#ነዳጅ
ለመጪው የ2016 ዓ/ም ወደ አገር ለማስገባት ለታቀደው 4.3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ 4.4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት አስታውቋል።
ኢትዮጵያ በ2016 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋትን ነዳጅ ለማስገባት የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ፣ " ቪቶል " የተባለው የባህሬን ኩባንያ በድጋሚ በማሸነፉ የኮንትራት ውል ስምምነት ተፈርሟል፡፡
ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በ2016 ዓ.ም. ለማስገባት ያቀደውን ሙሉ ለሙሉ ቤንዚን፣ እንዲሁም ከጠቅላላው የነጭ ናፍጣ ግዥ 40 በመቶውን " ቪቶል " ኩባንያ እንደሚያስገባ ታውቋል፡፡
በስምምነቱ መሠረት ለ1 ዓመት የሚያስፈልገውን 760 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ቤንዚንና 1.2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነጭ ናፍጣ ኩባንያው ያቀርባል፡፡
" ቪቶል " ጨረታውን ያሸነፈው ከሁለት ሌሎች ኩባንያዎች ጋር ተወዳድሮ እንደሆነ ተነግሯል።
" ቪቶል " እየተጠናቀቀ ላለፈው የበጀት ዓመት በተመሳሳይ የወጣውን ጨረታ አሸንፎ ሲያቀርብ ነበር።
ለ2016 በጀት ዓመት ያስፈልጋል ተብሎ የታቀደው ነዳጅ ከ2015 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በስምንት በመቶ ብልጫ አለው፡፡
በተናጠል ሲታይ ቤንዚን ስምንት በመቶና ነጭ ናፍጣ አምስት በመቶ ጭማሪ ይኖራቸዋል፡፡
Via Ethiopian Reporter
@tikvahethiopia
ለመጪው የ2016 ዓ/ም ወደ አገር ለማስገባት ለታቀደው 4.3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ 4.4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት አስታውቋል።
ኢትዮጵያ በ2016 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋትን ነዳጅ ለማስገባት የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ፣ " ቪቶል " የተባለው የባህሬን ኩባንያ በድጋሚ በማሸነፉ የኮንትራት ውል ስምምነት ተፈርሟል፡፡
ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በ2016 ዓ.ም. ለማስገባት ያቀደውን ሙሉ ለሙሉ ቤንዚን፣ እንዲሁም ከጠቅላላው የነጭ ናፍጣ ግዥ 40 በመቶውን " ቪቶል " ኩባንያ እንደሚያስገባ ታውቋል፡፡
በስምምነቱ መሠረት ለ1 ዓመት የሚያስፈልገውን 760 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ቤንዚንና 1.2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነጭ ናፍጣ ኩባንያው ያቀርባል፡፡
" ቪቶል " ጨረታውን ያሸነፈው ከሁለት ሌሎች ኩባንያዎች ጋር ተወዳድሮ እንደሆነ ተነግሯል።
" ቪቶል " እየተጠናቀቀ ላለፈው የበጀት ዓመት በተመሳሳይ የወጣውን ጨረታ አሸንፎ ሲያቀርብ ነበር።
ለ2016 በጀት ዓመት ያስፈልጋል ተብሎ የታቀደው ነዳጅ ከ2015 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በስምንት በመቶ ብልጫ አለው፡፡
በተናጠል ሲታይ ቤንዚን ስምንት በመቶና ነጭ ናፍጣ አምስት በመቶ ጭማሪ ይኖራቸዋል፡፡
Via Ethiopian Reporter
@tikvahethiopia
#ነዳጅ
ሳዑዲ አረቢያ ከነዳጅ ምርቷ በቀን 1 ሚሊዮን በርሜል እቀንሳለሁ ማለቷን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ መጨመሩ ተነገረ።
ሌሎች የዓለማችን ነዳጃ አምራች አገራትም በተመሳሳይ የነዳጅን ዋጋን ለማረጋጋት በማሰብ የምርት አቅርቦታቸውን ለመቀነስ ተስማምተዋል ተብሏል።
ሳዑዲ አረቢያ በቀጣዩ ሀምሌ ወር በየቀኑ 1 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ከምርት አቅርቦቷ ላይ እንደምትቀነስ የገለጸች ሲሆን የነዳጅ ላኪዎች ሀገራት ማህበር ወይም ኦፔክ+ እንደ አውሮፓውያኑ በ2024 ዕለታዊ የነዳጅ አቅርቦት በ1.4 ሚሊዮን በርሜል እንደሚቀንስ ገልጿል።
ኦፔክ+ የዓለምን 40 በመቶ የነዳጅ ፍላጎት የሚያሟላ ሲሆን ውሳኔው በዓለም የነዳጅ ምርት ዋጋ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ሊያሳድር ይችላል።
የሳዑዲን ውሳኔ ተከትሎ በእስያ ገበያ የደፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በ 2.4 በመቶ አሻቅቦ በበርሜል 77 ዶላር ሆኗል።
የሳዑዲ ኢነርጂ ሚንስትር ልዑል አብዱላዚዝ ቢን ሰልማን ፤ የነዳጅ ምርት አቅቦቱን የመቀነሱ ውሳኔ አስፈላጊ ከሆነ ከሃምሌም በኃላ #ሊራዘም ይችላል ብለዋል። ውሳኔው የዓለም የነዳጅ ዋጋን እንደሚያረጋጋ ገልጸዋል።
#ቢቢሲ
@tikvahethiopia
ሳዑዲ አረቢያ ከነዳጅ ምርቷ በቀን 1 ሚሊዮን በርሜል እቀንሳለሁ ማለቷን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ መጨመሩ ተነገረ።
ሌሎች የዓለማችን ነዳጃ አምራች አገራትም በተመሳሳይ የነዳጅን ዋጋን ለማረጋጋት በማሰብ የምርት አቅርቦታቸውን ለመቀነስ ተስማምተዋል ተብሏል።
ሳዑዲ አረቢያ በቀጣዩ ሀምሌ ወር በየቀኑ 1 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ከምርት አቅርቦቷ ላይ እንደምትቀነስ የገለጸች ሲሆን የነዳጅ ላኪዎች ሀገራት ማህበር ወይም ኦፔክ+ እንደ አውሮፓውያኑ በ2024 ዕለታዊ የነዳጅ አቅርቦት በ1.4 ሚሊዮን በርሜል እንደሚቀንስ ገልጿል።
ኦፔክ+ የዓለምን 40 በመቶ የነዳጅ ፍላጎት የሚያሟላ ሲሆን ውሳኔው በዓለም የነዳጅ ምርት ዋጋ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ሊያሳድር ይችላል።
የሳዑዲን ውሳኔ ተከትሎ በእስያ ገበያ የደፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በ 2.4 በመቶ አሻቅቦ በበርሜል 77 ዶላር ሆኗል።
የሳዑዲ ኢነርጂ ሚንስትር ልዑል አብዱላዚዝ ቢን ሰልማን ፤ የነዳጅ ምርት አቅቦቱን የመቀነሱ ውሳኔ አስፈላጊ ከሆነ ከሃምሌም በኃላ #ሊራዘም ይችላል ብለዋል። ውሳኔው የዓለም የነዳጅ ዋጋን እንደሚያረጋጋ ገልጸዋል።
#ቢቢሲ
@tikvahethiopia
#ነዳጅ📈
የነዳጅ ዋጋ እያሻቀበ ለረጅም ጊዜ ሊቆይ ይችላል ሲሉ የነዳጅ ላኪዎች ህብረት መሪ አስጠነቀቁ።
የ23 ነዳጅ ላኪ ሀገራት ህብረት የሆነው ኦፔክ+ ዋና ፀሀፊ ሄይታም አል ጋይስ ፤ ለሃይል አቅርቦት ያለው ፍላጎት በመጨመሩ የነደጅ ዋጋ እንዳሻቀበ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።
ዋና ጸሃፊው " በቀን የነዳጅ ፍላጎት ወደ 2.4 ሚሊዮን በርሜል ሲያድግ እየተመለከትን ነው " ብለዋል።
ሁለቱ ዋነኛ የነዳጅ አምራችና ' ኦፔክ+ ' አባል የሆኑት ሳዑዲና ሩሲያ የወሰኑት ውሳኔ በዚህ ዓመት መጨረሻ ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ያስከትላል ሲል ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ አስታውቋል።
" ይህ ሁለት ሉአላዊ ሀገራት ሳዑዲ አረቢያ እና ሩስያ በፍቃደኝነት የወሰኑት ነው። ይህ ውሳኔ እርግጠኛ ልንሆንበት በማንችልበት ሁኔታ ምክንያት የተደረገ ጥንቃቄ ወይም ቅድመ ዝግጅት ብለን ልንገልጸው እንችላል " ሲሉ የኦፔክ+ ዋና ጸሃፊ ተናግረዋል።
ሰሞኑን በምርት እጥረት ምክንያት የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 95 ዶላርን አልፎ የነበረ ሲሆን ዋጋው 100 ዶላርን ሊያልፍ ይችላል የሚል ስጋትን ፈጥሯል።
ይህ የዋጋ ለውጥ በሚቀጥሉት 10 ወራት ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ሊያሻቅብ እንደሚችልና በወሳኝ የኢኮኖሚ መስኮች ያለው የዋጋ ግሽበት ለረዥም ጊዜ እንዲቀጥል ምክንያት ይሆናል የሚል ስጋትን ማጫሩን #ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የነዳጅ ዋጋ እያሻቀበ ለረጅም ጊዜ ሊቆይ ይችላል ሲሉ የነዳጅ ላኪዎች ህብረት መሪ አስጠነቀቁ።
የ23 ነዳጅ ላኪ ሀገራት ህብረት የሆነው ኦፔክ+ ዋና ፀሀፊ ሄይታም አል ጋይስ ፤ ለሃይል አቅርቦት ያለው ፍላጎት በመጨመሩ የነደጅ ዋጋ እንዳሻቀበ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።
ዋና ጸሃፊው " በቀን የነዳጅ ፍላጎት ወደ 2.4 ሚሊዮን በርሜል ሲያድግ እየተመለከትን ነው " ብለዋል።
