#አሜሪካ
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አንደኛ ዓመትን አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል።
አንቶኒ ብሊንከን ምን አሉ ?
- ብሊንከን በደፈናው #ኢትዮጵያ እና #ኤርትራ ጠብ ከሚያጭሩ ድርጊቶች እንዲቆጠቡና የአካባቢውን አገራት ነጻነት፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ማክበር አለባቸው ብለዋል።
- የኤርትራ ኃይሎች ከትግራይ ክልል ሙሉ ለሙሉ መውጣትን እንዳለባቸው ገልጸዋል።
- ስምምነቱን ተከትሎ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መመሥረቱን ጨምሮ የተወሰዱ በጎ እርምጃዎችን አሜሪካ እንደምትደግፍ አሳውቀዋል።
- ህወሓት ኃይሎቹ ከባድ መሳሪያቸውን ፈትተው ተዋጊዎች ማሰናበት በተጀመረበት ጊዜ በትግራይ ውስጥ ዘላቂ ሰላም ለማስፍን ተጨማሪ እርምጃዎች መውሰድ ያስፈልጋል። ለዚህም የኤርትራ ኃይሎች ሙሉ ለሙሉ መውጣት አለባቸው ብለዋል።
- ብሊንከን አሜሪካ በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎችም አካባቢዎች ያሉት ግጭቶች እንደሚያሳስባት ገልጸዋል። ያለው ነገር በቀላሉ ሊታወክ የሚችለውን የኢትዮጵያን ሰላም አደጋ ላይ እንደጣለው አመልክተዋል።
- በአገሪቱ በተለያዩ ወገኖች የቀጠለው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና ጥቃት፣ " የመርዛማ ንግግሮች " መስፋፋት በጦርነቱ ምክንያት የሳሳውን ማኅበራዊ ትስስር የበለጠ እየሸረሸረው መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ፦
🔹አስተማማኝ የሽግግር ፍትሕ፣
🔹ሐቀኛ እና አካታች ብሔራዊ ምክክር በመላዋ አገሪቱ ተግባራዊ እንዲሆን እንዲሁም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የሚካሄዱትን ግጭቶች ለመፍታት ውይይት እንዲደረግ አስቸኳይ ጥሪ አቅርበዋል።
#BBC
#SecretaryofStateAntonyJBlinken
@tikvahethiopia
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አንደኛ ዓመትን አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል።
አንቶኒ ብሊንከን ምን አሉ ?
- ብሊንከን በደፈናው #ኢትዮጵያ እና #ኤርትራ ጠብ ከሚያጭሩ ድርጊቶች እንዲቆጠቡና የአካባቢውን አገራት ነጻነት፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ማክበር አለባቸው ብለዋል።
- የኤርትራ ኃይሎች ከትግራይ ክልል ሙሉ ለሙሉ መውጣትን እንዳለባቸው ገልጸዋል።
- ስምምነቱን ተከትሎ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መመሥረቱን ጨምሮ የተወሰዱ በጎ እርምጃዎችን አሜሪካ እንደምትደግፍ አሳውቀዋል።
- ህወሓት ኃይሎቹ ከባድ መሳሪያቸውን ፈትተው ተዋጊዎች ማሰናበት በተጀመረበት ጊዜ በትግራይ ውስጥ ዘላቂ ሰላም ለማስፍን ተጨማሪ እርምጃዎች መውሰድ ያስፈልጋል። ለዚህም የኤርትራ ኃይሎች ሙሉ ለሙሉ መውጣት አለባቸው ብለዋል።
- ብሊንከን አሜሪካ በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎችም አካባቢዎች ያሉት ግጭቶች እንደሚያሳስባት ገልጸዋል። ያለው ነገር በቀላሉ ሊታወክ የሚችለውን የኢትዮጵያን ሰላም አደጋ ላይ እንደጣለው አመልክተዋል።
- በአገሪቱ በተለያዩ ወገኖች የቀጠለው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና ጥቃት፣ " የመርዛማ ንግግሮች " መስፋፋት በጦርነቱ ምክንያት የሳሳውን ማኅበራዊ ትስስር የበለጠ እየሸረሸረው መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ፦
