስ ፤ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴርን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው የተከሰተው 6.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ሲሆን በዚህም እጅግ በጣም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በዋነኛነት የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው በአትላስ ተራራ አካባቢ ነው ተብሏል።
ይህም ከማራኬሽ በደቡብ ምዕራብ 71 ኪሎ ሜትር ርቆ ይገኛል። ጥልቀቱም 18.5 ኪሎ ሜትር ነው። በማራኬሽና በሌሎችም ደቡባዊ አካባቢዎች ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።
አል-ሀውዝ፣ ማራኬሽ፣ ኦራዛቴ፣ አዚል፣ ክሪቾዋ እና ታራውዳንት በተባሉት አካባቢዎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል።
በመሬት መንቀጥቀጡ ሕንጻዎችና ጎዳናዎች ሲናዱ ታይተዋል።
ሞሮኮ በደረሰው አደጋ የ3 ቀን ሀዘን አውጃለች።
በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት በደረሰው ጉዳት የኢትዮጵያ መሪን ጨምሮ የሀገራትና ተቋማት መሪዎች ሀዘናቸውን እና ለሞሮኮ ህዝብ ያላቸውን አጋርነት እየገለፁ ይገኛሉ።
NB. የሟቾች ቁጥር አሁን ካለውም ይጨምራል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopia
እጅግ አስደንጋጭ ነው በተባለው የሞሮኮ መሬት መንቀጥቀጥ ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች ሞቱ።
በሞሮኮ በመሬት መንቀጥቀጥ እስካሁን ባለው 1,305 ሰዎች መሞታቸው ታውቋል።
ቢቢሲ ኒውስ ፤ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴርን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው የተከሰተው 6.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ሲሆን በዚህም እጅግ በጣም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በዋነኛነት የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው በአትላስ ተራራ አካባቢ ነው ተብሏል።
ይህም ከማራኬሽ በደቡብ ምዕራብ 71 ኪሎ ሜትር ርቆ ይገኛል። ጥልቀቱም 18.5 ኪሎ ሜትር ነው። በማራኬሽና በሌሎችም ደቡባዊ አካባቢዎች ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።
አል-ሀውዝ፣ ማራኬሽ፣ ኦራዛቴ፣ አዚል፣ ክሪቾዋ እና ታራውዳንት በተባሉት አካባቢዎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል።
በመሬት መንቀጥቀጡ ሕንጻዎችና ጎዳናዎች ሲናዱ ታይተዋል።
ሞሮኮ በደረሰው አደጋ የ3 ቀን ሀዘን አውጃለች።
በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት በደረሰው ጉዳት የኢትዮጵያ መሪን ጨምሮ የሀገራትና ተቋማት መሪዎች ሀዘናቸውን እና ለሞሮኮ ህዝብ ያላቸውን አጋርነት እየገለፁ ይገኛሉ።
NB. የሟቾች ቁጥር አሁን ካለውም ይጨምራል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopia
😢3.23K👍788❤178🕊145😱73🙏60🥰25👎21
#CBE
እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳቸሁ!
===========
የበዓል ሸመታዎን
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ POS ማሽኖች ይፈፅሙ!
መልካም በአል ይሁንላችሁ!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#commercialbankofethiopia #digitalbanking #Ethiopia
እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳቸሁ!
===========
የበዓል ሸመታዎን
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ POS ማሽኖች ይፈፅሙ!