ሁለቱ ዋነኛ የነዳጅ አምራችና ' ኦፔክ+ ' አባል የሆኑት ሳዑዲና ሩሲያ የወሰኑት ውሳኔ በዚህ ዓመት መጨረሻ ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ያስከትላል ሲል ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ አስታውቋል።
" ይህ ሁለት ሉአላዊ ሀገራት ሳዑዲ አረቢያ እና ሩስያ በፍቃደኝነት የወሰኑት ነው። ይህ ውሳኔ እርግጠኛ ልንሆንበት በማንችልበት ሁኔታ ምክንያት የተደረገ ጥንቃቄ ወይም ቅድመ ዝግጅት ብለን ልንገልጸው እንችላል " ሲሉ የኦፔክ+ ዋና ጸሃፊ ተናግረዋል።
ሰሞኑን በምርት እጥረት ምክንያት የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 95 ዶላርን አልፎ የነበረ ሲሆን ዋጋው 100 ዶላርን ሊያልፍ ይችላል የሚል ስጋትን ፈጥሯል።
ይህ የዋጋ ለውጥ በሚቀጥሉት 10 ወራት ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ሊያሻቅብ እንደሚችልና በወሳኝ የኢኮኖሚ መስኮች ያለው የዋጋ ግሽበት ለረዥም ጊዜ እንዲቀጥል ምክንያት ይሆናል የሚል ስጋትን ማጫሩን #ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ። በእስራኤል እና በፍልስጤም ሃማስ መካከል የተቀሰቀሰው ከፍተኛ ጦርነት የነዳጅ ዋጋ እንዲጨምር ማድረጉ ተዘግቧል። የአንድ በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በ4 % በላይ መጨመሩ ተነግሯል። ባለፉት ሳምንታት ወደ 96 ዶላር ደርሶ የነበረው የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ባለፉት ቀናት ጥሩ የሚባል ቅናሽ እያሳየ መጥቶ ነበር። ነገር ግን ቅዳሜ በሃማስ እና እስራኤል መካከል…
#ነዳጅ
በመካከለኛው ምሥራቅ በእስራኤልና ሀማስ መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ መፍጠር የጀመረው የዋጋ ጭማሪ ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ በኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ የመጣው የነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ የበለጠ ሰማይ ሊነካ ይችላል የሚል ሥጋት ፈጥሯል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት እስካሁን ድረስ የነዳጅ ዋጋን ወደ ተጠቃሚው ለማስተላለፍ በወሰነው መሠረት እስሁን ድረስ በአማካይ ከአሥር በመቶ በላይ የዋጋ ጭማሪ እያደረገ የመጣ በመሆኑ በእስራኤል እና ሀማስ መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት ሊፈጥር የሚችለው የዓለም የነዳጅ ዋጋ በቀጥታ ወደ ተጠቃሚው ማኅበረሰብ ከማስተላለፍ ሊቆጠብ እንደሚገባ የኢኮኖሚ ባለሞያው አቶ አወት ተክኤ መክረዋል።
የኢኮኖሚ ባለሞያው አቶ አወት ተክሌ ምን አሉ ?
" በመካከለኛው ምሥራቅ የሚከሰት ጦርነትና አለመረጋጋት በዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ የሚያሳድር ነው።
በቀዳሚነትም የዓለም የነዳጅ አቅርቦትና ገበያ የሚታወክ በመሆኑ፣ ይህ ሁኔታ የሚከሰት ከሆነ አሉታዊ ተፅዕኖው ለኢትዮጵያም የሚተርፍ እና የሚያሰጋ ነው።
የዓለም የነዳጅ ምርትና ገበያ ሰላምን ይፈልጋል። እንዲህ ያሉ ትልልቅ ጦርነቶች በተለይ አገሮች በፖለቲካ አመለካከታቸው ወገንተኝነታቸውን በግልጽ በሚያሳዩበት ወቅት የነዳጅ ግብይት ላይ ተፅዕኖ ይኖረዋል።
በተለይ አሁን በተቀሰቀሰው የእስራኤል እና ሀማስ ጦርነት ምክንያት በአካባቢው የሚገኙ የመካከለኛው ምሥራቅ ነዳጅ ባለፀጎች ለአንደኛው ወገን የሚያደላ የፖለቲካ አቋም ለመያዝ ከተገደዱ ይህንን የፖለቲካ አቋማቸውን የሚገልጹት የነዳጅ ምርትና አቅርቦታቸውን በመገደብ እንደሚሆን ቀደም ሲል የነበራቸውን ተሞክሮ ያሳያል።
ከዛሬ 50 ዓመታት በፊት በነዚሁ ወገኖች መካከል በተቀሰቀሰ ጦርነት ነዳጅ አምራች አገሮች በሁለቱ ተፋላሚዎች መካከል ጎራ ለይተው በመሠለፋቸው በዓለም የነዳጅ ምርትና አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ዕክል ፈጥረው ነበር።
አሁንም እነዚሁ ተመሳሳይ አገሮች የሚፋለሙበት ጦርነት በመከሰቱ በነዳጅ ሀብት የታደሉት የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች በዋናነትም፣ ኢራንና ሳዑዲ ዓረቢያ ያሉ አገሮች አንደኛውን ተፋላሚ ወገን ደግፈው ምዕራባዊያኑ ደግሞ ሌላኛውን ወገን ደግፈው የሚቆሙ ከሆነ የዓለም የነዳጅ ምርትና አቅርቦትን ሊያስተጓጉልና ዋጋውም ጣሪያ ሊነካ ይችላል።
ይህ ሁኔታ ከተከሰተ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ አገሮች ትልቅ ፈተና ነው።
ስለዚህ የኢትዮጵያ መንግሥት ከነዳጅ ድጎማ ለመውጣት ቀስ በቀስ የሚያደርገውን የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሠረት ያደረገ ወርኃዊ የችርቻሮ ዋጋ ማስተካከያ ቆም ብሎ ሊፈትሸው ይገባል።
ያልጠበቀውን ጦርነት ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እንዳለ ኅብረተሰቡ ላይ መጫን የሚያዋጣ አይደለም።
መንግሥት ከነዳጅ ድጎማ ለመውጣት በገበያ ዋጋ እየሠራ ቢሆንም እንዲህ ባሉ ያልተጠበቁ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ግን ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ ግንዛቤ ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል።
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አጠቃላይ ኢኮኖሚው ላይ የሚፈጥረው ተፅዕኖው ግልጽ ከመሆኑ አንፃር በተለይም በአሁኑ ወቅት የሚታየው የዋጋ ንረት ጦርነቱ ሊያስከትል የሚችለውን የዋጋ ጭማሪ ኅብረተሰቡ ላይ እንዲጫን ማድረግ ተገቢ አይሆንም።
ይህ ካልሆነ ግን የዋጋ ንረቱን በማባባስ ማኅበረሰብን ብሎም ኢኮኖሚውን ይጎዳል።
በሌላ በኩል ግን የእስራኤልና የፍልስጤም ጦርነት ከተፋላሚ አገሮች ባሻገር አገሮችን ጎራ ለይተው ወገንተኝነታቸውን እየገለጹ መሆን ምናልባት ትላልቆቹ የነዳጅ አቅራቢዎች ነዳጅ ባያቀርቡ ዓለም ላይ ችግር እንዳይኖር በተቃራኒ ያሉ አገሮች ተጨማሪ ነዳጅ በማቅረብ ገበያውን ለማረጋጋት ሊሞክሩ የሚችሉበት ዕድል እንዳለ አለ። ይህ ሊሆን የሚችለበት ዕድል ጠባብ ቢሆንም አሁን ካለው ሁኔታ አንፃር ሲታይ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው አይቀመስም ብዙ አገሮችን ተጎጂ ያደርጋቸዋል፡፡
በተለይ ከፍተኛ የገቢ ንግድ ያለቸው አገሮች የዋጋ ጭማሪ ሊያስከትልባቸው ይችላል። ስለዚህ በተለይ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ሊያስከትል የሚችለው ተፅዕኖ በማሰብ መንግሥትም ጊዜውን የዋጀ አሠራር ያስፈልገዋል።
በአጠቃላይ ግን የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ዓለም አቀፉን ኢኮኖሚ ይፈትናል፡፡
ጦርነቱ ዛሬ ያቆማል ቢባል እንኳን በብዙ መልኩ ተፅዕኖው ቀላል አይሆንም። በተለይ ዕቃን የሚያጓጉዙ የትራንስፖርት ዘርፎች በሚፈጠርባቸው ሥጋት እንቅስቃሴያቸው ይገደባል፡፡ ከዚህም ሌላ መንቀሳቀስ ከቻሉም ከፍተኛ የኢንሹራንስ ሽፋን የሚጠይቁ መሆኑንና ተያያዥ ጉዳዮች የአቅርቦት ዋጋን ስለሚያስወድዱ የጦርነቱ ግልጽ የሆነ ተፅዕኖ አለው። "
(ከሪፖርተር የተወሰደ)
@tikvahethiopia
በመካከለኛው ምሥራቅ በእስራኤልና ሀማስ መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ መፍጠር የጀመረው የዋጋ ጭማሪ ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ በኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ የመጣው የነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ የበለጠ ሰማይ ሊነካ ይችላል የሚል ሥጋት ፈጥሯል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት እስካሁን ድረስ የነዳጅ ዋጋን ወደ ተጠቃሚው ለማስተላለፍ በወሰነው መሠረት እስሁን ድረስ በአማካይ ከአሥር በመቶ በላይ የዋጋ ጭማሪ እያደረገ የመጣ በመሆኑ በእስራኤል እና ሀማስ መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት ሊፈጥር የሚችለው የዓለም የነዳጅ ዋጋ በቀጥታ ወደ ተጠቃሚው ማኅበረሰብ ከማስተላለፍ ሊቆጠብ እንደሚገባ የኢኮኖሚ ባለሞያው አቶ አወት ተክኤ መክረዋል።
የኢኮኖሚ ባለሞያው አቶ አወት ተክሌ ምን አሉ ?