🔹አስተማማኝ የሽግግር ፍትሕ፣
🔹ሐቀኛ እና አካታች ብሔራዊ ምክክር በመላዋ አገሪቱ ተግባራዊ እንዲሆን እንዲሁም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የሚካሄዱትን ግጭቶች ለመፍታት ውይይት እንዲደረግ አስቸኳይ ጥሪ አቅርበዋል።
#BBC
#SecretaryofStateAntonyJBlinken
@tikvahethiopia
#ኤርትራ
ኤርትራ የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌላ ቤርቦክን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረን አውሮፕላንን ከአየር ክልሏ ማስወጣቷ ተነግሯል።
የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌላ ባየርቦክ ትላንት እንዳስታወቁት፤ ወደ ጂቡቲ ሲጓዝ የነበረው የጀርመን መንግስት አውሮፕላን ያለ እቅድ ሳዑዲ አረቢያ ለማረፍ መገደዱን ገልጸለዋል።
ይህ የሆነ በኤርትራ የአየር ክልል ላይ ለማለፍ ፍቃድ ባለማግኘቱ እንደሆነም አስታውቀዋል።
ሚኒስትሯ በ3 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለ3 ቀናት ጉብኝት ለማድረግ በጉዞ ላይ የነበሩ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ጉብኝታቸውም ጂቡቲ ነበረች።
ሚኒስትሯ ፤ ያለ እቅድ በሳዑዲ አረቢያ ለማረፍ መገደዳቸው በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ያለውን አለመረጋጋት ያመለክታል ብለዋል።
ትላንት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው ለማደር የተገደዱት ሚኒስትሯ ዛሬ በጅቡቲ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።
የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ " አውሮፕላኑን በኤርትራ የአየር ክልል ላይ ለማብረር ፈቃድ እንዳልተሰጠው ያወቅነው ትናንት ጠዋት ከበረራው ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ ነበር " ብሏል።
አውሮፕላኑ #በበረራ_ላይ_እያለ ፈቃዱን ያገኛል ተብሎ በመወሰኑ ወደዚያ መሄዱንም ገልጿል።
ከቤርቦክ ጋር የተጓዙት ልዑካን ፤ አውሮፕላኑ እየበረረ ፈቃድ ማግኘት እንግዳ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
ቤርቦክን ፤ የሱዳን ጦርነት ጉዳይ እና የቀይ ባህር የመርከብ መንገድ ጉዳይ ትኩረት አድርጓል የተባለው የምሥራቅ አፍሪቃ ጉብኝታቸውን ነገ በደቡብ ሱዳን ያጠናቅቃሉ ተብሏል።
#AlAinNews #DW
@tikvahethiopia
ኤርትራ የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌላ ቤርቦክን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረን አውሮፕላንን ከአየር ክልሏ ማስወጣቷ ተነግሯል።
የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌላ ባየርቦክ ትላንት እንዳስታወቁት፤ ወደ ጂቡቲ ሲጓዝ የነበረው የጀርመን መንግስት አውሮፕላን ያለ እቅድ ሳዑዲ አረቢያ ለማረፍ መገደዱን ገልጸለዋል።
ይህ የሆነ በኤርትራ የአየር ክልል ላይ ለማለፍ ፍቃድ ባለማግኘቱ እንደሆነም አስታውቀዋል።
ሚኒስትሯ በ3 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለ3 ቀናት ጉብኝት ለማድረግ በጉዞ ላይ የነበሩ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ጉብኝታቸውም ጂቡቲ ነበረች።