መልካም በአል ይሁንላችሁ!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#commercialbankofethiopia #digitalbanking #Ethiopia
👍140👎38❤16😱7🥰3🕊3👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#GERD🇪🇹
" በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ
ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው ፣ በፀሎታቸው በስራው ለተሳተፉ ምስጋና አቅርበው " እንኳን ደስ አላችሁ " ብለዋል።
ለኢዜአ ቃላቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን መሪና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዳግሞ ፤ ባለፉት 4 ዓመታት የውሃ ሙሌት ስራውን ለማከናወን የሚያስችል በቂ የዝናብ መጠን መገኘቱን አስረድተዋል።
የውሃ ሙሌት ስራው በታችኛው ተፋሰስ አገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት በማያደርስ መልኩ መከናወኑን ገልጸዋል።
ለአብነትም በዘንድሮው ክረምት በግብጽ የሚገኘው የአሰዋን ግድብ ከበቂ በላይ ውሃ በመያዙ ምክንያት በግድቡ ማስተንፈሻ አማካኝነት ውሃ የማፋሰስ ስራ ሲያከናወን መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡
ይህም ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስቱ አገራት የትብብር ምንጭ ከመሆን ባሻገር በታችኛው ተፋሰስ አገራት የሚያስከትለው ጉዳት እንደሌለ በተግባር ያመላከተ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡
አሁን ላይ ኃይል ማመንጨት የጀመሩት ሁለቱ ተርባይኖች በስራ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ እንደሚገቡ አሳውቀዋል።
4ኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ በግድቡ ግንባታ ሂደት ሌላኛውን አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑንም ገልጸዋል።
ከዚህ በኋላ የሚኖሩት ስራዎች ከዚህ ቀደም ከተለፈባቸው የተሻሉ እንደሚሆኑ የጠቀሱት ዶ/ር ኢንጅነር ስለሺ ፤ " ይህ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ስኬት ነው " ብለዋል፡፡
@tikvahethiopia
" በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ
ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው ፣ በፀሎታቸው በስራው ለተሳተፉ ምስጋና አቅርበው " እንኳን ደስ አላችሁ " ብለዋል።
ለኢዜአ ቃላቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን መሪና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዳግሞ ፤ ባለፉት 4 ዓመታት የውሃ ሙሌት ስራውን ለማከናወን የሚያስችል በቂ የዝናብ መጠን መገኘቱን አስረድተዋል።
የውሃ ሙሌት ስራው በታችኛው ተፋሰስ አገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት በማያደርስ መልኩ መከናወኑን ገልጸዋል።
ለአብነትም በዘንድሮው ክረምት በግብጽ የሚገኘው የአሰዋን ግድብ ከበቂ በላይ ውሃ በመያዙ ምክንያት በግድቡ ማስተንፈሻ አማካኝነት ውሃ የማፋሰስ ስራ ሲያከናወን መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡
ይህም ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስቱ አገራት የትብብር ምንጭ ከመሆን ባሻገር በታችኛው ተፋሰስ አገራት የሚያስከትለው ጉዳት እንደሌለ በተግባር ያመላከተ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡
አሁን ላይ ኃይል ማመንጨት የጀመሩት ሁለቱ ተርባይኖች በስራ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ እንደሚገቡ አሳውቀዋል።
4ኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ በግድቡ ግንባታ ሂደት ሌላኛውን አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑንም ገልጸዋል።
ከዚህ በኋላ የሚኖሩት ስራዎች ከዚህ ቀደም ከተለፈባቸው የተሻሉ እንደሚሆኑ የጠቀሱት ዶ/ር ኢንጅነር ስለሺ ፤ " ይህ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ስኬት ነው " ብለዋል፡፡
@tikvahethiopia
👍1.29K👎201❤135🕊29🙏20😱9😢2
" በአዲሱ ዓመት የሰው ሕይወትን የሚቀጥፉ የመሳሪያ አፈ ሙዞች በሙሉ ወደ መጋዝን መግባት አለባቸው " - ቅዱስነታቸው
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2016 ዓመተ ምሕረት የዘመን መለወጫን በማስመልከት አባታዊ ቃለ በረከት አስተላለፉ።
ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦
" ... ያለፈው ዓመት ያሳረፈብንን ሁለንተናዊ ተጽዕኖ በሚገባ አስተውለን፣ ዳግም ወደ አዲሱ ዓመት እንዳይሸጋገርብን ካላደረግን አዲሱ ዓመት ለኛ የሚሰጠን ትርጉም ምንድን ነው ?
ባለፉት ዓመታት በሃይማኖት፣ በባህል በታሪክ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና ፖለቲካዊ እንዲሁም በሕዝባችን ሥር የሰደደውን የእርስ በርስ መጠራጠር ከልብ መርምረን ወደ ድሮው እኛነታችን ካልተመለከትንስ አዲስ ዘመን እያልን ማክበራችን ምን ፋይዳ አለው ?
ይህንን ሁሉ በአዲሱ ዓመት በማጤን ያለፈውን ጎጂ ነገር በመተው፤ ጠቃሚውን ግን ይበልጥ በማጠናከር አዲሱን ዓመት መቀበል አለብን።
ከሁሉ በላይ ለሀገራችንና ለሕዝባችን የሚጠቅመው ምንድነው ? በሚለው በምር መስራት አለብን፤ በመለያየት፣ በመፎካከር፣ በመበቃቀል፣ በመናናቅ፣ የራስን ጥቅም ብቻ ለማስጠበቅ በመጣር፣ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ኃይልን በመጠቀም፣ የሕዝብን ጥቅም ማስከበርና የሀገርን አንድነት ማስቀጠል አይቻልም ፤ ሀገራችንንና ሕዝባችንን ወደ ዕመቀ ዕመቅ እየከተቱ ያሉ እንደዚህ ያሉ አስተሳሰቦች ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ ከአሮጌው ዓመት ጋራ አብረው መወገድ አለባቸው።
በአዲሱ ዓመት የሰው ሕይወትን የሚቀጥፉ የመሳሪያ አፈ ሙዞች በሙሉ ወደ መጋዝን መግባት አለባቸው፤ ችግሮችን በውይይት፣ አሊያም በሕግ እየተፈቱ የሀገርና የሕዝብ ሉዓላዊነት ነጻነትና አንድነት መረጋገጥ አለበት፤ ሀገርንና ሕዝብን ለዘለቄታው በአንድነት የሚያስቀጥሉ የሕግ የበላይነትን ማክበር፣ እኩልነትን ማረጋገጥ፣ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ፣ የተጐዳውን መደገፍ፣ ሆድ የባሰውን ማለዘብ፣ የተጠቃውን ማጽናናት ሲቻል ነው፡፡
በአዲሱ ዓመት ይህንን ለማድረግ በቊርጥ ከተነሣን ሰላማችን ወደነበረበት ይመለሳል፡፡ ሀገራችንም በበረከት ትሞላለች፤ ስለዚህም ኢትዮጵያውያን የሆናችሁ ልጆቻችን ሁሉ ይህንን ጥሪያችንን ተቀብላችሁ የጥፋት መሳሪያችሁንም አስቀምጣችሁ ወደ ሰላም ማእድ ቀርባችሁ በወንድማማችነት መንፈስ ችግራችሁን በክብ ጠረጴዛ በውይይት በመፍታት የሀገሪቱንና የሕዝቡን አንድነት እንድታስቀጥሉ ሁሉን በሚያይ እግዚአብሔር ስም እንማጸናችኋለን፡፡ "
(ሙሉ መልዕክታቸውን ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2016 ዓመተ ምሕረት የዘመን መለወጫን በማስመልከት አባታዊ ቃለ በረከት አስተላለፉ።
ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦
" ... ያለፈው ዓመት ያሳረፈብንን ሁለንተናዊ ተጽዕኖ በሚገባ አስተውለን፣ ዳግም ወደ አዲሱ ዓመት እንዳይሸጋገርብን ካላደረግን አዲሱ ዓመት ለኛ የሚሰጠን ትርጉም ምንድን ነው ?
ባለፉት ዓመታት በሃይማኖት፣ በባህል በታሪክ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና ፖለቲካዊ እንዲሁም በሕዝባችን ሥር የሰደደውን የእርስ በርስ መጠራጠር ከልብ መርምረን ወደ ድሮው እኛነታችን ካልተመለከትንስ አዲስ ዘመን እያልን ማክበራችን ምን ፋይዳ አለው ?
ይህንን ሁሉ በአዲሱ ዓመት በማጤን ያለፈውን ጎጂ ነገር በመተው፤ ጠቃሚውን ግን ይበልጥ በማጠናከር አዲሱን ዓመት መቀበል አለብን።
ከሁሉ በላይ ለሀገራችንና ለሕዝባችን የሚጠቅመው ምንድነው ? በሚለው በምር መስራት አለብን፤ በመለያየት፣ በመፎካከር፣ በመበቃቀል፣ በመናናቅ፣ የራስን ጥቅም ብቻ ለማስጠበቅ በመጣር፣ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ኃይልን በመጠቀም፣ የሕዝብን ጥቅም ማስከበርና የሀገርን አንድነት ማስቀጠል አይቻልም ፤ ሀገራችንንና ሕዝባችንን ወደ ዕመቀ ዕመቅ እየከተቱ ያሉ እንደዚህ ያሉ አስተሳሰቦች ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ ከአሮጌው ዓመት ጋራ አብረው መወገድ አለባቸው።
በአዲሱ ዓመት የሰው ሕይወትን የሚቀጥፉ የመሳሪያ አፈ ሙዞች በሙሉ ወደ መጋዝን መግባት አለባቸው፤ ችግሮችን በውይይት፣ አሊያም በሕግ እየተፈቱ የሀገርና የሕዝብ ሉዓላዊነት ነጻነትና አንድነት መረጋገጥ አለበት፤ ሀገርንና ሕዝብን ለዘለቄታው በአንድነት የሚያስቀጥሉ የሕግ የበላይነትን ማክበር፣ እኩልነትን ማረጋገጥ፣ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ፣ የተጐዳውን መደገፍ፣ ሆድ የባሰውን ማለዘብ፣ የተጠቃውን ማጽናናት ሲቻል ነው፡፡
በአዲሱ ዓመት ይህንን ለማድረግ በቊርጥ ከተነሣን ሰላማችን ወደነበረበት ይመለሳል፡፡ ሀገራችንም በበረከት ትሞላለች፤ ስለዚህም ኢትዮጵያውያን የሆናችሁ ልጆቻችን ሁሉ ይህንን ጥሪያችንን ተቀብላችሁ የጥፋት መሳሪያችሁንም አስቀምጣችሁ ወደ ሰላም ማእድ ቀርባችሁ በወንድማማችነት መንፈስ ችግራችሁን በክብ ጠረጴዛ በውይይት በመፍታት የሀገሪቱንና የሕዝቡን አንድነት እንድታስቀጥሉ ሁሉን በሚያይ እግዚአብሔር ስም እንማጸናችኋለን፡፡ "
(ሙሉ መልዕክታቸውን ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
❤2.43K👍676🕊114👎101🙏92🥰38😱6😢4😡1
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 " በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው…
#GERD🇪🇹
ግድቡ ከዚህ በኃላ ውሃ አይዝም ?
" 4ኛና የመጨረሻው ሲባል ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት " - ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት መጠናቀቅን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የመጨረሻ ሙሌት " ሲሉ መግለፃቸውን ተከትሎ በርካቶች " ግድቡ ከአሁን በኃላ ውሃ አይዝም ? " የሚል ጥያቄ ፈጥሮባቸዋል።
ይህንን በተመለከተ ቃላቸውን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ የሰጡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ፦
" አራተኛና የመጨረሻው የውሃ ሙሌት የተባለው አራቱ ዙሮች ከፍተኛ የውሃ መጠን የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ነው።
በእነዚህ አራት ዙሮች ግድቡ መያዝ ያለበትን የውሃ መጠን መያዝ ችሏል።
አራተኛና የመጨረሻው ሲባልም ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት።
ይልቁንም ግድቡ #እየተጠናቀቀ በመሆኑ ፣ ከፍተኛ የውሃ መጠን ሳያስፈልግ ይከናወናል። "
Credit - Ethio FM 107.8
@tikvahethiopia
ግድቡ ከዚህ በኃላ ውሃ አይዝም ?
" 4ኛና የመጨረሻው ሲባል ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት " - ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት መጠናቀቅን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የመጨረሻ ሙሌት " ሲሉ መግለፃቸውን ተከትሎ በርካቶች " ግድቡ ከአሁን በኃላ ውሃ አይዝም ? " የሚል ጥያቄ ፈጥሮባቸዋል።
ይህንን በተመለከተ ቃላቸውን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ የሰጡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ፦
" አራተኛና የመጨረሻው የውሃ ሙሌት የተባለው አራቱ ዙሮች ከፍተኛ የውሃ መጠን የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ነው።
በእነዚህ አራት ዙሮች ግድቡ መያዝ ያለበትን የውሃ መጠን መያዝ ችሏል።
አራተኛና የመጨረሻው ሲባልም ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት።
ይልቁንም ግድቡ #እየተጠናቀቀ በመሆኑ ፣ ከፍተኛ የውሃ መጠን ሳያስፈልግ ይከናወናል። "
Credit - Ethio FM 107.8
@tikvahethiopia
👍13.3K👎368❤163🕊35😢23😱20🙏18🥰8😡1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የኛ በሆነው አዲስ ዓመት በአዲስ ተስፋ እንደ አደይ ፈክተን ማርሻችንን ወደላቀ ስኬት እንቀይር!
መልካም አዲስ ዓመት።
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
መልካም አዲስ ዓመት።
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
👍158❤32👎20🥰15🙏11🕊7😢2😱1