" አደጋው አስደንጋጭ ድንገተኛ ክሰተትና መላው የተቋሙን ማህበረሰብ መሪር ሃዘን ላይ የጣለ ነው " - ቀብሪ ደሃር ዩኒቨርሲቲ
4 የቀብሪ ደሃር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በመኪና አደጋ ህይወታቸው አለፈ።
ትላንት መጋቢት 9 ቀን 2015 ዓ/ም በደረሰ የመኪና አደጋ 4 የቀብሪ ደሃር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህይወታቸው ማለፉን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ዩኒቨርሲቲው ስለ አደጋው ዝርዝር መረጃ ባይሰጥም አደጋው እጅግ በጣም አስደንጋጭ ድንገተኛ ክስተትና መላው የተቋሙን ማህበረሰብ መሪር ሃዘን ላይ የጣለ ነው ብሏል።
ተቋሙ በመኪና አደጋ ህይወታቸው እንዳለፈ ካሳወቃቸው ተማሪዎች ሶስቱ የሶስተኛ ዓመት ተማሪዎቹ አንዱ ደግሞ የአራተኛ አመት ተማሪ መሆኑን ገልጿል።
ስማቸውም ደሳለው ፈጠነ (ከተፈጥሮ ሃብት አያያዝ) ፣ በላይ አንዱዓለም (ከተፈጥሮ ሃብት አያያዝ) ፣ አቸነፍ አሰፋ (ከአግሮ ቢዝነስ) ፣ በላቸው አሳየ (ከአግሮ ቢዝነስ) መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
4 የቀብሪ ደሃር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በመኪና አደጋ ህይወታቸው አለፈ።
ትላንት መጋቢት 9 ቀን 2015 ዓ/ም በደረሰ የመኪና አደጋ 4 የቀብሪ ደሃር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህይወታቸው ማለፉን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ዩኒቨርሲቲው ስለ አደጋው ዝርዝር መረጃ ባይሰጥም አደጋው እጅግ በጣም አስደንጋጭ ድንገተኛ ክስተትና መላው የተቋሙን ማህበረሰብ መሪር ሃዘን ላይ የጣለ ነው ብሏል።
ተቋሙ በመኪና አደጋ ህይወታቸው እንዳለፈ ካሳወቃቸው ተማሪዎች ሶስቱ የሶስተኛ ዓመት ተማሪዎቹ አንዱ ደግሞ የአራተኛ አመት ተማሪ መሆኑን ገልጿል።
ስማቸውም ደሳለው ፈጠነ (ከተፈጥሮ ሃብት አያያዝ) ፣ በላይ አንዱዓለም (ከተፈጥሮ ሃብት አያያዝ) ፣ አቸነፍ አሰፋ (ከአግሮ ቢዝነስ) ፣ በላቸው አሳየ (ከአግሮ ቢዝነስ) መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " እናት እና ልጅን ጨምሮ አራት ሰዎች በጎርፍ ተወስደዋል " በአዲስ አበባ ትናንት ምሽት በጣለው ዝናብ እናት እና ልጆችን ጨምሮ አራት ሰዎች በጎርፍ መወሰዳቸውን የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳውቋል። ትናንት ምሽት የጣለውን ዝናብ ተከትሎ ከምሽቱ 12:05 ሰዓት በንፋስስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ማንጎ ሰፈር ወንዝ ዳርቻ ላይ በሚገኙ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ ጎርፍ…
" የአራቱም ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል " - የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ ከተማ ወረዳ 12 በተለምዶ " ማንጎ ሰፈር " እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 9 ቀን 2015 ዓ.ም በደረሰዉ የጎርፍ አደጋ #እናት እና #ልጅን ጨምሮ 4 ሰዎች በጎርፍ መወሰዳቸዉን ተከትሎ የአስክሬን ፍለጋ ሲደረግ ውሏል።
በዚህም የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የዋናተኛ ቡድን የአራቱንም ሰዎች አስከሬን ማግኘት እንደቻለ ኮሚሽኑ አሳውቋል።
የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሟቾቹን አስከሬን ለማግኘት በተደረገዉ ጥረት ለአካባቢዉ ማህበረሰብና ለጸጥታ ሀይሎች ምስጋናዉን አቅርቧል።
#ሰሞኑን_እየጣለ_ባለዉ_ዝናብ ተመሳሳይ አደጋ እንዳያጋጥም ህብረተሰቡ አስፈላጊዉን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኮሚሽን መ/ቤቱ አሳስቧል።