ሚኒስትሯ ፤ ያለ እቅድ በሳዑዲ አረቢያ ለማረፍ መገደዳቸው በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ያለውን አለመረጋጋት ያመለክታል ብለዋል።
ትላንት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው ለማደር የተገደዱት ሚኒስትሯ ዛሬ በጅቡቲ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።
የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ " አውሮፕላኑን በኤርትራ የአየር ክልል ላይ ለማብረር ፈቃድ እንዳልተሰጠው ያወቅነው ትናንት ጠዋት ከበረራው ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ ነበር " ብሏል።
አውሮፕላኑ #በበረራ_ላይ_እያለ ፈቃዱን ያገኛል ተብሎ በመወሰኑ ወደዚያ መሄዱንም ገልጿል።
ከቤርቦክ ጋር የተጓዙት ልዑካን ፤ አውሮፕላኑ እየበረረ ፈቃድ ማግኘት እንግዳ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
ቤርቦክን ፤ የሱዳን ጦርነት ጉዳይ እና የቀይ ባህር የመርከብ መንገድ ጉዳይ ትኩረት አድርጓል የተባለው የምሥራቅ አፍሪቃ ጉብኝታቸውን ነገ በደቡብ ሱዳን ያጠናቅቃሉ ተብሏል።
#AlAinNews #DW
@tikvahethiopia
የኤርትራ መንግሥት 46 እስረኞችን ለቀቀ።
በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ #ኤርትራ ተወስደው በኤርትራ መንግሥት ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ውስጥ 46ቱ በዛሬው ዕለት ተለቀው ሽራሮ ከተማ ገብተዋል።
የሽራሮ ከንቲባ አቶ ሙሉ ብርሃነ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድርገጽ በሰጡት ቃል ፥ እስረኞቹ በኤርትራ የጋሽ ባርካ ዞን መቀመጫ በሆነችው የባረንቱ ከተማ ታስረው የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ ጠዋት በ”አይሱዙ” ተሽከርካሪ ተጭነው ሽራሮ እንደገቡ ተናግረዋል።
በእስር ላይ የቆዩት የትግራይ ተወላጆች “ ምህረት ተደርጎላቸው ” የተለቀቁ ሲሆን ይህም በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት እና በኤርትራ ሰራዊት መካከል ሲካሄድ በቆየ ንግግር መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።
እስረኞቹ ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገው፤ በጦርነቱ ጊዜ “ ከባድ የሆነ ወንጀል ያልፈጸሙ ናቸው ” በሚል ምክንያት ነው።
በኤርትራ እስር ላይ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች መካከል አሁንም ያልተፈቱ አሉ።
የዛሬው እርምጃ የቀሩትም እንደሚለቀቁ “ ተስፋ ሰጪ ነው ” ሲሉ የሽራሮ ከተማ ከንቲባ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ #ኤርትራ ተወስደው በኤርትራ መንግሥት ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ውስጥ 46ቱ በዛሬው ዕለት ተለቀው ሽራሮ ከተማ ገብተዋል።
የሽራሮ ከንቲባ አቶ ሙሉ ብርሃነ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድርገጽ በሰጡት ቃል ፥ እስረኞቹ በኤርትራ የጋሽ ባርካ ዞን መቀመጫ በሆነችው የባረንቱ ከተማ ታስረው የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ ጠዋት በ”አይሱዙ” ተሽከርካሪ ተጭነው ሽራሮ እንደገቡ ተናግረዋል።
በእስር ላይ የቆዩት የትግራይ ተወላጆች “ ምህረት ተደርጎላቸው ” የተለቀቁ ሲሆን ይህም በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት እና በኤርትራ ሰራዊት መካከል ሲካሄድ በቆየ ንግግር መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።
እስረኞቹ ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገው፤ በጦርነቱ ጊዜ “ ከባድ የሆነ ወንጀል ያልፈጸሙ ናቸው ” በሚል ምክንያት ነው።
በኤርትራ እስር ላይ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች መካከል አሁንም ያልተፈቱ አሉ።
የዛሬው እርምጃ የቀሩትም እንደሚለቀቁ “ ተስፋ ሰጪ ነው ” ሲሉ የሽራሮ ከተማ ከንቲባ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ምን አሉ ? 🔵 " ሕገ-መንግሥቱ ለውጥረት መንስዔ ከመሆኑም ባሻገር ሀገር ግንባታን የሚያስፋፋ አይደለም " - የኤርትራው ፕሬዝዳንት የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት ምሽት በመንግሥታቸው የቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው ስለወቅታዊ ጉዳዮች ቃለ-ምልልስ ሰጥተዋል። ፕሬዝደንቱ ሶማሊያ፣ ግብፅ እና ሀገራቸው ኤርትራ ስለገቡት ስምምነት፣ በኢትዮጵያ በተለይ በትግራይ ክልል ስላለው…
#ኤርትራ
🚨 " አምባገነኑ ኢሳያስ በህግ ለመተዳደር፣ ለህጋዊ ጉዳዮች፣ ለህገመንግስት ባዕድ ናቸው ! " - የፋና ቴሌቪዥን ዘገባ
🔴 " አምባገነንነትን አጥብቀው የሚወዱት ኢሳያስ ምርጫንም ሆነ የህግ የበላይነትን እምቢኝ እንዳሉ ወንበራቸው ላይ አርጅተዋል ! "
ፋና ቴሌቪዥን በኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ላይ " የአስመራው መንግሥት ነገር - የራሷ አሮባት " በሚል የሰራው ጠንከር ያለ ዘገባ መነጋገሪያ ሆኗል።
" የገዢውን ፓርቲ አቋም ያንጸባርቃል እንዲሁም የመንግሥት ልሳን ነው " እየተባለ የሚነገርለት ፋና ቴሌቪዥን ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል የሰላም ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ በዚህ ልክ ኢሳያስን እና አስተዳደራቸውን አምርሮ የሚተች ዘገባ አውጥቶ አያውቅም።
በትግራይ ጦርነት ወቅት እንኳን ስለ ኤርትራው ገዢ ኢሳያስ ብዙ ሲባል የነበረ ቢሆንም የሻዕቢያ ሰራዊት የሰራቸውን የግፍ ተግባራት በይፋ ተናግሮ አያውቅም ነበር።
በተለይ ከፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረም እና ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት የግድ እንደሚገባ በግልጽ አቋሟን ይፋ ካደረገች በኃላ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል የነበረው ግንኙነት ሻክሯል በሚባልበት በዚህ ወቅት ጠንካራ እና ድፍረት የተሞላበት ዘገባ ሰርቶ ወጥቷል።
የዘገባው መነሻ ሰሞነኛው የኢሳያስ ቃለ ምልልስ ነው።
የፋና ዘገባ " በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ያለውን እጅግ የሻከረ ወቅታዊ ሁኔታ ያሳያል " ተብሏል።
ፋና በሰራው ዘገባ ስለ ፕሬዜዳንት ኢሳያስ ምን አለ ?
➡ በቡዙ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግር ውስጥ የተዘፈቀችውን የራሳቸውን ሀገር ረስተው ስለ ሌሎች ሀገራት እና ስለ ኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ሲፈተፍቱ ነበር።
➡ ኤርትራ በህገመንግስት መስተዳደር ብርቅ የሆናባት ሀገር ናት። ይህ ሆኖ እያለ ህገመንግስት ያላትን ኢትዮጵያን መተቸታቸው አስገራሚ ነው።
➡ ላለፉት 30 ዓመታት በላይ ያለ ምንም ተቀናቃኝ ኤርትራን የገዙት ኢሳያስ መንግሥታቸው ህገመንግስት ፣ ምርጫ ፣ ነጻና ገለልተኛ የዴሞክራሲ ተቋማት የሚባል ነገር አያውቅም ፤ ፍላጎትም የላቸውም። ደግሞ አፋቸውን ሞልተው ይህንኑ ይናገራሉ።
➡ ምርጫም ሆነ ተቀናቃኝ እንዳይኖር ለሶስት አስርት ዓመታት አፍነው እያስተዳደሩ ፣ በኢኮኖሚም ሆነ ፖለቲካም ከዓለም ስለራቀች ሀገራቸ ኤርትራ ለመናገር ነውር አስመስለውታል።
➡ ለቀጠናዊ ሰላም እና ትብብር ጆሮ የማይሰጡት ኢሳያስ በቀጠናው ሰላም መደፍረስ ጣታቸውን ኢትዮጵያ ላይ ቀስረዋል።
➡ የህገመንግስት አስተዳደር የሌላቸው ኢሳያስ የኢትዮጵያን ህገመንግስት ለመተቸት ደፍረዋል።
➡ ኤርትራ ህገመንግስት ካፀደቀች ሩብ ክፍለዘመን ቢሆናትም አምባገነንነትን አጥብቀው የሚወዱት ኢሳያስ ከመሳቢያቸው ስር ሽጉጠው ምርጫንም የህግ የበላይነትንም እምቢኝ እንዳሉ ወንበራቸው ላይ አርጅተዋል።
➡ ህገመንግስት የሌላቸው ሰው የኢትዮጵያ ህገመንግስት ላይ አስተያየት መስጠታቸው ስላቅ ይሆናል።
➡ አምባገነኑ ኢሳያስ በህግ ለመተዳደር፣ ለህጋዊ ጉዳዮች፣ ለህገመንግስት ባዕድ ናቸው።
➡ አምባገነኑ ኢሳያስ የጎረቤቶቻቸው በህግ መመራት የራሳቸውን ድካም የሚያጋልጥባቸው ይመስላቸዋል።
➡ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሚያደረጉ የጎረቤት ሀገራትን አይወዱም።
➡ ኢሳያስ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠን መንግስት ለማወክ ከጀርባ ታጣቂ አሰልጥነው የሚልኩ መሆናቸውን ቴሌቪዥን ላይ ሲቀርቡ ይረሱታል።
➡ እራሳቸውን የቀጠናው ጠበቃ የሀገራቱ ሰላም ወዳድ አድርገው የብልጣ ብልጥ ጨዋታ ይጫወታሉ።
➡ ኤርትራን እንደ ሲንጋፖር አደርጋለሁ የሚለው ቅዠት ወደ ተግባር መለወጥ ሲያቅታቸው የናቋት ጎረቤታቸው ኢትዮጵያ በየአመቱ 8% በላይ እድገት እያስመዘገበች በኢኮኖሚ የቀጠናው ቁንጮ መሆኗ ቅናት ውስጥ ከቷቸዋል።
➡ ኢትዮጵያ ዜጎቿን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ከማድረግ አልፋ ምስራቅ አፍሪካን በኃይል እያስተሳሰረች ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት የአፍሪካን ሁለተኛ ኢኮኖሚ ገንብታለች።
➡ ኢሳያስ ድፍን 30 ዓመታት የመሯት ሀገር ከ30 ዓመታት በፊት በተገነባ መሰረተ ልማት እየኖሩ ነው።
➡ በኤርትራ ኢንተርኔት እና ስልክ በቤተሰብ ኮታ ነው የሚሰጠው። ገንዘብ በATM ማውጣት ብርቅ የሆነባት ሀገር ናት። ዜጎች ሰርግ እንኳን ለመከወን የሚያወጡት ወጪ ኦዲት የሚደረግባት ሀገር ናት።
➡ ኤርትራውያን ነገን ያለ ተስፋ ኑሮን በጨለማ ለመግፋት ተገደዋል።
➡ ጉባ ላይ በተለኮሰው የብርሃን ችቦ (GERD) ዜጎቿን ከጨለማ ወደ ብርሃን ለማሻገር እየተጣደፈችን ያለችውን ጎረቤታቸውን (ኢትዮጵያን) ለመተቸት አንደበታቸውን ሲያላቅቁ ምንም የመሸማቀቅ ስሜት አይታይባቸውም።
➡ ኢሳያስ የሚመሩት መንግሥት የጀርባ እቅዱ ኢትዮጵያን አፈራርሶ ለመግዛት እንደነበር በተደጋጋሚ ከሚያሰሙት ንግግራቸው ተስተውሏል።
➡ ከግብፅ እና ሶማሊያ መሪዎች ጋር ' ቀጠናዊ ሰላም ለማምጣት ' በሚል የዳቦ ስም በሰጡት መርዛማ ቀጠናውን የማተራመስ ሃሳብ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ላይ ስጋት የደቀነ ስምምነት አስመራ ላይ ሲፈራረሙ ታይተዋል። ' ነገሩ ሆድ ሲያቅ .. ' መሆኑን ከ30 ዓመቷ ወጣት ሀገር መረዳት ይቻላል።
➡ አንድ አምስተኛውን ህዝባቸውን ስደተኛ ያደረጉ ኢሳያስ በሰው ሀገር ጉዳይ በመፈትፈት የሚስተካከላቸው አይገኝም።
➡ ኢሳያስ አምርረው የሚጠሉት ለኢትዮጵያውያን የሰንደቅ አላማ ፕሮጀክት የሆነው የህዳሴ ግድብ ሪቫን ሊቆረጥ መቅረቡ እረፍት ነስቷቸዋል።
ይህንን ዘገባ የተመለከቱ በርካቶች ዘገባው " ወቅታዊውን በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ያለውን ቁርሾ / ጤናማ ያልሆነ ግንኙነት ያሳያል " የሚል ሃሳባቸውን ሰጥተውበታል።
https://youtu.be/UdzP3vtR4DI?feature=shared
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
🚨 " አምባገነኑ ኢሳያስ በህግ ለመተዳደር፣ ለህጋዊ ጉዳዮች፣ ለህገመንግስት ባዕድ ናቸው ! " - የፋና ቴሌቪዥን ዘገባ
🔴 " አምባገነንነትን አጥብቀው የሚወዱት ኢሳያስ ምርጫንም ሆነ የህግ የበላይነትን እምቢኝ እንዳሉ ወንበራቸው ላይ አርጅተዋል ! "
ፋና ቴሌቪዥን በኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ላይ " የአስመራው መንግሥት ነገር - የራሷ አሮባት " በሚል የሰራው ጠንከር ያለ ዘገባ መነጋገሪያ ሆኗል።
" የገዢውን ፓርቲ አቋም ያንጸባርቃል እንዲሁም የመንግሥት ልሳን ነው " እየተባለ የሚነገርለት ፋና ቴሌቪዥን ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል የሰላም ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ በዚህ ልክ ኢሳያስን እና አስተዳደራቸውን አምርሮ የሚተች ዘገባ አውጥቶ አያውቅም።
በትግራይ ጦርነት ወቅት እንኳን ስለ ኤርትራው ገዢ ኢሳያስ ብዙ ሲባል የነበረ ቢሆንም የሻዕቢያ ሰራዊት የሰራቸውን የግፍ ተግባራት በይፋ ተናግሮ አያውቅም ነበር።
በተለይ ከፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረም እና ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት የግድ እንደሚገባ በግልጽ አቋሟን ይፋ ካደረገች በኃላ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል የነበረው ግንኙነት ሻክሯል በሚባልበት በዚህ ወቅት ጠንካራ እና ድፍረት የተሞላበት ዘገባ ሰርቶ ወጥቷል።
የዘገባው መነሻ ሰሞነኛው የኢሳያስ ቃለ ምልልስ ነው።
የፋና ዘገባ " በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ያለውን እጅግ የሻከረ ወቅታዊ ሁኔታ ያሳያል " ተብሏል።
ፋና በሰራው ዘገባ ስለ ፕሬዜዳንት ኢሳያስ ምን አለ ?
➡ በቡዙ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግር ውስጥ የተዘፈቀችውን የራሳቸውን ሀገር ረስተው ስለ ሌሎች ሀገራት እና ስለ ኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ሲፈተፍቱ ነበር።
➡ ኤርትራ በህገመንግስት መስተዳደር ብርቅ የሆናባት ሀገር ናት። ይህ ሆኖ እያለ ህገመንግስት ያላትን ኢትዮጵያን መተቸታቸው አስገራሚ ነው።
➡ ላለፉት 30 ዓመታት በላይ ያለ ምንም ተቀናቃኝ ኤርትራን የገዙት ኢሳያስ መንግሥታቸው ህገመንግስት ፣ ምርጫ ፣ ነጻና ገለልተኛ የዴሞክራሲ ተቋማት የሚባል ነገር አያውቅም ፤ ፍላጎትም የላቸውም። ደግሞ አፋቸውን ሞልተው ይህንኑ ይናገራሉ።
➡ ምርጫም ሆነ ተቀናቃኝ እንዳይኖር ለሶስት አስርት ዓመታት አፍነው እያስተዳደሩ ፣ በኢኮኖሚም ሆነ ፖለቲካም ከዓለም ስለራቀች ሀገራቸ ኤርትራ ለመናገር ነውር አስመስለውታል።
➡ ለቀጠናዊ ሰላም እና ትብብር ጆሮ የማይሰጡት ኢሳያስ በቀጠናው ሰላም መደፍረስ ጣታቸውን ኢትዮጵያ ላይ ቀስረዋል።
➡ የህገመንግስት አስተዳደር የሌላቸው ኢሳያስ የኢትዮጵያን ህገመንግስት ለመተቸት ደፍረዋል።
➡ ኤርትራ ህገመንግስት ካፀደቀች ሩብ ክፍለዘመን ቢሆናትም አምባገነንነትን አጥብቀው የሚወዱት ኢሳያስ ከመሳቢያቸው ስር ሽጉጠው ምርጫንም የህግ የበላይነትንም እምቢኝ እንዳሉ ወንበራቸው ላይ አርጅተዋል።
➡ ህገመንግስት የሌላቸው ሰው የኢትዮጵያ ህገመንግስት ላይ አስተያየት መስጠታቸው ስላቅ ይሆናል።
➡ አምባገነኑ ኢሳያስ በህግ ለመተዳደር፣ ለህጋዊ ጉዳዮች፣ ለህገመንግስት ባዕድ ናቸው።
➡ አምባገነኑ ኢሳያስ የጎረቤቶቻቸው በህግ መመራት የራሳቸውን ድካም የሚያጋልጥባቸው ይመስላቸዋል።
➡ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሚያደረጉ የጎረቤት ሀገራትን አይወዱም።
➡ ኢሳያስ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠን መንግስት ለማወክ ከጀርባ ታጣቂ አሰልጥነው የሚልኩ መሆናቸውን ቴሌቪዥን ላይ ሲቀርቡ ይረሱታል።
➡ እራሳቸውን የቀጠናው ጠበቃ የሀገራቱ ሰላም ወዳድ አድርገው የብልጣ ብልጥ ጨዋታ ይጫወታሉ።
➡ ኤርትራን እንደ ሲንጋፖር አደርጋለሁ የሚለው ቅዠት ወደ ተግባር መለወጥ ሲያቅታቸው የናቋት ጎረቤታቸው ኢትዮጵያ በየአመቱ 8% በላይ እድገት እያስመዘገበች በኢኮኖሚ የቀጠናው ቁንጮ መሆኗ ቅናት ውስጥ ከቷቸዋል።
➡ ኢትዮጵያ ዜጎቿን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ከማድረግ አልፋ ምስራቅ አፍሪካን በኃይል እያስተሳሰረች ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት የአፍሪካን ሁለተኛ ኢኮኖሚ ገንብታለች።
➡ ኢሳያስ ድፍን 30 ዓመታት የመሯት ሀገር ከ30 ዓመታት በፊት በተገነባ መሰረተ ልማት እየኖሩ ነው።
➡ በኤርትራ ኢንተርኔት እና ስልክ በቤተሰብ ኮታ ነው የሚሰጠው። ገንዘብ በATM ማውጣት ብርቅ የሆነባት ሀገር ናት። ዜጎች ሰርግ እንኳን ለመከወን የሚያወጡት ወጪ ኦዲት የሚደረግባት ሀገር ናት።
➡ ኤርትራውያን ነገን ያለ ተስፋ ኑሮን በጨለማ ለመግፋት ተገደዋል።
➡ ጉባ ላይ በተለኮሰው የብርሃን ችቦ (GERD) ዜጎቿን ከጨለማ ወደ ብርሃን ለማሻገር እየተጣደፈችን ያለችውን ጎረቤታቸውን (ኢትዮጵያን) ለመተቸት አንደበታቸውን ሲያላቅቁ ምንም የመሸማቀቅ ስሜት አይታይባቸውም።
➡ ኢሳያስ የሚመሩት መንግሥት የጀርባ እቅዱ ኢትዮጵያን አፈራርሶ ለመግዛት እንደነበር በተደጋጋሚ ከሚያሰሙት ንግግራቸው ተስተውሏል።
➡ ከግብፅ እና ሶማሊያ መሪዎች ጋር ' ቀጠናዊ ሰላም ለማምጣት ' በሚል የዳቦ ስም በሰጡት መርዛማ ቀጠናውን የማተራመስ ሃሳብ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ላይ ስጋት የደቀነ ስምምነት አስመራ ላይ ሲፈራረሙ ታይተዋል። ' ነገሩ ሆድ ሲያቅ .. ' መሆኑን ከ30 ዓመቷ ወጣት ሀገር መረዳት ይቻላል።
➡ አንድ አምስተኛውን ህዝባቸውን ስደተኛ ያደረጉ ኢሳያስ በሰው ሀገር ጉዳይ በመፈትፈት የሚስተካከላቸው አይገኝም።
➡ ኢሳያስ አምርረው የሚጠሉት ለኢትዮጵያውያን የሰንደቅ አላማ ፕሮጀክት የሆነው የህዳሴ ግድብ ሪቫን ሊቆረጥ መቅረቡ እረፍት ነስቷቸዋል።
ይህንን ዘገባ የተመለከቱ በርካቶች ዘገባው " ወቅታዊውን በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ያለውን ቁርሾ / ጤናማ ያልሆነ ግንኙነት ያሳያል " የሚል ሃሳባቸውን ሰጥተውበታል።
https://youtu.be/UdzP3vtR4DI?feature=shared
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia