TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአሁን ሰዓት በናይሮቢ እየተሰጠ ባለው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ወታደራዊ አመራሮች ባለፈው በደቡብ አፍሪካ፣ ለተፈረመው የሰላም ስምምነት ቁርጠኝነታቸውን ገልፀዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን ይጠብቁ። @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#BREAKING
በናይሮቢ ሳምንት ያህል የፈጀውን ውይይት ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ከፍተኛ የጦር አዛዦች #ጦርነቱን_ለማቆም የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በዘላቂነት ግጭት እንዲቆም ስምምነት መፈረማቸው ይታወሳል ዛሬ ወታደራዊ አመራሮቹ በናይሮቢ ስምምነቱን ለማስፈጸም የሚያችል ስነድ ተፈራርመዋል፡፡
ተጨማሪ መረጃ ይጠብቁ።
Video Credit : Ruud Elmendrop
@tikvahethiopia
በናይሮቢ ሳምንት ያህል የፈጀውን ውይይት ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ከፍተኛ የጦር አዛዦች #ጦርነቱን_ለማቆም የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በዘላቂነት ግጭት እንዲቆም ስምምነት መፈረማቸው ይታወሳል ዛሬ ወታደራዊ አመራሮቹ በናይሮቢ ስምምነቱን ለማስፈጸም የሚያችል ስነድ ተፈራርመዋል፡፡
ተጨማሪ መረጃ ይጠብቁ።
Video Credit : Ruud Elmendrop
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING በናይሮቢ ሳምንት ያህል የፈጀውን ውይይት ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ከፍተኛ የጦር አዛዦች #ጦርነቱን_ለማቆም የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በዘላቂነት ግጭት እንዲቆም ስምምነት መፈረማቸው ይታወሳል ዛሬ ወታደራዊ አመራሮቹ በናይሮቢ ስምምነቱን ለማስፈጸም የሚያችል ስነድ ተፈራርመዋል፡፡ ተጨማሪ መረጃ ይጠብቁ።…
#Update
የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች ለሰብአዊ ርዳታ " ያልተገደበ እንቅስቃሴን ለማመቻቸት " መስማማታቸውን ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች ለሰብአዊ ርዳታ " ያልተገደበ እንቅስቃሴን ለማመቻቸት " መስማማታቸውን ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
በሰላም ስምምነቱ መሠረት የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ የሚፈቱበት ዝርዝር ዕቅድ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አዛዥና የሕወሐት ታጣቂዎች አዛዥ በናይሮቢ መክረዋል።
በሰላም ስምምነቱ በተያዘው የጊዜ ገደብ ትጥቅ የሚፈታበትንና መከላከያ ወደ መቐለ የሚገባበትን ዕቅድ ላይም #ተስማምተዋል። ዕቅዱም በቀጣይ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለዕቅዱ ተግባራዊነት የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በስምምነቱ መሠረት የሚጠበቅባቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መንግሥት ማሳሰቡን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ከናይሮቢው ስምምነት በኃላ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
በሰላም ስምምነቱ መሠረት የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ የሚፈቱበት ዝርዝር ዕቅድ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አዛዥና የሕወሐት ታጣቂዎች አዛዥ በናይሮቢ መክረዋል።
በሰላም ስምምነቱ በተያዘው የጊዜ ገደብ ትጥቅ የሚፈታበትንና መከላከያ ወደ መቐለ የሚገባበትን ዕቅድ ላይም #ተስማምተዋል። ዕቅዱም በቀጣይ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለዕቅዱ ተግባራዊነት የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በስምምነቱ መሠረት የሚጠበቅባቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መንግሥት ማሳሰቡን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ከናይሮቢው ስምምነት በኃላ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በሰላም ስምምነቱ መሠረት የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ የሚፈቱበት ዝርዝር ዕቅድ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አዛዥና የሕወሐት ታጣቂዎች አዛዥ በናይሮቢ መክረዋል። በሰላም ስምምነቱ በተያዘው የጊዜ ገደብ ትጥቅ የሚፈታበትንና መከላከያ ወደ መቐለ የሚገባበትን ዕቅድ ላይም #ተስማምተዋል። ዕቅዱም በቀጣይ ተግባራዊ ይደረጋል። ለዕቅዱ ተግባራዊነት የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በስምምነቱ መሠረት…
#Update
የአፍሪካ ህብረት (AU) የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ የዛሬው ስምምነት ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት፣ የሰላማዊ ሰዎችን ደኅንነት መጠበቅ፣ የትጥቅ መፍታትን እና ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ጉልህ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
የአፍሪካ ህብረት (AU) የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ የዛሬው ስምምነት ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት፣ የሰላማዊ ሰዎችን ደኅንነት መጠበቅ፣ የትጥቅ መፍታትን እና ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ጉልህ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአፍሪካ ህብረት (AU) የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ የዛሬው ስምምነት ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት፣ የሰላማዊ ሰዎችን ደኅንነት መጠበቅ፣ የትጥቅ መፍታትን እና ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ጉልህ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። @tikvahethiopia
#Africa
አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፦
" ዛሬ የተፈረመው ስምምነት #የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን ይፈታሉ የሚለውን እሳቤ እንዲጸና ያደረገ ነው ። "
#ENA
@tikvahethiopia
አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፦
" ዛሬ የተፈረመው ስምምነት #የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን ይፈታሉ የሚለውን እሳቤ እንዲጸና ያደረገ ነው ። "
#ENA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Africa አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፦ " ዛሬ የተፈረመው ስምምነት #የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን ይፈታሉ የሚለውን እሳቤ እንዲጸና ያደረገ ነው ። " #ENA @tikvahethiopia
#Update
ዛሬ በናይሮቢ #በተፈረመው_ስምምነት መሰረት ፤ በሚቀጥሉት 7 ቀናት ወታደራዊ ሀላፊዎቹ ለወታደሮቻቸው ኦረንቴሽን እንደሚሰጡና ከዛም የፌደራል ባለስልጣናት በትግራይ ኃላፊነታቸውን እንደሚረከቡ ይገልፃል።
የከባድ መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትም በትግራይ ክልል ያሉ የውጭ ኃይሎች እና ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ ያሉ ኃይሎች ከክልሉ መውጣት ጋር በአንድ ግዜ እንደሚፈፀም ይገልጻል።
የቀላል መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትን ለማሳለጥ ከሁለቱም ወገን የተውጣጣ ኮሚቴ እንደሚቋቋምም የስምምነት ሰነዱ ላይ ሰፍሯል።
(Credit : ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikvahethiopia
ዛሬ በናይሮቢ #በተፈረመው_ስምምነት መሰረት ፤ በሚቀጥሉት 7 ቀናት ወታደራዊ ሀላፊዎቹ ለወታደሮቻቸው ኦረንቴሽን እንደሚሰጡና ከዛም የፌደራል ባለስልጣናት በትግራይ ኃላፊነታቸውን እንደሚረከቡ ይገልፃል።
የከባድ መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትም በትግራይ ክልል ያሉ የውጭ ኃይሎች እና ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ ያሉ ኃይሎች ከክልሉ መውጣት ጋር በአንድ ግዜ እንደሚፈፀም ይገልጻል።
የቀላል መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትን ለማሳለጥ ከሁለቱም ወገን የተውጣጣ ኮሚቴ እንደሚቋቋምም የስምምነት ሰነዱ ላይ ሰፍሯል።
(Credit : ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Peace
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ምን አሉ ?
የፕሪቶሪያ ስምምነትና የዛሬው ናይሮቢ ስምምነት ተፈፃሚ እንዲሆን ለማድረግ በሙሉ ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።
ጀነራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ?
የዛሬው ስምምነት በትግራይ ውስጥ በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ስቃይ ያስወግዳል የሚል ተስፋ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ኡሁሩ ኬንያታ ምን አሉ ?
ኡሁሩ ኬንያታ በዛሬው መግለጫ ስምምነቱ በጦር ወንጀሎች ላይ " ተጠያቂነትን " ያጠቃልል እንደሆነ ለተጠየቀ ጥያቄ ምላሽ ሰጥተው ነበር።
ኡሁሩ ኬንያታ ይህ " የመሳሪያ ድምፅ ፀጥ ሲል እና አስከፊው የሰብአዊ ሁኔታ ሲስተካከል " እንደሚመጣ ተናግረዋል።
" በሰላማዊ ሰዎች ላይ ግፍ የሚፈጽም አካል ላይ ከባድ ማዕቀብ ይጣልበታል " ብለዋል።
@tikvahethiopia
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ምን አሉ ?
የፕሪቶሪያ ስምምነትና የዛሬው ናይሮቢ ስምምነት ተፈፃሚ እንዲሆን ለማድረግ በሙሉ ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።
ጀነራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ?
የዛሬው ስምምነት በትግራይ ውስጥ በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ስቃይ ያስወግዳል የሚል ተስፋ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ኡሁሩ ኬንያታ ምን አሉ ?
ኡሁሩ ኬንያታ በዛሬው መግለጫ ስምምነቱ በጦር ወንጀሎች ላይ " ተጠያቂነትን " ያጠቃልል እንደሆነ ለተጠየቀ ጥያቄ ምላሽ ሰጥተው ነበር።
ኡሁሩ ኬንያታ ይህ " የመሳሪያ ድምፅ ፀጥ ሲል እና አስከፊው የሰብአዊ ሁኔታ ሲስተካከል " እንደሚመጣ ተናግረዋል።
" በሰላማዊ ሰዎች ላይ ግፍ የሚፈጽም አካል ላይ ከባድ ማዕቀብ ይጣልበታል " ብለዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Peace ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ምን አሉ ? የፕሪቶሪያ ስምምነትና የዛሬው ናይሮቢ ስምምነት ተፈፃሚ እንዲሆን ለማድረግ በሙሉ ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። ጀነራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ? የዛሬው ስምምነት በትግራይ ውስጥ በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ስቃይ ያስወግዳል የሚል ተስፋ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል። ኡሁሩ ኬንያታ ምን አሉ ? ኡሁሩ ኬንያታ በዛሬው መግለጫ ስምምነቱ በጦር…
#Update
በደቡብ አፍሪካ ፤ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የኢትዮጵያ መንግስትን ወልክለው ፊርማቸውን ያኖሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከዛሬው የናይሮቢው ስምምነት በኃላ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።
አምባሳደር ሬድዋን ፤ ከዛሬው የቀጠለ ውይይት (በወታደራዊ ኃላፊዎች መካከል) የዛሬ ወር ገደማ (mid-December) በትግራይ ክልል መዲና #መቐለ ላይ ሊደረግ እንደሚችል ጠቁመዋል።
ዋናውና የውይይቶቹ ፍፃሜ ደግሞ በፈረንጆቹ አዲስ አመት #አዲስ_አበባ ላይ ሊደረግ እንደሚችል ገልፀዋል።
የናይሮቢው ውይይት በተጀመረበት ዕለት ኡሁሩ ኬንያታ ፤ " በፕሪቶሪያ ጀመርን፣ መንገዳችን እየተጠጋ ፤ አሁን ናይሮቢ ነን ፣ በሚቀጥለው ጊዜ ስብሰባችን መቐለ እንደሚሆን ተስፋ አድርጋለሁ ፤ በመጨረሻም አዲስ አበባ ላይ አብረን እናከብራለን። ይህ ጸሎታችን ፣ ተስፋ የምናደርገው እና የምንፈልገው ነው። " ማለታቸው አይዘነጋም።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው ፤ የናይሮቢው ውይይት የተደረገው በፕሪቶርያ የተደረገውን ስምምነትን መሰረት አድርጎ መሆኑን ገልፀዋል።
ነገር ግን በዚህ ውይይት የውጭ ኃይሎች ጉዳይ " sticking point " እንደነበር እና ውይይቱ በዛ ሁኔታ የተካሄደ እንደነበር አስረድተዋል።
(አምባሳደር ሬድዋን እና አቶ ጌታቸው ቃላቸውን የሰጡት በዛው ኬንያ፣ ናይሮቢ ለሚገኘው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ነው )
@tikvahethiopia
በደቡብ አፍሪካ ፤ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የኢትዮጵያ መንግስትን ወልክለው ፊርማቸውን ያኖሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከዛሬው የናይሮቢው ስምምነት በኃላ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።
አምባሳደር ሬድዋን ፤ ከዛሬው የቀጠለ ውይይት (በወታደራዊ ኃላፊዎች መካከል) የዛሬ ወር ገደማ (mid-December) በትግራይ ክልል መዲና #መቐለ ላይ ሊደረግ እንደሚችል ጠቁመዋል።
ዋናውና የውይይቶቹ ፍፃሜ ደግሞ በፈረንጆቹ አዲስ አመት #አዲስ_አበባ ላይ ሊደረግ እንደሚችል ገልፀዋል።
የናይሮቢው ውይይት በተጀመረበት ዕለት ኡሁሩ ኬንያታ ፤ " በፕሪቶሪያ ጀመርን፣ መንገዳችን እየተጠጋ ፤ አሁን ናይሮቢ ነን ፣ በሚቀጥለው ጊዜ ስብሰባችን መቐለ እንደሚሆን ተስፋ አድርጋለሁ ፤ በመጨረሻም አዲስ አበባ ላይ አብረን እናከብራለን። ይህ ጸሎታችን ፣ ተስፋ የምናደርገው እና የምንፈልገው ነው። " ማለታቸው አይዘነጋም።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው ፤ የናይሮቢው ውይይት የተደረገው በፕሪቶርያ የተደረገውን ስምምነትን መሰረት አድርጎ መሆኑን ገልፀዋል።
ነገር ግን በዚህ ውይይት የውጭ ኃይሎች ጉዳይ " sticking point " እንደነበር እና ውይይቱ በዛ ሁኔታ የተካሄደ እንደነበር አስረድተዋል።
(አምባሳደር ሬድዋን እና አቶ ጌታቸው ቃላቸውን የሰጡት በዛው ኬንያ፣ ናይሮቢ ለሚገኘው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ነው )
@tikvahethiopia
#የፀጥታ_ጉዳይ
" የክልል እና የፌደራል የጸጥታ ሀይል እንዲገባልን አመልክተናል " - አቶ ውብሸት አበራ
ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ከሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ተኩስ እንደከፈቱ ተሰምቷል።
ለአል ዓይን ኒውስ የደራ ወረዳ፤ ጉንዶ መስቀል ከተማ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ፤ መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀው የኦነግ ሸኔ ቡድን ታጣቂዎች ወደ ከተማዋ ዘልቀው በመግባት ከባድ ጥቃት እያደረሱ ነው።
ነዋሪዎቹ በቅድሚያ ጥቃቱ በገጠር ቀበሌዎች ላይ መጀመሩን አመልክተው ማለዳ ሶስት ሰዓት ላይ ወደ ጉንዶመስቀል ከተማ በመግባት ተኩስ መክፈታቸውንና የመንግስት እና የግለሰብ ንብረቶችም እየተዘረፈ ነው ብለዋል።
በጉንዶ መስቀል ከተማ ዙሪያ ላይ ባሉት ቀበሌዎች የሚኖሩ ዜጎችም መኖሪያ ቤቶች በታጣቂዎቹ እየተቃጠለ እና ከብቶቻቸው እየተወሰዱባቸው እንደሆነ ነዋሪዎቹ አመልክተዋል። በስፍራው ላይ የመንግስት የጸጥታ መዋቅር እንደሌለም አክለዋል።
የደራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ውብሸት አበራ በሰጡት ቃል ፤ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ወደ ደራ ወረዳ ዋና ከተማ ጉንዶመስቀል መግባታቸውን ገልጸዋል።
" ታጣቂዎቹ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ በከተማዋ ባሉ ባንኮች፣ የመንግስት ተቋማት እና የግለሰቦችን ንብረት እየዘረፉ ነው " ያሉት አስተዳዳሪው የክልል እና የፌደራል የጸጥታ ሀይል እንዲገባላቸው ማመልከታቸውን ለአል አይን ኒውስ ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
" የክልል እና የፌደራል የጸጥታ ሀይል እንዲገባልን አመልክተናል " - አቶ ውብሸት አበራ
ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ከሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ተኩስ እንደከፈቱ ተሰምቷል።
ለአል ዓይን ኒውስ የደራ ወረዳ፤ ጉንዶ መስቀል ከተማ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ፤ መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀው የኦነግ ሸኔ ቡድን ታጣቂዎች ወደ ከተማዋ ዘልቀው በመግባት ከባድ ጥቃት እያደረሱ ነው።
ነዋሪዎቹ በቅድሚያ ጥቃቱ በገጠር ቀበሌዎች ላይ መጀመሩን አመልክተው ማለዳ ሶስት ሰዓት ላይ ወደ ጉንዶመስቀል ከተማ በመግባት ተኩስ መክፈታቸውንና የመንግስት እና የግለሰብ ንብረቶችም እየተዘረፈ ነው ብለዋል።
በጉንዶ መስቀል ከተማ ዙሪያ ላይ ባሉት ቀበሌዎች የሚኖሩ ዜጎችም መኖሪያ ቤቶች በታጣቂዎቹ እየተቃጠለ እና ከብቶቻቸው እየተወሰዱባቸው እንደሆነ ነዋሪዎቹ አመልክተዋል። በስፍራው ላይ የመንግስት የጸጥታ መዋቅር እንደሌለም አክለዋል።
የደራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ውብሸት አበራ በሰጡት ቃል ፤ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ወደ ደራ ወረዳ ዋና ከተማ ጉንዶመስቀል መግባታቸውን ገልጸዋል።
" ታጣቂዎቹ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ በከተማዋ ባሉ ባንኮች፣ የመንግስት ተቋማት እና የግለሰቦችን ንብረት እየዘረፉ ነው " ያሉት አስተዳዳሪው የክልል እና የፌደራል የጸጥታ ሀይል እንዲገባላቸው ማመልከታቸውን ለአል አይን ኒውስ ገልጸዋል።
@tikvahethiopia