ምንጭ፦ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ ከተማ ወረዳ 12 በተለምዶ " ማንጎ ሰፈር " እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 9 ቀን 2015 ዓ.ም በደረሰዉ የጎርፍ አደጋ #እናት እና #ልጅን ጨምሮ 4 ሰዎች በጎርፍ መወሰዳቸዉን ተከትሎ የአስክሬን ፍለጋ ሲደረግ ውሏል።
በዚህም የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የዋናተኛ ቡድን የአራቱንም ሰዎች አስከሬን ማግኘት እንደቻለ ኮሚሽኑ አሳውቋል።
የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሟቾቹን አስከሬን ለማግኘት በተደረገዉ ጥረት ለአካባቢዉ ማህበረሰብና ለጸጥታ ሀይሎች ምስጋናዉን አቅርቧል።
#ሰሞኑን_እየጣለ_ባለዉ_ዝናብ ተመሳሳይ አደጋ እንዳያጋጥም ህብረተሰቡ አስፈላጊዉን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኮሚሽን መ/ቤቱ አሳስቧል።
ምንጭ፦ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
@tikvahethiopia
" ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፍ አልጠራሁም " - የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት የጠራው ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን አሳውቋል።
በዚህ ዓመት ሊሰጥ በታሰበው የመውጫ ፈተና ዙሪያ ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስሙ የተሰራጨው መረጃ ህብረቱን የማይወክል መሆኑን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል።
በዚህ ዓመት እንዲሰጥ በተወሰነው የመውጫ ፈተና ላይ ተማሪዎች በሚያነሷቸው ስጋቶችና ቅሬታዎች ላይ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ከሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይቶች መደረጋቸውን ወደፊትም እንደሚደረጉ ህብረቱ ገልጿል።
በውይይቶቹ የተነሱ ሀሳቦች ገሚሶቹ ምላሽ ያገኙ ሲሆን በቀጣይ የሚስተካከሉ መረጃዎችን የሚያሳወቅ መሆኑንም ህብረቱ ጠቁሟል።
ፈተናው የተማሪዎችን ብቃት የሚመዝንና የትምህርት ጥራት ሊያስጠብቅ በሚችልበት ሁኔታ ላይ አሁንም በጋራ እየሠራ መሆኑን ህብረቱ አስታውሷል።
ተማሪዎች በፈተናው እና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ሀሳብ በግቢያቸው ለሚገኙ የተማሪዎች ህብረት እያቀረቡ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አማካይነት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመወያየት ምላሽ የሚሰጥበት መሆኑንም ገልጿል።
በቅርቡ የተሰራጨው መረጃ ህብረቱን የማይወክልና ተቀባይነት የሌለው መሆኑን የገለጸው ህብረቱ፤ በህብረቱ የተጠራ ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል።
ተመራቂ ተማሪዎች በተቋሞቻቸውና በተማሪዎች ህብረት አማካይነት የሚሰጡ የድጋፍ ትምህርቶችን በመከታተል ለመውጫ ፈተናው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ህብረቱ ጥሪ አድርጓል።
ሐሰተኛና የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም ህብረቱ አሳስቧል።
More : @tikvahuniversity
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት የጠራው ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን አሳውቋል።
በዚህ ዓመት ሊሰጥ በታሰበው የመውጫ ፈተና ዙሪያ ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስሙ የተሰራጨው መረጃ ህብረቱን የማይወክል መሆኑን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል።
በዚህ ዓመት እንዲሰጥ በተወሰነው የመውጫ ፈተና ላይ ተማሪዎች በሚያነሷቸው ስጋቶችና ቅሬታዎች ላይ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ከሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይቶች መደረጋቸውን ወደፊትም እንደሚደረጉ ህብረቱ ገልጿል።
በውይይቶቹ የተነሱ ሀሳቦች ገሚሶቹ ምላሽ ያገኙ ሲሆን በቀጣይ የሚስተካከሉ መረጃዎችን የሚያሳወቅ መሆኑንም ህብረቱ ጠቁሟል።
ፈተናው የተማሪዎችን ብቃት የሚመዝንና የትምህርት ጥራት ሊያስጠብቅ በሚችልበት ሁኔታ ላይ አሁንም በጋራ እየሠራ መሆኑን ህብረቱ አስታውሷል።
ተማሪዎች በፈተናው እና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ሀሳብ በግቢያቸው ለሚገኙ የተማሪዎች ህብረት እያቀረቡ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አማካይነት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመወያየት ምላሽ የሚሰጥበት መሆኑንም ገልጿል።
በቅርቡ የተሰራጨው መረጃ ህብረቱን የማይወክልና ተቀባይነት የሌለው መሆኑን የገለጸው ህብረቱ፤ በህብረቱ የተጠራ ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል።
ተመራቂ ተማሪዎች በተቋሞቻቸውና በተማሪዎች ህብረት አማካይነት የሚሰጡ የድጋፍ ትምህርቶችን በመከታተል ለመውጫ ፈተናው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ህብረቱ ጥሪ አድርጓል።
ሐሰተኛና የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም ህብረቱ አሳስቧል።
More : @tikvahuniversity
#Commercepal
ለነጋዴዎች በሙሉ፣ አዲሱና ዘመናዊውን የኮሜርስፓል የመገበያያ መድረክ በመጠቀም ማንኛውንም ምርት በቀላሉ ይሽጡ።
ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፡
1. የግብር ከፋይ ምዝገባ ቁጥር (TIN Number)
2. ህጋዊ የንግድ ፈቃድ
3. ስልክ ቁጥር
በ 9491 የነፃ መስመር በመደወል ይመዝገቡ!
App Store: https://apps.apple.com/us/app/commercepal/id1669974212
Play Store: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.commercepal
Visit our website: https://commercepal.com/browse
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ //t.iss.one/CommercePal_et
ለነጋዴዎች በሙሉ፣ አዲሱና ዘመናዊውን የኮሜርስፓል የመገበያያ መድረክ በመጠቀም ማንኛውንም ምርት በቀላሉ ይሽጡ።
ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፡
1. የግብር ከፋይ ምዝገባ ቁጥር (TIN Number)
2. ህጋዊ የንግድ ፈቃድ
3. ስልክ ቁጥር
በ 9491 የነፃ መስመር በመደወል ይመዝገቡ!
App Store: https://apps.apple.com/us/app/commercepal/id1669974212
Play Store: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.commercepal
Visit our website: https://commercepal.com/browse
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ //t.iss.one/CommercePal_et
#HailemariamDessalegn
የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ " የታንዛኒያ ፕሬዜዳንታዊ የምግብ እና ግብርና/እርሻ አቅርቦት ምክር ቤት " አባል ተደርገው መሾማቸውን ገለፁ።
አቶ ኃይለማርያም የምክር ቤቱ አባል ተደርገው የተሾሙት በታንዛኒያ ፕሬዜዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ነው።
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው የምክር ቤቱ አባል ተደርገው በፕሬዜዳንት ሳሚያ ሱሉሁ በመሾማቸው ክብር እንደተሰማቸው ገልጸዋል።
ታንዛኒያ የግብርና ውጤቶቿን / ምርቷን ለገበያ ለማቅረብ እንዲሁም አነስተኛ እርሻን ለመለወጥ ያላት አቅም በጣም ትልቅ መሆኑን አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አመልክተዋል።
#ምክርቤቱ : ከጥር 25 እስከ 27 ቀን 2023 በሴኔጋል ዳካር የአፍሪካ የምግብ ምርትን አስመልክቶ በተካሄደው የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ (የዳካር 2ኛው የምግብ ጉባዔ - አፍሪካን መመገብ ፣ የምግብ ሉዓላዊነት እና ፅናት) ላይ የተላለፈውን የውሳኔ ሃሳብ ማለትም እያንዳንዱ ሀገር ግብርናን ለማስፋፋት እና የምግብ አቅርቦትን ለማሳደግ የስትራቴጂዎችን አፈፃፀም የሚመራ ም/ቤት ለማቋቋም በተወሰነ ውሳኔ መሰረት ነው ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ ፕሬዜዳንቷ ምክር ቤቱን ያቋቋሙት።
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በገዛ ፍቃዳቸው ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣናቸውን ከለቀቁ በኃላ ከባለቤታቸው የቀድሞ ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ተስፋዬ ጋር በመሰረቱት " ኃለማርያም እና ሮማን ፋውንዴሽን " እንዲሁም አፍሪካ ውስጥ በተለያዩ ተቋማት በመሪነት እየሰሩ ይገኛሉ።
@tikvahethiopia
የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ " የታንዛኒያ ፕሬዜዳንታዊ የምግብ እና ግብርና/እርሻ አቅርቦት ምክር ቤት " አባል ተደርገው መሾማቸውን ገለፁ።
አቶ ኃይለማርያም የምክር ቤቱ አባል ተደርገው የተሾሙት በታንዛኒያ ፕሬዜዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ነው።
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው የምክር ቤቱ አባል ተደርገው በፕሬዜዳንት ሳሚያ ሱሉሁ በመሾማቸው ክብር እንደተሰማቸው ገልጸዋል።
ታንዛኒያ የግብርና ውጤቶቿን / ምርቷን ለገበያ ለማቅረብ እንዲሁም አነስተኛ እርሻን ለመለወጥ ያላት አቅም በጣም ትልቅ መሆኑን አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አመልክተዋል።
#ምክርቤቱ : ከጥር 25 እስከ 27 ቀን 2023 በሴኔጋል ዳካር የአፍሪካ የምግብ ምርትን አስመልክቶ በተካሄደው የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ (የዳካር 2ኛው የምግብ ጉባዔ - አፍሪካን መመገብ ፣ የምግብ ሉዓላዊነት እና ፅናት) ላይ የተላለፈውን የውሳኔ ሃሳብ ማለትም እያንዳንዱ ሀገር ግብርናን ለማስፋፋት እና የምግብ አቅርቦትን ለማሳደግ የስትራቴጂዎችን አፈፃፀም የሚመራ ም/ቤት ለማቋቋም በተወሰነ ውሳኔ መሰረት ነው ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ ፕሬዜዳንቷ ምክር ቤቱን ያቋቋሙት።
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በገዛ ፍቃዳቸው ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣናቸውን ከለቀቁ በኃላ ከባለቤታቸው የቀድሞ ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ተስፋዬ ጋር በመሰረቱት " ኃለማርያም እና ሮማን ፋውንዴሽን " እንዲሁም አፍሪካ ውስጥ በተለያዩ ተቋማት በመሪነት እየሰሩ ይገኛሉ።
@tikvahethiopia
#አየር_ኃይል
በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ሙያ ፍላጎት ያላቸውን ወጣቶች ለማሰልጠን ዛሬ ይፋዊ ጥሪ አቅርቧል።
አየር ኃይል ፤ የአውሮፕላን ቴኪኒሻንነትን ሙያ መሰልጠን የሚፈልጉ ወጣቶች የወጡትን መስፈርቶች ሊያሟሉ እንደሚገባ አመልክቷል።
ከመስፈርቶቹ አንዱ የሆነው " የትምህርትና ሌሎች መመዘኛ " ሲሆን በዚህም በአየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ለመሰልጠን ፦
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆኑ በሂሳብ ፣ ፊዚክስ ፣ እንግሊዘኛ ትምህርቶች አማካኝ ውጤህ ከ50% እና ከዚያ በላይ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል።
- በ2013 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና አጠቃላይ ውጤት 300 እና ከዚያ በላይ ያላቸው መሆን አለባቸው።
- በ2014 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ደግሞ አጠቃላይ ውጤት 250 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ አለባቸው።
አየር ኃይል የሚያመለክቱ ወጣቶች የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱበትን ኦርጂናል ሰርተፊኬት እንዲሁም የኮሌጅ / ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከሆኑ ከሚማሩበት ተቋም የመጨረሻ አመት የውጤት ሪፖርት ማቅረብ አለባቸው ብሏል።
ከዚህ ባለፈ አየር ኃይል አካዳሚ የሚቀበላቸው በራሱ በአካዳሚው የሚሰጠውን #የመግቢያ_ፈተና ማለፍ የሚችሉትን እንደሆነ ገልጿል።
የምዝገባው ቦታዎች ከላይ ተያይዟል ።
የምዝገባው ቀን ከመጋቢት 18 ቀን 2015 ዓ/ም እስከ መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት እንደሆነ አየር ኃይል አሳውቋል።
(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ሙያ ፍላጎት ያላቸውን ወጣቶች ለማሰልጠን ዛሬ ይፋዊ ጥሪ አቅርቧል።
አየር ኃይል ፤ የአውሮፕላን ቴኪኒሻንነትን ሙያ መሰልጠን የሚፈልጉ ወጣቶች የወጡትን መስፈርቶች ሊያሟሉ እንደሚገባ አመልክቷል።
ከመስፈርቶቹ አንዱ የሆነው " የትምህርትና ሌሎች መመዘኛ " ሲሆን በዚህም በአየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ለመሰልጠን ፦
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆኑ በሂሳብ ፣ ፊዚክስ ፣ እንግሊዘኛ ትምህርቶች አማካኝ ውጤህ ከ50% እና ከዚያ በላይ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል።
- በ2013 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና አጠቃላይ ውጤት 300 እና ከዚያ በላይ ያላቸው መሆን አለባቸው።
- በ2014 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ደግሞ አጠቃላይ ውጤት 250 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ አለባቸው።
አየር ኃይል የሚያመለክቱ ወጣቶች የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱበትን ኦርጂናል ሰርተፊኬት እንዲሁም የኮሌጅ / ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከሆኑ ከሚማሩበት ተቋም የመጨረሻ አመት የውጤት ሪፖርት ማቅረብ አለባቸው ብሏል።
ከዚህ ባለፈ አየር ኃይል አካዳሚ የሚቀበላቸው በራሱ በአካዳሚው የሚሰጠውን #የመግቢያ_ፈተና ማለፍ የሚችሉትን እንደሆነ ገልጿል።
የምዝገባው ቦታዎች ከላይ ተያይዟል ።
የምዝገባው ቀን ከመጋቢት 18 ቀን 2015 ዓ/ም እስከ መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት እንደሆነ አየር ኃይል አሳውቋል።
(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#ExodusPhysiotherapy
በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች
~ ለአንገት፣ ለትክሻ፣ ለወገብ ህመም ፣ ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች፣ በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ!
የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን፤ ስልክ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች
~ ለአንገት፣ ለትክሻ፣ ለወገብ ህመም ፣ ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች፣ በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ!
የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን፤ ስልክ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
#ኬንያ
በጎረቤት ኬንያ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ አንድ ሰው ተገደለ።
የኬንያ ተቃዋሚው ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ የኑሮ መወደድን እና ፖለቲካዊ ጥያቄዎችን መሠረት አድርገው ደጋፊዎቻቸው ዛሬ ሰኞ መጋቢት 11/2015 ዓ.ም. ለተቃውሞ አደባባይ እንዲወጡ ጠርተው ነበር።
የኬንያ መንግሥት የተቃውሞ ሰልፉ ሕገወጥ እና ያልተፈቀደ ነው ቢልም፣ በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች ውስጥ በአንስተኛ ደረጃ ወደ ጎዳና የወጡ ተቃዋሚዎች ታይተዋል።
ፖሊስም ተቃዋሚዎችን ለመበተን ከፍተኛ ኃይል ያለው ውሃ እና አስለቃሽ ጋዝ የተጠቀመ ሲሆን፣ እስካሁን አንድ ሰው ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት መሞቱ ተዘግቧል።
የተቃዋሚ ፓርቲው መሪ ራይላ ኦዲንጋ ምንም እንኳን ፍርድ ቤት ክሳቸውን ውድቅ ቢያደርገውም ባለፈው ዓመት ነሐሴ የተካሄደው ምርጫ ተሰርቋል የሚለውን ክሳቸውን አሁንም እያቀረቡ ነው።
በተጨማሪም ሥልጣን ከያዘ ስድስት ወራትን ያስቆጠረው የዊሊያም ሩቶ መንግሥት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ያለውን የኑሮ ውድነት መፍትሄ ሊያበጅለት አልቻለም በማለት ደጋፊዎቻቸውን ለአደባባይ ተቃውሞ ጠርተዋል።
በተለይ ኦዲንጋ ከፍተኛ ደጋፊ ባላቸው የናይሮቢ የድሆች መኖሪያ በሆነው ኪቤራ አካባቢ ፖሊሶች ከተቃዋሚዎች ጋር ተጋጭተዋል።
በማዕከላዊ ናይሮቢ የሚገኙ የንግድ ተቋማትም የፀጥታ ችግሩን በመፍራት ዝግ ሆነው አስከ እኩለ ቀን ድረስ የቆዩ ሲሆን፣ ፖሊስ ለተቃውሞ የወጡ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጋዝ በትነዋል።
በማዕከላዊ የከተማዋ ክፍል ውስጥ በሚገኘው የኬንያታ ጎዳና ላይም አንዳንድ ተቃዋሚዎች በፖሊሶች ላይ ድንጋይ ሲወረውሩ መታየታቸውን #ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
በጎረቤት ኬንያ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ አንድ ሰው ተገደለ።
የኬንያ ተቃዋሚው ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ የኑሮ መወደድን እና ፖለቲካዊ ጥያቄዎችን መሠረት አድርገው ደጋፊዎቻቸው ዛሬ ሰኞ መጋቢት 11/2015 ዓ.ም. ለተቃውሞ አደባባይ እንዲወጡ ጠርተው ነበር።
የኬንያ መንግሥት የተቃውሞ ሰልፉ ሕገወጥ እና ያልተፈቀደ ነው ቢልም፣ በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች ውስጥ በአንስተኛ ደረጃ ወደ ጎዳና የወጡ ተቃዋሚዎች ታይተዋል።
ፖሊስም ተቃዋሚዎችን ለመበተን ከፍተኛ ኃይል ያለው ውሃ እና አስለቃሽ ጋዝ የተጠቀመ ሲሆን፣ እስካሁን አንድ ሰው ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት መሞቱ ተዘግቧል።
የተቃዋሚ ፓርቲው መሪ ራይላ ኦዲንጋ ምንም እንኳን ፍርድ ቤት ክሳቸውን ውድቅ ቢያደርገውም ባለፈው ዓመት ነሐሴ የተካሄደው ምርጫ ተሰርቋል የሚለውን ክሳቸውን አሁንም እያቀረቡ ነው።
በተጨማሪም ሥልጣን ከያዘ ስድስት ወራትን ያስቆጠረው የዊሊያም ሩቶ መንግሥት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ያለውን የኑሮ ውድነት መፍትሄ ሊያበጅለት አልቻለም በማለት ደጋፊዎቻቸውን ለአደባባይ ተቃውሞ ጠርተዋል።
በተለይ ኦዲንጋ ከፍተኛ ደጋፊ ባላቸው የናይሮቢ የድሆች መኖሪያ በሆነው ኪቤራ አካባቢ ፖሊሶች ከተቃዋሚዎች ጋር ተጋጭተዋል።
በማዕከላዊ ናይሮቢ የሚገኙ የንግድ ተቋማትም የፀጥታ ችግሩን በመፍራት ዝግ ሆነው አስከ እኩለ ቀን ድረስ የቆዩ ሲሆን፣ ፖሊስ ለተቃውሞ የወጡ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጋዝ በትነዋል።
በማዕከላዊ የከተማዋ ክፍል ውስጥ በሚገኘው የኬንያታ ጎዳና ላይም አንዳንድ ተቃዋሚዎች በፖሊሶች ላይ ድንጋይ ሲወረውሩ መታየታቸውን #ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
" የተዘረፍነው ካሜራን ጨምሮ ሙሉ ንብረቶቻችንን ነው " - ጋዜጠኛ ሙልጌታ አንበርብር
ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ህጋዊ ፍቃድ አግኝቶ በኦንላይ ሚዲያ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው " ኢትዮ 251 " ሚዲያ ካሜራን ጨምሮ ሙሉ ንብረቶቹን እንደተዘረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
ሚዲያው ዘረፋው የተፈጸመው ትናንት ዕሁድ መጋቢት 10/2015 ዓ/ም መሆኑን ገልጿል።
የኢትዮ 251 ሚዲያ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር ለቲክቫህ በላከው መልዕክት " ዘረፋው ጠንካራ ጥበቃ ባለውና መሐል አራት ኪሎ ድንቅ ሥራ ኮምፕሌክስ ላይ በሚገኘው የድርጅቱ ስቱዲዮ ነው የተፈፀመው። " ብሏል።
በዘረፋው የድርጅቱ መገልገያ የነበሩ ፦
- አራት ዘመናዊ ካሜራዎች፣
- ኔክማይክ፣
- ዙመር እና ሌሎችም መገልገያ ቁሳቁሶች ተዘርፈው ተወስደዋል ሲል አመልክቷል።
ቁሳቁሶቹ ከ "ኢትዮ 251" በተጨማሪ፤ " አራት ኪሎ ሚዲያ " እና "ነገረ ወልቃይት "ን የመሳሰሉ ሚዲያዎች የሚገለገሉባቸው እንደነበረም ገልጿል።
" የፕሮዳክሽን እቃዎቹን ትናንት እሁድ ዕኩለ ቀን ድረስ ስንሰራባቸው ነበር " ያለው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ " የተዘረፉት ንብረቶች አጠቃላይ ዋጋ ከአንድ ነጥብ ሰባት ሚሊዮን (1,700,000) ብር በላይ የሚገመት ነው " ሲል አስረድቷል።
" የተከራየንበት ህንፃ ድንቅ ሥራ ኮምፕሌክስ ላይ ሁለት ባንኮችን ጨምሮ ሌሎች ታላላቅ ድርጅቶች ለዓመታት እየሠሩ ያለ ቢሆንም አንዳቸውም ሊዘረፋ ቀርቶ ሙከራ እንኳ ተደርጎባቸው እንደማያውቅ ባደረግነው ማጣራት አረጋግጠናል " ያለው ጋዜጠኛው " ስምንተኛ ፎቅ ድረስ በመውጣት የሚዲያ ተቋምን መዝረፍ የሕዝብ ድምፅ በሆኑ በሚዲያ ላይ የተቃጣ ጥቃት በመሆኑ፣ እንደ ቀላል የሚታይ ጉዳይ አይደለም " ብሏል።
@tikvahethiopia
ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ህጋዊ ፍቃድ አግኝቶ በኦንላይ ሚዲያ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው " ኢትዮ 251 " ሚዲያ ካሜራን ጨምሮ ሙሉ ንብረቶቹን እንደተዘረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
ሚዲያው ዘረፋው የተፈጸመው ትናንት ዕሁድ መጋቢት 10/2015 ዓ/ም መሆኑን ገልጿል።
የኢትዮ 251 ሚዲያ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር ለቲክቫህ በላከው መልዕክት " ዘረፋው ጠንካራ ጥበቃ ባለውና መሐል አራት ኪሎ ድንቅ ሥራ ኮምፕሌክስ ላይ በሚገኘው የድርጅቱ ስቱዲዮ ነው የተፈፀመው። " ብሏል።
በዘረፋው የድርጅቱ መገልገያ የነበሩ ፦
- አራት ዘመናዊ ካሜራዎች፣
- ኔክማይክ፣
- ዙመር እና ሌሎችም መገልገያ ቁሳቁሶች ተዘርፈው ተወስደዋል ሲል አመልክቷል።
ቁሳቁሶቹ ከ "ኢትዮ 251" በተጨማሪ፤ " አራት ኪሎ ሚዲያ " እና "ነገረ ወልቃይት "ን የመሳሰሉ ሚዲያዎች የሚገለገሉባቸው እንደነበረም ገልጿል።
" የፕሮዳክሽን እቃዎቹን ትናንት እሁድ ዕኩለ ቀን ድረስ ስንሰራባቸው ነበር " ያለው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ " የተዘረፉት ንብረቶች አጠቃላይ ዋጋ ከአንድ ነጥብ ሰባት ሚሊዮን (1,700,000) ብር በላይ የሚገመት ነው " ሲል አስረድቷል።
" የተከራየንበት ህንፃ ድንቅ ሥራ ኮምፕሌክስ ላይ ሁለት ባንኮችን ጨምሮ ሌሎች ታላላቅ ድርጅቶች ለዓመታት እየሠሩ ያለ ቢሆንም አንዳቸውም ሊዘረፋ ቀርቶ ሙከራ እንኳ ተደርጎባቸው እንደማያውቅ ባደረግነው ማጣራት አረጋግጠናል " ያለው ጋዜጠኛው " ስምንተኛ ፎቅ ድረስ በመውጣት የሚዲያ ተቋምን መዝረፍ የሕዝብ ድምፅ በሆኑ በሚዲያ ላይ የተቃጣ ጥቃት በመሆኑ፣ እንደ ቀላል የሚታይ ጉዳይ አይደለም " ብሏል።
@tikvahethiopia