" በመካከለኛው ምሥራቅ የሚከሰት ጦርነትና አለመረጋጋት በዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ የሚያሳድር ነው።
በቀዳሚነትም የዓለም የነዳጅ አቅርቦትና ገበያ የሚታወክ በመሆኑ፣ ይህ ሁኔታ የሚከሰት ከሆነ አሉታዊ ተፅዕኖው ለኢትዮጵያም የሚተርፍ እና የሚያሰጋ ነው።
የዓለም የነዳጅ ምርትና ገበያ ሰላምን ይፈልጋል። እንዲህ ያሉ ትልልቅ ጦርነቶች በተለይ አገሮች በፖለቲካ አመለካከታቸው ወገንተኝነታቸውን በግልጽ በሚያሳዩበት ወቅት የነዳጅ ግብይት ላይ ተፅዕኖ ይኖረዋል።
በተለይ አሁን በተቀሰቀሰው የእስራኤል እና ሀማስ ጦርነት ምክንያት በአካባቢው የሚገኙ የመካከለኛው ምሥራቅ ነዳጅ ባለፀጎች ለአንደኛው ወገን የሚያደላ የፖለቲካ አቋም ለመያዝ ከተገደዱ ይህንን የፖለቲካ አቋማቸውን የሚገልጹት የነዳጅ ምርትና አቅርቦታቸውን በመገደብ እንደሚሆን ቀደም ሲል የነበራቸውን ተሞክሮ ያሳያል።
ከዛሬ 50 ዓመታት በፊት በነዚሁ ወገኖች መካከል በተቀሰቀሰ ጦርነት ነዳጅ አምራች አገሮች በሁለቱ ተፋላሚዎች መካከል ጎራ ለይተው በመሠለፋቸው በዓለም የነዳጅ ምርትና አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ዕክል ፈጥረው ነበር።
አሁንም እነዚሁ ተመሳሳይ አገሮች የሚፋለሙበት ጦርነት በመከሰቱ በነዳጅ ሀብት የታደሉት የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች በዋናነትም፣ ኢራንና ሳዑዲ ዓረቢያ ያሉ አገሮች አንደኛውን ተፋላሚ ወገን ደግፈው ምዕራባዊያኑ ደግሞ ሌላኛውን ወገን ደግፈው የሚቆሙ ከሆነ የዓለም የነዳጅ ምርትና አቅርቦትን ሊያስተጓጉልና ዋጋውም ጣሪያ ሊነካ ይችላል።
ይህ ሁኔታ ከተከሰተ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ አገሮች ትልቅ ፈተና ነው።
ስለዚህ የኢትዮጵያ መንግሥት ከነዳጅ ድጎማ ለመውጣት ቀስ በቀስ የሚያደርገውን የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሠረት ያደረገ ወርኃዊ የችርቻሮ ዋጋ ማስተካከያ ቆም ብሎ ሊፈትሸው ይገባል።
ያልጠበቀውን ጦርነት ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እንዳለ ኅብረተሰቡ ላይ መጫን የሚያዋጣ አይደለም።
መንግሥት ከነዳጅ ድጎማ ለመውጣት በገበያ ዋጋ እየሠራ ቢሆንም እንዲህ ባሉ ያልተጠበቁ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ግን ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ ግንዛቤ ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል።
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አጠቃላይ ኢኮኖሚው ላይ የሚፈጥረው ተፅዕኖው ግልጽ ከመሆኑ አንፃር በተለይም በአሁኑ ወቅት የሚታየው የዋጋ ንረት ጦርነቱ ሊያስከትል የሚችለውን የዋጋ ጭማሪ ኅብረተሰቡ ላይ እንዲጫን ማድረግ ተገቢ አይሆንም።
ይህ ካልሆነ ግን የዋጋ ንረቱን በማባባስ ማኅበረሰብን ብሎም ኢኮኖሚውን ይጎዳል።
በሌላ በኩል ግን የእስራኤልና የፍልስጤም ጦርነት ከተፋላሚ አገሮች ባሻገር አገሮችን ጎራ ለይተው ወገንተኝነታቸውን እየገለጹ መሆን ምናልባት ትላልቆቹ የነዳጅ አቅራቢዎች ነዳጅ ባያቀርቡ ዓለም ላይ ችግር እንዳይኖር በተቃራኒ ያሉ አገሮች ተጨማሪ ነዳጅ በማቅረብ ገበያውን ለማረጋጋት ሊሞክሩ የሚችሉበት ዕድል እንዳለ አለ። ይህ ሊሆን የሚችለበት ዕድል ጠባብ ቢሆንም አሁን ካለው ሁኔታ አንፃር ሲታይ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው አይቀመስም ብዙ አገሮችን ተጎጂ ያደርጋቸዋል፡፡
በተለይ ከፍተኛ የገቢ ንግድ ያለቸው አገሮች የዋጋ ጭማሪ ሊያስከትልባቸው ይችላል። ስለዚህ በተለይ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ሊያስከትል የሚችለው ተፅዕኖ በማሰብ መንግሥትም ጊዜውን የዋጀ አሠራር ያስፈልገዋል።
በአጠቃላይ ግን የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ዓለም አቀፉን ኢኮኖሚ ይፈትናል፡፡
ጦርነቱ ዛሬ ያቆማል ቢባል እንኳን በብዙ መልኩ ተፅዕኖው ቀላል አይሆንም። በተለይ ዕቃን የሚያጓጉዙ የትራንስፖርት ዘርፎች በሚፈጠርባቸው ሥጋት እንቅስቃሴያቸው ይገደባል፡፡ ከዚህም ሌላ መንቀሳቀስ ከቻሉም ከፍተኛ የኢንሹራንስ ሽፋን የሚጠይቁ መሆኑንና ተያያዥ ጉዳዮች የአቅርቦት ዋጋን ስለሚያስወድዱ የጦርነቱ ግልጽ የሆነ ተፅዕኖ አለው። "
(ከሪፖርተር የተወሰደ)
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #ነዳጅ
የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ስጪ በሆኑ ተሽከርካሪዎች ላይ የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ በተደርገ ማሻሻያ ቀደም ሲል ሲሰጥ ከነበረው የድጎማ መጠን ዝቅ አንዲል መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ ማሻሻያ የተደረገው ፦
- በአገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣
- የከተማ አውቶብሶች
- ፐብሊክ ባስ
- ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
በየ6 ወሩ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች የድጎማ መጠን ማስተካከያ የሚደረግ ሲሆን ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም ለሚቀጥሉት 6 ወራት ፦
* ለቤንዚን ተጠቃሚ አገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣የከተማ አውቶብሶች እና ፐብሊክ ባስ ብር 22.36 በሊትር ሲሰጥ የነበረውን ድጎማ ወደ 19.16 በሊትር ዝቅ እንዲል፣
* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲሰጥ የነበረው ብር 23.21 በሊትር ድጎማ በሊትር 19.89 ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡
የታለመ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር የሚሰጠው ድጎማ በየሶስት ወሩ የሚከለስ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በዚህም ፦
* ከጥር 1 ቀን 2016ዓ.ም እስከ መጋቢት 30 ቀን 2016ዓ.ም ድረስ ለቤንዚን ተጠቃሚዎች ሲስጥ የነበረው ብር 12.78 በሊትር ድጎማ ወደ 6.39 በሊትር፣
* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲስጥ የበነረው የብር 13.27 ድጎማ ወደ ብር 6.63 በሊትር ተቀናሽ እንዲሆን የተወሰነ መሆኑ ተገልጿል፡፡
መረጃው የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኤፍ ቢ ሲ ነው።
@tikvahethiopia
የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ስጪ በሆኑ ተሽከርካሪዎች ላይ የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ በተደርገ ማሻሻያ ቀደም ሲል ሲሰጥ ከነበረው የድጎማ መጠን ዝቅ አንዲል መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ ማሻሻያ የተደረገው ፦
- በአገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣
- የከተማ አውቶብሶች
- ፐብሊክ ባስ
- ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
በየ6 ወሩ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች የድጎማ መጠን ማስተካከያ የሚደረግ ሲሆን ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም ለሚቀጥሉት 6 ወራት ፦
* ለቤንዚን ተጠቃሚ አገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣የከተማ አውቶብሶች እና ፐብሊክ ባስ ብር 22.36 በሊትር ሲሰጥ የነበረውን ድጎማ ወደ 19.16 በሊትር ዝቅ እንዲል፣
* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲሰጥ የነበረው ብር 23.21 በሊትር ድጎማ በሊትር 19.89 ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡
የታለመ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር የሚሰጠው ድጎማ በየሶስት ወሩ የሚከለስ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በዚህም ፦
* ከጥር 1 ቀን 2016ዓ.ም እስከ መጋቢት 30 ቀን 2016ዓ.ም ድረስ ለቤንዚን ተጠቃሚዎች ሲስጥ የነበረው ብር 12.78 በሊትር ድጎማ ወደ 6.39 በሊትር፣
* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲስጥ የበነረው የብር 13.27 ድጎማ ወደ ብር 6.63 በሊትር ተቀናሽ እንዲሆን የተወሰነ መሆኑ ተገልጿል፡፡
መረጃው የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኤፍ ቢ ሲ ነው።
@tikvahethiopia
#አዲስአበባ #ነዳጅ
የኢትዮጵያ ነዳጅ አዳዮች ማህበር ፥ በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ዕጥረት መከሰቱንና ምክንያቱ ደግሞ ጅቡቲ ላይ የዘነበ ከባድ ዝናብን ተከትሎ የመንገድ መቆራረጥ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጿል።
በተጨማሪም አስቀድሞም ከቦታዉ በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እየተጫነ ባለመሆኑ መሆኑን አመልክቷል።
የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ደሳለኝ አበባየሁ ፥ እነዚህ ምክንያቶች ከነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች የተነገራቸዉ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ችግሩ ለመስተካከል ጊዜ ይወስድ እንደሆን የተጠየቁት አቶ ደሳለኝ " ጉዳዩ ትልቅ ነዉ፤ እንደ ቀላል የሚታይ አይደለም ያሉን ሲሆን፤ በእርግጠኝነት መንግስትም ሌት ተቀን ርብርብ አድርጎ ነገሮችን ያስተካክላል ብለን ተስፋ እናደርጋለን " ብለዋል።
ከጅቡቲ ከሚመጣዉ በተጨማሪ ክምችት ውስጥ ነዳጅ አልነበረም ወይ ? የተባሉት አቶ ደሳለኝ፤ " ቤንዚን ከአዋሽ ፣ ከሱሉልታ ዲፖዎች ነው እየተጫነ ያለዉ ፤ አሁን ላይ ግን ከክምችት ለመጫን ያልፈለጉበት የራሳቸዉ ምክንያት ይኖራቸዋል ፤ መንግስትም ይህንን አይቶ መፍትሄ ይሰጣል ብለን እንጠብቃለን " ብለዋል።
" አንድ ያለን መንገድ የጅቡቲ ብቻ ነዉ " ብለው " መንገዱ የተበላሸ በመሆኑ ደግሞ የመቆራረጥ ችግር ያጋጥማል ከባድ ዝናብ ሲዘንብ ደግሞ ችግሩን ከፍ ያደርገዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
" እንደዚህ ዓይነት ችግሮች የሚያግጥሙ በመሆኑ ለተወሰነ ጊዜ በትዕግስት ማለፍ አስፈላጊ ነው " ብለዋል።
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ ረጃጅም የነዳጅ ሰልፎች እየተስተዋሉ ይገኛል።
ይህ መረጃ የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ነዳጅ አዳዮች ማህበር ፥ በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ዕጥረት መከሰቱንና ምክንያቱ ደግሞ ጅቡቲ ላይ የዘነበ ከባድ ዝናብን ተከትሎ የመንገድ መቆራረጥ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጿል።
በተጨማሪም አስቀድሞም ከቦታዉ በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እየተጫነ ባለመሆኑ መሆኑን አመልክቷል።
የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ደሳለኝ አበባየሁ ፥ እነዚህ ምክንያቶች ከነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች የተነገራቸዉ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ችግሩ ለመስተካከል ጊዜ ይወስድ እንደሆን የተጠየቁት አቶ ደሳለኝ " ጉዳዩ ትልቅ ነዉ፤ እንደ ቀላል የሚታይ አይደለም ያሉን ሲሆን፤ በእርግጠኝነት መንግስትም ሌት ተቀን ርብርብ አድርጎ ነገሮችን ያስተካክላል ብለን ተስፋ እናደርጋለን " ብለዋል።
ከጅቡቲ ከሚመጣዉ በተጨማሪ ክምችት ውስጥ ነዳጅ አልነበረም ወይ ? የተባሉት አቶ ደሳለኝ፤ " ቤንዚን ከአዋሽ ፣ ከሱሉልታ ዲፖዎች ነው እየተጫነ ያለዉ ፤ አሁን ላይ ግን ከክምችት ለመጫን ያልፈለጉበት የራሳቸዉ ምክንያት ይኖራቸዋል ፤ መንግስትም ይህንን አይቶ መፍትሄ ይሰጣል ብለን እንጠብቃለን " ብለዋል።
" አንድ ያለን መንገድ የጅቡቲ ብቻ ነዉ " ብለው " መንገዱ የተበላሸ በመሆኑ ደግሞ የመቆራረጥ ችግር ያጋጥማል ከባድ ዝናብ ሲዘንብ ደግሞ ችግሩን ከፍ ያደርገዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
" እንደዚህ ዓይነት ችግሮች የሚያግጥሙ በመሆኑ ለተወሰነ ጊዜ በትዕግስት ማለፍ አስፈላጊ ነው " ብለዋል።
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ ረጃጅም የነዳጅ ሰልፎች እየተስተዋሉ ይገኛል።
ይህ መረጃ የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አዲስአበባ #ነዳጅ የኢትዮጵያ ነዳጅ አዳዮች ማህበር ፥ በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ዕጥረት መከሰቱንና ምክንያቱ ደግሞ ጅቡቲ ላይ የዘነበ ከባድ ዝናብን ተከትሎ የመንገድ መቆራረጥ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪም አስቀድሞም ከቦታዉ በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እየተጫነ ባለመሆኑ መሆኑን አመልክቷል። የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ደሳለኝ አበባየሁ ፥ እነዚህ ምክንያቶች ከነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች የተነገራቸዉ…
#ነዳጅ
" እስከ ነገ ጠዋት ድረስ ችግሩ ይቀረፋል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ፥ በአዲስ አበባ የነዳጅ እጥረት የተፈጠረው ጅቡቲ ላይ የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ድልድይ በመሰበሩ ነው ብሏል።
በተጨማሪም ነዳጅ የጫነ አንድ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ መንገድ መዘጋጋት በማስከተሉ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን ገልጿል።
ችግሩን ለመቅረፍ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች በድሬደዋ በኩል እንዲገቡ መደረጉን የገለጸው ድርጅቱ ይሄንኑ ተከትሎ ትናንት ከሰአት ጀምሮ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች መግባት መጀመራቸውን አሳውቋል።
#ዛሬ እና #ነገ ነዳጅ የጫኑ ተጨማሪ ቦቴዎች እንደሚገቡና ችግሩ እስከ ነገ ጠዋት ድረስ እንደሚቀረፍ ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጠው ቃል ገልጿል።
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ነዳጅ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል። አሽከርካሪዎች ነዳጅ ለማግኘት እጅግ ረጅም ሰልፍ ለመጠበቅ እየተገደዱ ሲሆን በዚህ ምክንያት ስራቸውም እየተስተጓጎለ ነው።
@tikvahethiopia
" እስከ ነገ ጠዋት ድረስ ችግሩ ይቀረፋል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ፥ በአዲስ አበባ የነዳጅ እጥረት የተፈጠረው ጅቡቲ ላይ የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ድልድይ በመሰበሩ ነው ብሏል።
በተጨማሪም ነዳጅ የጫነ አንድ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ መንገድ መዘጋጋት በማስከተሉ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን ገልጿል።
ችግሩን ለመቅረፍ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች በድሬደዋ በኩል እንዲገቡ መደረጉን የገለጸው ድርጅቱ ይሄንኑ ተከትሎ ትናንት ከሰአት ጀምሮ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች መግባት መጀመራቸውን አሳውቋል።
#ዛሬ እና #ነገ ነዳጅ የጫኑ ተጨማሪ ቦቴዎች እንደሚገቡና ችግሩ እስከ ነገ ጠዋት ድረስ እንደሚቀረፍ ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጠው ቃል ገልጿል።
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ነዳጅ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል። አሽከርካሪዎች ነዳጅ ለማግኘት እጅግ ረጅም ሰልፍ ለመጠበቅ እየተገደዱ ሲሆን በዚህ ምክንያት ስራቸውም እየተስተጓጎለ ነው።
@tikvahethiopia
#ነዳጅ ፦ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የነዳጅ ማደያዎች እለታዊ የነዳጅ አቅርቦት መጠንን ከትላንት ጀምሮ ይፋ ማድረግ ጀምሯል።
አሁን ላይ በከተማዋ 123 ማደያዎች ግልጋሎት እየሰጡ ነው ተብሏል።
ቢሮው ፤ " በየዕለቱ የነዋጅ ማደያዎችን እለታዊ የነዳጅ አቅርቦት መጠን ይፋ ማድረግ የተጀመረው በአገልግሎቱ ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲሁም የተገልጋች እንግልት ለመቀነስ ነው " ብሏል።
ነዳጅ ማደያዎች የት ቦታ እንደሚገኙ እና በእለቱ የተራገፈው ነዳጅ መጠን እንዲሁም የጥቆማ ስርዓቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
አሁን ላይ በከተማዋ 123 ማደያዎች ግልጋሎት እየሰጡ ነው ተብሏል።
ቢሮው ፤ " በየዕለቱ የነዋጅ ማደያዎችን እለታዊ የነዳጅ አቅርቦት መጠን ይፋ ማድረግ የተጀመረው በአገልግሎቱ ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲሁም የተገልጋች እንግልት ለመቀነስ ነው " ብሏል።
ነዳጅ ማደያዎች የት ቦታ እንደሚገኙ እና በእለቱ የተራገፈው ነዳጅ መጠን እንዲሁም የጥቆማ ስርዓቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
#ነዳጅ
ዛሬ በአዲስ አበባ የምትንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ነዳጅ ያለባቸውን ማደያዎች ከያዙት የነዳጅ መጠን ጨምሮ ከላይ በምስሉ መመልከት ትችላላችሁ።
#AddisAbabaTradeBureau
@tikvahethiopia
ዛሬ በአዲስ አበባ የምትንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ነዳጅ ያለባቸውን ማደያዎች ከያዙት የነዳጅ መጠን ጨምሮ ከላይ በምስሉ መመልከት ትችላላችሁ።
#AddisAbabaTradeBureau
@tikvahethiopia
#ነዳጅ ፦ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ዛሬ አገልግሎት የሚሰጡ ማደያዎች እና በመሰራጨት ላይ የሚገኝ የነዳጅ አቅርቦት መረጃ ከላይ ተያይዟል።
#AddisAbabaTradeBureau
@tikvahethiopia
#AddisAbabaTradeBureau
@tikvahethiopia
#ነዳጅ #ረቂቅአዋጅ
🔴" ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ ንግድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ አረጋግጠናል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
🔵 " ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል " - ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
በህገወጥ የነዳጅ ግብይት የታየዘ ግለሰብ ነዳጁ ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስራትና እስከ 100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ።
ረቂቁ ምን ይላል ?
- አዲስ የነዳጅ ምርት አከፋፋዮች ስራ ለመጀመር ቢያንስ 500 ሺህ ሊትር የነዳጅ ውጤቶች መያዝ የሚችል ማከማቻ / ዴፖ እና 4 ማደያዎችን ማዘጋጀት እንዳለባቸው ያስገድዳል።
- በስራ ላይ ያሉ ማደያዎች ደግሞ አዋጁ ከሚጸድቅበት ጊዜ ጀምሮ ለአዲስ አከፋፋዮች የተጣሉትን ግዴታዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- አዲስ ጀማሪ ሆኑ ነባሮቹ በ3 ዓመታት ውስጥ ተጨማሪ 6 ማደያዎችን የመገንባት ግዴታ አለባቸው።
- የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ያከማቸ፣ ሊሸጥ ከሚገባው ሰው ቦታና የግብይት ስርዓት ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ወይም አደጋ ያስከትላሉ በተባሉ መያዣዎች ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ የተያዘው የነዳጅ ውጤት ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስርና ከብር 50 ሺህ እስከ ብር 100 ሺህ የሚደርስ ቅጣት ይፈጸምበታል።
- መንግሥት ከሚያወጣው የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ተመን ውጪ በተደጋጋሚ የመገበያየት ወንጀል እንዲሁም የነዳጅ ምርቶችን ከባዕድ ነገሮች ጋር መቀላቀል እስከ 3 ዓመት እስርና እስከ 300 ሺህ ብር ቅጣት ያስጥላል።
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ እስመለአለም ምህረቱ ምን አሉ ?
አሁን አሁን ወደነዳጅ አቅራቢነት ስራ ለመሰማራት ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ነው ብለዋል።
በድርጅቱ በተደረገው ጥናት ይህ ፍላጎት የኮንትሮባንድ ንግድ እና ከባንክ ብድር ለመወሰድ ተብሎ የሚደረግ እንደሆነ ተደርሶበታል ሲሉ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ፥ በዚህ 9 እና 10 ዓመት ውስጥ ከነበሩት 8 ወይም 9 ካምፓኒዎች አሁን 59 መድረሳቸውን ጠቁመዋል።
3ቱ የመንግሥት ገንዘብ አባክነው በፍርድ ቤት ክርክር ላይ ናቸው።
56ቱ ካምፓኒዎችን በማርኬትሼር በመደልደል ነዳጅ እየተሰጠ መሆኑን የገለጹ ሲሆን " ይህ ሁኔታ እራሱ እስካሁን ስምምነት የሌለበት ሁልጊዜ ጭቅጭቅ ያለበት ድርጊት ነው " ብለዋል።
ወደ ነዳጅ ግብይት አዲስ የሚገቡ ካምፓኒዎችን በተመለከተ ምንድነው አላማቸው ? ለምንድነው እንዲህ እያደገ የመጣው የሚለው መጠናቱን ገልጸዋል።
በጥናቱ ውጤትም " ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ ነው የተረጋገጠው " ብለዋል።
እነዚህ የነዳጅ ካምፓኒዎች ባንኮች ጋር ሄደው ብድር በሚጠይቁበት ጊዜ ባንኮቹ " ከናተ ጋር ያላቸው የሥራ አፈጻጸም ይጻፍልን " እየተባለ ደብዳቤ እንደሚጻፍ ገልጸዋል።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
° አዋጁ አላማ መንግሥት በየዓመቱ በሚሊዮን ዶላሮች የሚያወጣበትን ለነዳጅ ምርት በአግባቡ ለማስተዳደር ነው።
° በመንግሥት በኩል የነዳጅ አቅርቦትን የማበራከት አላማ የለም።
° አዋጁ በእያንዳዱ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ ባሉት ተዋናዮች ላይ የህግ ሪስትሪክሽኖችን ይጥላል። የአቅራቢ፣ የማደያ ... ግዴታዎች አሉ።
° ግብይታችን ችግር አለበት። የአቅርቦት ችግር ሳይኖር ስርጭት ላይ ትልቅ ችግር አለ። የታሰበላቸው ቦታ ያለመድረስን በተመለከተ በክልሎች የሚቀርበው ቅሬታ ገሚሱ ትክክል ነው።
° ነዳጅ አለ !! ሳምንት ሁለት ሳምንት ገበያ ማስራብ ፣ በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ ነዳጅ ይዞ ' ቤንዚን የለም ፤ ናፍጣ የለም ' ብሎ መለጠፍ ይሄ ደግሞ ተጠያቂነት የማያስከትልበት ሴክተራል ባህሪው እንዲቀየር ይታሰባል፤ ይፈለጋል በመንግሥት በኩል ለዛም ነው ይሄ አዋጅ የሚወጣው።
° ከዚህ በኃላ ንግድን አንከለክልም እናሰፋዋለን ፤ ግብይቱ እንዲሳለጥ እንፈልጋለን ነገር ግን ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል።
° የነዳጅ ኮታ እና ስርጭት ላይ ፍትሃዊ ስርዓት ለመፍጠር ይሰራል።
° ከአቅርቦት እና ስርጭት ይልቅ ማስተዳደሩ ከባድ ነው።
° ነዳጅ እያላቸው ዘግተው የሚቀመጡ ማደያዎች በስፋት አሉ። የቅጣት መጠኑ ላይ ጠንካራ ስራ ይሰራል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሪፖርተር እንዲሁም ከህ/ተ/ም/ቤት የቀጥታ ስርጭት ማግኘቱን ይገልጻል።
#ኢትዮጵያ #ነዳጅ #ረቂቅአዋጅ
@tikvahethiopia
🔴" ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ ንግድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ አረጋግጠናል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
🔵 " ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል " - ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
በህገወጥ የነዳጅ ግብይት የታየዘ ግለሰብ ነዳጁ ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስራትና እስከ 100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ።
ረቂቁ ምን ይላል ?
- አዲስ የነዳጅ ምርት አከፋፋዮች ስራ ለመጀመር ቢያንስ 500 ሺህ ሊትር የነዳጅ ውጤቶች መያዝ የሚችል ማከማቻ / ዴፖ እና 4 ማደያዎችን ማዘጋጀት እንዳለባቸው ያስገድዳል።
- በስራ ላይ ያሉ ማደያዎች ደግሞ አዋጁ ከሚጸድቅበት ጊዜ ጀምሮ ለአዲስ አከፋፋዮች የተጣሉትን ግዴታዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- አዲስ ጀማሪ ሆኑ ነባሮቹ በ3 ዓመታት ውስጥ ተጨማሪ 6 ማደያዎችን የመገንባት ግዴታ አለባቸው።
- የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ያከማቸ፣ ሊሸጥ ከሚገባው ሰው ቦታና የግብይት ስርዓት ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ወይም አደጋ ያስከትላሉ በተባሉ መያዣዎች ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ የተያዘው የነዳጅ ውጤት ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስርና ከብር 50 ሺህ እስከ ብር 100 ሺህ የሚደርስ ቅጣት ይፈጸምበታል።
- መንግሥት ከሚያወጣው የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ተመን ውጪ በተደጋጋሚ የመገበያየት ወንጀል እንዲሁም የነዳጅ ምርቶችን ከባዕድ ነገሮች ጋር መቀላቀል እስከ 3 ዓመት እስርና እስከ 300 ሺህ ብር ቅጣት ያስጥላል።
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ እስመለአለም ምህረቱ ምን አሉ ?
አሁን አሁን ወደነዳጅ አቅራቢነት ስራ ለመሰማራት ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ነው ብለዋል።
በድርጅቱ በተደረገው ጥናት ይህ ፍላጎት የኮንትሮባንድ ንግድ እና ከባንክ ብድር ለመወሰድ ተብሎ የሚደረግ እንደሆነ ተደርሶበታል ሲሉ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ፥ በዚህ 9 እና 10 ዓመት ውስጥ ከነበሩት 8 ወይም 9 ካምፓኒዎች አሁን 59 መድረሳቸውን ጠቁመዋል።
3ቱ የመንግሥት ገንዘብ አባክነው በፍርድ ቤት ክርክር ላይ ናቸው።
56ቱ ካምፓኒዎችን በማርኬትሼር በመደልደል ነዳጅ እየተሰጠ መሆኑን የገለጹ ሲሆን " ይህ ሁኔታ እራሱ እስካሁን ስምምነት የሌለበት ሁልጊዜ ጭቅጭቅ ያለበት ድርጊት ነው " ብለዋል።
ወደ ነዳጅ ግብይት አዲስ የሚገቡ ካምፓኒዎችን በተመለከተ ምንድነው አላማቸው ? ለምንድነው እንዲህ እያደገ የመጣው የሚለው መጠናቱን ገልጸዋል።
በጥናቱ ውጤትም " ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ ነው የተረጋገጠው " ብለዋል።
እነዚህ የነዳጅ ካምፓኒዎች ባንኮች ጋር ሄደው ብድር በሚጠይቁበት ጊዜ ባንኮቹ " ከናተ ጋር ያላቸው የሥራ አፈጻጸም ይጻፍልን " እየተባለ ደብዳቤ እንደሚጻፍ ገልጸዋል።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
° አዋጁ አላማ መንግሥት በየዓመቱ በሚሊዮን ዶላሮች የሚያወጣበትን ለነዳጅ ምርት በአግባቡ ለማስተዳደር ነው።
° በመንግሥት በኩል የነዳጅ አቅርቦትን የማበራከት አላማ የለም።
° አዋጁ በእያንዳዱ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ ባሉት ተዋናዮች ላይ የህግ ሪስትሪክሽኖችን ይጥላል። የአቅራቢ፣ የማደያ ... ግዴታዎች አሉ።
° ግብይታችን ችግር አለበት። የአቅርቦት ችግር ሳይኖር ስርጭት ላይ ትልቅ ችግር አለ። የታሰበላቸው ቦታ ያለመድረስን በተመለከተ በክልሎች የሚቀርበው ቅሬታ ገሚሱ ትክክል ነው።
° ነዳጅ አለ !! ሳምንት ሁለት ሳምንት ገበያ ማስራብ ፣ በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ ነዳጅ ይዞ ' ቤንዚን የለም ፤ ናፍጣ የለም ' ብሎ መለጠፍ ይሄ ደግሞ ተጠያቂነት የማያስከትልበት ሴክተራል ባህሪው እንዲቀየር ይታሰባል፤ ይፈለጋል በመንግሥት በኩል ለዛም ነው ይሄ አዋጅ የሚወጣው።
° ከዚህ በኃላ ንግድን አንከለክልም እናሰፋዋለን ፤ ግብይቱ እንዲሳለጥ እንፈልጋለን ነገር ግን ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል።
° የነዳጅ ኮታ እና ስርጭት ላይ ፍትሃዊ ስርዓት ለመፍጠር ይሰራል።
° ከአቅርቦት እና ስርጭት ይልቅ ማስተዳደሩ ከባድ ነው።
° ነዳጅ እያላቸው ዘግተው የሚቀመጡ ማደያዎች በስፋት አሉ። የቅጣት መጠኑ ላይ ጠንካራ ስራ ይሰራል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሪፖርተር እንዲሁም ከህ/ተ/ም/ቤት የቀጥታ ስርጭት ማግኘቱን ይገልጻል።
#ኢትዮጵያ #ነዳጅ #ረቂቅአዋጅ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ። ከመስከረም 28/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በሥራ ላይ የሚቆይ የሁሉም የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉ ተሰምቷል። በዚህ መሰረት፦ ➡️ ቤንዚን - ብር 91.14 በሊትር ➡️ ነጭ ናፍጣ - ብር 90.28 በሊትር ➡️ ኬሮሲን - ብር 90.28 በሊትር ➡️ ቀላል ጥቁር ናፍጣ - ብር 100.20 በሊትር ➡️ ከባድ ጥቁር ናፍጣ - ብር…
#ነዳጅ
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ የታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በህዳር ወር በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ " የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች ያልተገባ የነዳጅ ክምችት ከመያዝ እና የዋጋ ጭማሪ ከማድረግ ተቆጥበው ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ " ሲል አሳስቧል።
የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?
➡️ ቤንዚን - ብር 91.14 በሊትር
➡️ ነጭ ናፍጣ - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ኬሮሲን - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ቀላል ጥቁር ናፍጣ - ብር 100.20 በሊትር
➡️ ከባድ ጥቁር ናፍጣ - ብር 97.67 በሊትር
➡️ የአውሮፕላን ነዳጅ - ብር 77.76 በሊትር ሆኗል።
@tikvahethiopia
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ የታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በህዳር ወር በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ " የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች ያልተገባ የነዳጅ ክምችት ከመያዝ እና የዋጋ ጭማሪ ከማድረግ ተቆጥበው ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ " ሲል አሳስቧል።
የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?
➡️ ቤንዚን - ብር 91.14 በሊትር
➡️ ነጭ ናፍጣ - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ኬሮሲን - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ቀላል ጥቁር ናፍጣ - ብር 100.20 በሊትር
➡️ ከባድ ጥቁር ናፍጣ - ብር 97.67 በሊትር
➡️ የአውሮፕላን ነዳጅ - ብር 77.76 በሊትር ሆኗል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ የታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በህዳር ወር በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል። ሚኒስቴሩ " የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች ያልተገባ የነዳጅ ክምችት ከመያዝ እና የዋጋ ጭማሪ ከማድረግ ተቆጥበው ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን…
#ነዳጅ
ቤንዚን በሊትር 101.47 ብር ሲገባ ናፍጣ በሊትር 98.98 ብር ሆኗል።
ዛሬ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2017 ዓ/ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ መወሰኑን አሳውቋል።
በዚሁ መሰረት ፦
➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር
➡ አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር
➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር
➡ የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር
➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር
➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር ሆኖ እንዲሸጥ ተወስኗል።
#ነዳጅ #ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
ቤንዚን በሊትር 101.47 ብር ሲገባ ናፍጣ በሊትር 98.98 ብር ሆኗል።
ዛሬ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2017 ዓ/ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ መወሰኑን አሳውቋል።
በዚሁ መሰረት ፦
➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር
➡ አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር
➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር
➡ የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር
➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር
➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር ሆኖ እንዲሸጥ ተወስኗል።
#ነዳጅ #ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
#ነዳጅ
⛽️“ ነዳጅን በኮፓን የማድረግ እሳቤው በነዳጅ እጦት ተማረን ግዴታ የኤሌክትራክ ተሽከርካሪ እንድንጠቀም ለማድረግ ነው ” - አሽከርካሪዎች
➡️ “ ማደያ የነበረው ነዳጅ ሲጎድል የወሰዱትን በሁለት፣ በሦስት እጥፍ ጨምረው የመሸጥ ሁኔታዎች እንዳሉ በጥናት አረጋግጠናል” - ቢሮው
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ከጥር 30 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ነዳጅ የሚቀዳው ኩፓን እንደሆነ የሚገልጽ ሰርኩላር ከቀናት በፊት አውርዷል።
እንደ ቢሮው ገለጻ ከሆነ መመሪያውን ለማውረድ የተገደደው በተለይ ባለሁለትና ሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ነዳጅ በተደጋጋሚ በመቅዳት በውድ ዋጋ እየሸጡ ሌሎቹን ለነዳጅ እጥረት እያጋለጡ በመሆኑ ነው።
መመሪያውን በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ አሽከርካሪዎች ደግሞ፣ “ ነዳጅ በኩፖን እንዲሆን የተደረገው በአሽከርካሪዎች ሳቢያ ነው መባሉ የተጨፈለቀ እሳቤና እንደማንፈለግ ማሳያ ነው ” ሲሉ ትችታቸውን አቅርበዋል።
ጉዳዩን በጥናት ደርሰውበት ከሆነም ድርጊቱን የፈጸሙት ላይ እርምጃ መውሰድ እንጅ ሁሉን በአንድ ላይ ጨፍልቆ መውቀስ ተገቢ እንዳልሆነ ገልጸው፣ “ ነዳጅን በኮፖን የማድረግ እሳቤው በነዳጅ ተማረን ግዴታ የኤሌክትራክ ተሽከርካሪ እንድንጠቀም ለማድረግ ነው ” ብለዋል።
“ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪውንም መጠቀም አይገደንም ” ያሉት አሽከርካሪዎቹ፣ “ ግን በየትኛው የተሟላ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ነው የምንጠቀመው ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ነዳጅ በኮፖን እንዲቀዳ የተላለፈውን መመሪያ ተከትሎ ላቀረቡት ቅሬታና ስጋት ምላሽ እንዲሰጡ የቢሮውን ምክትል ኃላፊና የኮሚዩኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ታዲሁንን ጠይቋል።
ምን መለሱ?
“ ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ጋር የሚገናኝ ነገር የለም፡፡
የአገሪቱ የቀጣይ አቅጣጫ በእርግጥ እየተከተልን ካለነው ዓለማዊ አጠቃላይ ሁኔታ አኳያ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪን መጠቀም ጠቀሜታው የጎላ ነው ወደዛም ነው የምንሄደው በሂደት፡፡
ግን ዛሬ በአስገዳጅ ሁኔታ ይህን ፈጽሙ የሚል የተቀመጠ አቅጣጫ የለም፡፡ የኛም ፍላጎት ይሄ አይደለም፡፡ ችግሩን መፍታት ስላለብን ነው፡፡
ደብዳቤውም ሲጻፍ አጠቃላይ በክልሉ ያሉ ባለሁለትም ሆነ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ይህንን ወንጀል ፈጽመዋል የሚል ኢንቴንሽን የለውም፡፡ ይሄን አይነት እይታ የለንም፡፡
ግን ችግሩን የሚፈጥሩ አካላት በስፋት አሉ። ችግሩ በገሃድ የሚታይ ነው፡፡ የህዝቡም ቅሬታ ነው፡፡ ስለዚህ ካለው ነገር አኳያ ችግሩን ለመቅረፍ ከተቀመጡ አሰራሮች ውስጥ አንዱን ተግባራዊ ወደ ማድረግ ነው የገባነው፡፡
ይሄ ሲባል ሁሉም አሽከርካሪ በዚህ ደረጃ ወንጀል እየሰራ ነው የሚል እይታ የለንም፡፡ ግን ችግር የሚፈጥሩ አካላትን ለይቶ እርምጃ ለመውሰድ ያገለግለናል ” ብለዋል።
አጠቃላይ መመሪያውን መተግበር ያስፈለገበትን ምክንያት በተመለከተ ጠይቀናቸው በሰጡት ምላሽስ ምን አሉ ?
“ ምርት በስፋት ይገባ ነበር ከዚህ በፊት። የሚመጣው ምርት ግን በተቃራኒው ወደ ተለያዩ አካባቢዎች የሚወጣበት፣ የሚባክንበት ሁኔታ አለ። ምርትን ከካምፓኒዎች ተቀብለው የሚያሰራጩ የማደያ ባለቤቶችም አሉ።
ሁሉም ማለት አይቻልም የተወሰኑት ግን ለሚፈለገው አገልገግሎት እንዳይውል ጨለማን ተገን በማድረግ የድለላ ሥራ ለሚሰሩ አካላት በመስጠት የመጣን የነዳጅ ምርት ግማሽ ወይም ሙሉውን ዋጋ ጨምረው በአይሱዚ ጭነው የማውጣት ሁኔታዎች አሉ።
ከዚያ ባሸገር ግን እንደ ክልል በጣም የተቸገርነው የባጃጅና ሞተር ተሽከርካሪዎች ነዳጅ ከቀዱ በኋላ ውስጥ ለውስጥ ባሉ ቤቶች ውስጥ ወስደው ወደ ልላ እቃ በመገልበጥ በቀን ብዙ ዙር በመመላስ ነዳጅ ይቀዳሉ።
ያ ሲሆን ማደያ የነበረው ነዳጅ ሲጎድል የወሰዱትን በሁለት፣ በሦስት እጥፍ ጨምረው የመሸጥ ሁኔታዎች እንዳሉ በጥናት አረጋግጠናል። አብዛኛዎቹ ላይ እርምጃ ወስደናል።
ስለዚህ ይሄን ችግር ለመፍታት ሲባል ከዚህ በፊት በሪፎርም የተቀመጠ አሰራር ስለነበረ ይሄን አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ተብሎ ነው በአዲስ መልክ ሰርኩላር የተጻፈው።
ስለዚህ በአካባቢው ያሉ የንግድ ተቋማት ኮፖን ያዘጋጃሉ። ኮፓን ሲያዘጋጁ የአሽከርካሪው ስም፣ ፎቶ፣ የተሽከርካሪው ታርጋና ውስጥ ክፍል ያለ የሞተር ሚስጢር ቁጥር በማካተት ነው የሚዘጋጀው።
ያ ሲሆን ለአሽከርካሪው ትክክለኛ ምድባ ይደረለታል። በዚህ መልክ ስምሪት ይሰጥና በተፈቀደለት ቦታ ተኪዶ ነዳጅ ይቀዳል። ለአገልግሎት ሲያውል ተመልሶ ይቀዳል። ” ብለዋል።
ይህ በጥናት ጭምር የተረጋገጠ ከሆነ ነዳጅን አውጥቶ በመሸጥ አኳያ በተጨባጭ ምን ያህል አሽከርካሪዎችና ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል? ስንል ተጨማሪ ጥያቄ አቅርበናል።
ቢሮው ምን ምላሽ ሰጠ ?
“ ዋናው መሠረቱ፣ ምንጩ ማደያው ስለሆነ እሱ ላይም ቁጥጥር ተደርጓል። በተደጋጋሚ ከተለያዩ አካባቢዎች እርምጃ የተወሰደባቸው ወደ ሰባት ማደያዎች አሉ።
ወላይታ ዞን ወደ 4 ቦታዎች፣ ጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ ላይ፣ ጌዲዮ ዞን ላይ ይርጋጨፌ ከተማ፣ ሌሎቹም ጋ የነበሩትን አሽጎ በህግ ሂደት የተከሰሱበት ሁኔታ አለ።
የነዳጅ ምርቶችን ይዘው ሲንቀሳቀሱ የተገኙት ቁጥር ስፍር የለውም።
የተሽከርካሪዎቹ ቅርብ ጊዜ ነው በጥናት የተረጋገጠው። ከዚያ አኳያ ይህን ሰርኩላር መበተን ነበረብን። ግን በተጨባጭ ችግሩን እያወሳሰቡ ያሉት እነርሱ ናቸው። ” ሲሉ መልሰዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
⛽️“ ነዳጅን በኮፓን የማድረግ እሳቤው በነዳጅ እጦት ተማረን ግዴታ የኤሌክትራክ ተሽከርካሪ እንድንጠቀም ለማድረግ ነው ” - አሽከርካሪዎች
➡️ “ ማደያ የነበረው ነዳጅ ሲጎድል የወሰዱትን በሁለት፣ በሦስት እጥፍ ጨምረው የመሸጥ ሁኔታዎች እንዳሉ በጥናት አረጋግጠናል” - ቢሮው
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ከጥር 30 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ነዳጅ የሚቀዳው ኩፓን እንደሆነ የሚገልጽ ሰርኩላር ከቀናት በፊት አውርዷል።
እንደ ቢሮው ገለጻ ከሆነ መመሪያውን ለማውረድ የተገደደው በተለይ ባለሁለትና ሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ነዳጅ በተደጋጋሚ በመቅዳት በውድ ዋጋ እየሸጡ ሌሎቹን ለነዳጅ እጥረት እያጋለጡ በመሆኑ ነው።
መመሪያውን በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ አሽከርካሪዎች ደግሞ፣ “ ነዳጅ በኩፖን እንዲሆን የተደረገው በአሽከርካሪዎች ሳቢያ ነው መባሉ የተጨፈለቀ እሳቤና እንደማንፈለግ ማሳያ ነው ” ሲሉ ትችታቸውን አቅርበዋል።
ጉዳዩን በጥናት ደርሰውበት ከሆነም ድርጊቱን የፈጸሙት ላይ እርምጃ መውሰድ እንጅ ሁሉን በአንድ ላይ ጨፍልቆ መውቀስ ተገቢ እንዳልሆነ ገልጸው፣ “ ነዳጅን በኮፖን የማድረግ እሳቤው በነዳጅ ተማረን ግዴታ የኤሌክትራክ ተሽከርካሪ እንድንጠቀም ለማድረግ ነው ” ብለዋል።
“ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪውንም መጠቀም አይገደንም ” ያሉት አሽከርካሪዎቹ፣ “ ግን በየትኛው የተሟላ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ነው የምንጠቀመው ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ነዳጅ በኮፖን እንዲቀዳ የተላለፈውን መመሪያ ተከትሎ ላቀረቡት ቅሬታና ስጋት ምላሽ እንዲሰጡ የቢሮውን ምክትል ኃላፊና የኮሚዩኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ታዲሁንን ጠይቋል።
ምን መለሱ?
“ ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ጋር የሚገናኝ ነገር የለም፡፡
የአገሪቱ የቀጣይ አቅጣጫ በእርግጥ እየተከተልን ካለነው ዓለማዊ አጠቃላይ ሁኔታ አኳያ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪን መጠቀም ጠቀሜታው የጎላ ነው ወደዛም ነው የምንሄደው በሂደት፡፡
ግን ዛሬ በአስገዳጅ ሁኔታ ይህን ፈጽሙ የሚል የተቀመጠ አቅጣጫ የለም፡፡ የኛም ፍላጎት ይሄ አይደለም፡፡ ችግሩን መፍታት ስላለብን ነው፡፡
ደብዳቤውም ሲጻፍ አጠቃላይ በክልሉ ያሉ ባለሁለትም ሆነ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ይህንን ወንጀል ፈጽመዋል የሚል ኢንቴንሽን የለውም፡፡ ይሄን አይነት እይታ የለንም፡፡
ግን ችግሩን የሚፈጥሩ አካላት በስፋት አሉ። ችግሩ በገሃድ የሚታይ ነው፡፡ የህዝቡም ቅሬታ ነው፡፡ ስለዚህ ካለው ነገር አኳያ ችግሩን ለመቅረፍ ከተቀመጡ አሰራሮች ውስጥ አንዱን ተግባራዊ ወደ ማድረግ ነው የገባነው፡፡
ይሄ ሲባል ሁሉም አሽከርካሪ በዚህ ደረጃ ወንጀል እየሰራ ነው የሚል እይታ የለንም፡፡ ግን ችግር የሚፈጥሩ አካላትን ለይቶ እርምጃ ለመውሰድ ያገለግለናል ” ብለዋል።
አጠቃላይ መመሪያውን መተግበር ያስፈለገበትን ምክንያት በተመለከተ ጠይቀናቸው በሰጡት ምላሽስ ምን አሉ ?
“ ምርት በስፋት ይገባ ነበር ከዚህ በፊት። የሚመጣው ምርት ግን በተቃራኒው ወደ ተለያዩ አካባቢዎች የሚወጣበት፣ የሚባክንበት ሁኔታ አለ። ምርትን ከካምፓኒዎች ተቀብለው የሚያሰራጩ የማደያ ባለቤቶችም አሉ።
ሁሉም ማለት አይቻልም የተወሰኑት ግን ለሚፈለገው አገልገግሎት እንዳይውል ጨለማን ተገን በማድረግ የድለላ ሥራ ለሚሰሩ አካላት በመስጠት የመጣን የነዳጅ ምርት ግማሽ ወይም ሙሉውን ዋጋ ጨምረው በአይሱዚ ጭነው የማውጣት ሁኔታዎች አሉ።
ከዚያ ባሸገር ግን እንደ ክልል በጣም የተቸገርነው የባጃጅና ሞተር ተሽከርካሪዎች ነዳጅ ከቀዱ በኋላ ውስጥ ለውስጥ ባሉ ቤቶች ውስጥ ወስደው ወደ ልላ እቃ በመገልበጥ በቀን ብዙ ዙር በመመላስ ነዳጅ ይቀዳሉ።
ያ ሲሆን ማደያ የነበረው ነዳጅ ሲጎድል የወሰዱትን በሁለት፣ በሦስት እጥፍ ጨምረው የመሸጥ ሁኔታዎች እንዳሉ በጥናት አረጋግጠናል። አብዛኛዎቹ ላይ እርምጃ ወስደናል።
ስለዚህ ይሄን ችግር ለመፍታት ሲባል ከዚህ በፊት በሪፎርም የተቀመጠ አሰራር ስለነበረ ይሄን አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ተብሎ ነው በአዲስ መልክ ሰርኩላር የተጻፈው።
ስለዚህ በአካባቢው ያሉ የንግድ ተቋማት ኮፖን ያዘጋጃሉ። ኮፓን ሲያዘጋጁ የአሽከርካሪው ስም፣ ፎቶ፣ የተሽከርካሪው ታርጋና ውስጥ ክፍል ያለ የሞተር ሚስጢር ቁጥር በማካተት ነው የሚዘጋጀው።
ያ ሲሆን ለአሽከርካሪው ትክክለኛ ምድባ ይደረለታል። በዚህ መልክ ስምሪት ይሰጥና በተፈቀደለት ቦታ ተኪዶ ነዳጅ ይቀዳል። ለአገልግሎት ሲያውል ተመልሶ ይቀዳል። ” ብለዋል።
ይህ በጥናት ጭምር የተረጋገጠ ከሆነ ነዳጅን አውጥቶ በመሸጥ አኳያ በተጨባጭ ምን ያህል አሽከርካሪዎችና ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል? ስንል ተጨማሪ ጥያቄ አቅርበናል።
ቢሮው ምን ምላሽ ሰጠ ?
“ ዋናው መሠረቱ፣ ምንጩ ማደያው ስለሆነ እሱ ላይም ቁጥጥር ተደርጓል። በተደጋጋሚ ከተለያዩ አካባቢዎች እርምጃ የተወሰደባቸው ወደ ሰባት ማደያዎች አሉ።
ወላይታ ዞን ወደ 4 ቦታዎች፣ ጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ ላይ፣ ጌዲዮ ዞን ላይ ይርጋጨፌ ከተማ፣ ሌሎቹም ጋ የነበሩትን አሽጎ በህግ ሂደት የተከሰሱበት ሁኔታ አለ።
የነዳጅ ምርቶችን ይዘው ሲንቀሳቀሱ የተገኙት ቁጥር ስፍር የለውም።
የተሽከርካሪዎቹ ቅርብ ጊዜ ነው በጥናት የተረጋገጠው። ከዚያ አኳያ ይህን ሰርኩላር መበተን ነበረብን። ግን በተጨባጭ ችግሩን እያወሳሰቡ ያሉት እነርሱ ናቸው። ” ሲሉ መልሰዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ ቤንዚን በሊትር 101.47 ብር ሲገባ ናፍጣ በሊትር 98.98 ብር ሆኗል። ዛሬ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2017 ዓ/ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ መወሰኑን አሳውቋል። በዚሁ መሰረት ፦ ➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር…
#ነዳጅ
የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።
የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር
➡ አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር
➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር
➡ የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር
➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር
➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር
#ነዳጅ #ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።
የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር
➡ አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር
➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር
➡ የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር
➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር
➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር
#ነዳጅ #ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia