#Peace
የአፍሪካ ኅብረት #የሰላም_ንግግሩን የሚመሩ አካላትን፤ ቀንና ስፍራን አሳውቆ የሰላም ውይይቱ እንዲጀመር ኦፊሴላዊ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።
ይኸው በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ የቀረበው ጥሪ እንደሚያሳየው፦
- የውይይት ቦታ 👉 ደቡብ አፍሪካ
- የውይይቱ ቀን 👉 ከፊታችን ጥቅምት 8/2022 ጀምሮ
- የሰላም ውይይቱ የሚመራው 👉 በቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንትና በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ
- የሰላም ሂደቱ ፓናሊስት ሆነው የሚያገለግሉ 👉 የቀድሞ የኬንያ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፉምዚሌ ምላምቦ ንጉካ ናቸው።
የአፍሪካ ኅብረት ግብዣውን ለኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት እንዲሁም ለህወሓት ነው ያቀረበው።
የአፍሪካ ህብረትን ግብዣ የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት #መቀበሉን በይፋ አሳውቋል። ነገር ግን የውይይቱን መሪዎች፣ ቀንና ቦታ በዝርዝር አልገለፀም።
መንግስት " የአፍሪካ ኅብረት ግብዣ መንግሥት ከዚህ በፊት ያቀረባቸውን አቋሞች የጠበቀ ሆኖ ተገኝቷል " ብሏል።
" ንግግሩ በአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ብቻ እንዲሆንና ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲደረግ መንግሥት አቋሙን ሲገልጥ መቆይቷል " ሲልም አስታውሷል።
" ግጭቱን ለመፍታት ሁሉንም ዓይነት የመፍትሔ ርምጃዎች ለመውሰድ ስንቀሳቀስ ቆያቻለው " ያለው የፌዴራል መንግስት " ይህንኑ አጠናክሬ እቀጥላለሁ " ብሏል።
እስካሁን ድረስ በህወሓት በኩል ለዚሁ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ንግግር ግብዣ ይፋዊ ምላሽ አልተሰጠም።
NB. ከላይ የተያያዘው በሙሳ ፋኪ የተፈረመው ደብዳቤ ለፌዴራል መንግስት እና ለህወሓት የተላከ መሆኑን ሮይተርስ ከዲፕሎማቲክ ምንጮች ማረጋገጡ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የአፍሪካ ኅብረት #የሰላም_ንግግሩን የሚመሩ አካላትን፤ ቀንና ስፍራን አሳውቆ የሰላም ውይይቱ እንዲጀመር ኦፊሴላዊ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።
ይኸው በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ የቀረበው ጥሪ እንደሚያሳየው፦
- የውይይት ቦታ 👉 ደቡብ አፍሪካ
- የውይይቱ ቀን 👉 ከፊታችን ጥቅምት 8/2022 ጀምሮ
- የሰላም ውይይቱ የሚመራው 👉 በቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንትና በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ
- የሰላም ሂደቱ ፓናሊስት ሆነው የሚያገለግሉ 👉 የቀድሞ የኬንያ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፉምዚሌ ምላምቦ ንጉካ ናቸው።
የአፍሪካ ኅብረት ግብዣውን ለኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት እንዲሁም ለህወሓት ነው ያቀረበው።
የአፍሪካ ህብረትን ግብዣ የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት #መቀበሉን በይፋ አሳውቋል። ነገር ግን የውይይቱን መሪዎች፣ ቀንና ቦታ በዝርዝር አልገለፀም።
መንግስት " የአፍሪካ ኅብረት ግብዣ መንግሥት ከዚህ በፊት ያቀረባቸውን አቋሞች የጠበቀ ሆኖ ተገኝቷል " ብሏል።
" ንግግሩ በአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ብቻ እንዲሆንና ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲደረግ መንግሥት አቋሙን ሲገልጥ መቆይቷል " ሲልም አስታውሷል።
" ግጭቱን ለመፍታት ሁሉንም ዓይነት የመፍትሔ ርምጃዎች ለመውሰድ ስንቀሳቀስ ቆያቻለው " ያለው የፌዴራል መንግስት " ይህንኑ አጠናክሬ እቀጥላለሁ " ብሏል።
እስካሁን ድረስ በህወሓት በኩል ለዚሁ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ንግግር ግብዣ ይፋዊ ምላሽ አልተሰጠም።
NB. ከላይ የተያያዘው በሙሳ ፋኪ የተፈረመው ደብዳቤ ለፌዴራል መንግስት እና ለህወሓት የተላከ መሆኑን ሮይተርስ ከዲፕሎማቲክ ምንጮች ማረጋገጡ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት
መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ለሚጀምረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መስከረም 26-28 ተጠቃለው በመግባት መስከረም 29 ስለፈተናውና ተያያዥ ጉዳዮች በየተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች ገለጻ የሚደረግበት ዕለት መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቆ ነበር።
ሆኖም የእስልምና እምነት ተከታዮች መስከረም 28 የመዉሊድ በዓል አክብረዉ መስከረም 29/2015 ዓም እሁድ ጠዋት መግባት እንዲችሉ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደላቸዉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
የፈተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ገለጻ /Orientation/ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እሁድ ከሰዓት በኋላ እንዲሰጥ የተደረገ ሲሆን የእምነቱ ተከታይ ተማሪዎችም ይህንን አውቀው በተጠቀሰዉ ሰዓት በመገኘት ገለጻ /Orientation/ እንዲከታተሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
@tikvahethiopia
መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ለሚጀምረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መስከረም 26-28 ተጠቃለው በመግባት መስከረም 29 ስለፈተናውና ተያያዥ ጉዳዮች በየተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች ገለጻ የሚደረግበት ዕለት መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቆ ነበር።
ሆኖም የእስልምና እምነት ተከታዮች መስከረም 28 የመዉሊድ በዓል አክብረዉ መስከረም 29/2015 ዓም እሁድ ጠዋት መግባት እንዲችሉ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደላቸዉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
የፈተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ገለጻ /Orientation/ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እሁድ ከሰዓት በኋላ እንዲሰጥ የተደረገ ሲሆን የእምነቱ ተከታይ ተማሪዎችም ይህንን አውቀው በተጠቀሰዉ ሰዓት በመገኘት ገለጻ /Orientation/ እንዲከታተሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
@tikvahethiopia
#የሀሳብ_ቅኝቶች (ልዩ የወጣቶች መድረክ)
ሀሰተኛ መረጃ እንዲሁም የጥላቻ ንግግርን ለመግታት በሚደረጉ ጥረቶች ላይ ትኩረት ያደረገ " የሀሳብ ቅኝቶች " የተሰኘ መድረክ የፊታችን መስከረም 30 እና ጥቅምት 1 በአዲስ አበባ " ሸራተን አዲስ ሆቴል " ተሰናድቷል።
በዚህ መድረክ የፖናል ውይይት ፣ የአንድ ሰው ተውኔት፣ የሙዚቃና ልዩ ልዩ የመዝናኛ ዝግጅቶች የተካተቱበት ሲሆን የተለያዩ ሀሳቦችም ተነስተው የሚመከርበት የወጣቶች ዝግጅት ነው።
በመድረኩ ላይ ይመለከተኛል ፣ ሀሳብ አለኝ ፣ ማወቅ እፈልጋለሁ ለሚሉ ወጣቶች ሁሉ የተመቻቸ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ከሚሰሩ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር ለመገናኘት ጥሩ አጋጣሚ ይፈጥርላቸዋል።
በዝግጅቱ መሳተፍ ለሚፈልጉ ወጣቶች የመመዝገቢያ አማራጭ በነገው ዕለት ይፋ ይሆናል።
@tikvahethiopia
ሀሰተኛ መረጃ እንዲሁም የጥላቻ ንግግርን ለመግታት በሚደረጉ ጥረቶች ላይ ትኩረት ያደረገ " የሀሳብ ቅኝቶች " የተሰኘ መድረክ የፊታችን መስከረም 30 እና ጥቅምት 1 በአዲስ አበባ " ሸራተን አዲስ ሆቴል " ተሰናድቷል።
በዚህ መድረክ የፖናል ውይይት ፣ የአንድ ሰው ተውኔት፣ የሙዚቃና ልዩ ልዩ የመዝናኛ ዝግጅቶች የተካተቱበት ሲሆን የተለያዩ ሀሳቦችም ተነስተው የሚመከርበት የወጣቶች ዝግጅት ነው።
በመድረኩ ላይ ይመለከተኛል ፣ ሀሳብ አለኝ ፣ ማወቅ እፈልጋለሁ ለሚሉ ወጣቶች ሁሉ የተመቻቸ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ከሚሰሩ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር ለመገናኘት ጥሩ አጋጣሚ ይፈጥርላቸዋል።
በዝግጅቱ መሳተፍ ለሚፈልጉ ወጣቶች የመመዝገቢያ አማራጭ በነገው ዕለት ይፋ ይሆናል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Peace የአፍሪካ ኅብረት #የሰላም_ንግግሩን የሚመሩ አካላትን፤ ቀንና ስፍራን አሳውቆ የሰላም ውይይቱ እንዲጀመር ኦፊሴላዊ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል። ይኸው በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ የቀረበው ጥሪ እንደሚያሳየው፦ - የውይይት ቦታ 👉 ደቡብ አፍሪካ - የውይይቱ ቀን 👉 ከፊታችን ጥቅምት 8/2022 ጀምሮ - የሰላም ውይይቱ የሚመራው 👉 በቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንትና በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ…
#Update
ህወሓት በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ዛሬ ምሽት አሳውቋል።
ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቆርጠኞች ነን ሲልም ገልጿል።
ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ለአፍሪካ ህብረት ሊቀንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት በፃፉት ደብደቤ ፤ ለሰላም ሂደቱ ይረዳል ያሉትን " ግጭት ማቆም " ዋናው የድርድሩ የአጀንዳው አካል ተደርጎ ስለመያዙ ጠይቀዋል።
" ተደራዳሪዎቻችን ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመላክ ዝግጁ ነን " ሲሉም አሳውቀዋል።
" ግብዣው ቀደም ብሎ ያልተማከርንበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ቢሰጠን " ሲሉ በፃፉት ደብዳቤ ጠይቀዋል።
እነዚህም ፦
- በሰላም ውይይቱ ተጨማሪ ተዋናይን እንደ ተሳታፊዎች፣ ታዛቢዎች ወይም ዋስትና ሰጪዎች የሚጋበዙ ይኖሩ እንደሆነ፤
- ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አይነት ሚናዎችን ሊሰጥ እንደታሰበ ፤
- ለተደራዳሪ ቡድኑ የሎጅስቲክስ ፤ #የጉዞ እና የደህንነት ዝግጅቶችን በተመለከተ እንዲብራራላቸው ዶ/ር ደብረፅዮን ለፋኪ በላኩት ደብዳቤ ጠይቀዋል።
ዛሬ ጥዋት የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት በደቡብ አፍሪካ የሚደረገውን የሰላም ንግግር ግብዣ መቀበሉን ማሳወቁ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
ህወሓት በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ዛሬ ምሽት አሳውቋል።
ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቆርጠኞች ነን ሲልም ገልጿል።
ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ለአፍሪካ ህብረት ሊቀንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት በፃፉት ደብደቤ ፤ ለሰላም ሂደቱ ይረዳል ያሉትን " ግጭት ማቆም " ዋናው የድርድሩ የአጀንዳው አካል ተደርጎ ስለመያዙ ጠይቀዋል።
" ተደራዳሪዎቻችን ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመላክ ዝግጁ ነን " ሲሉም አሳውቀዋል።
" ግብዣው ቀደም ብሎ ያልተማከርንበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ቢሰጠን " ሲሉ በፃፉት ደብዳቤ ጠይቀዋል።
እነዚህም ፦
- በሰላም ውይይቱ ተጨማሪ ተዋናይን እንደ ተሳታፊዎች፣ ታዛቢዎች ወይም ዋስትና ሰጪዎች የሚጋበዙ ይኖሩ እንደሆነ፤
- ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አይነት ሚናዎችን ሊሰጥ እንደታሰበ ፤
- ለተደራዳሪ ቡድኑ የሎጅስቲክስ ፤ #የጉዞ እና የደህንነት ዝግጅቶችን በተመለከተ እንዲብራራላቸው ዶ/ር ደብረፅዮን ለፋኪ በላኩት ደብዳቤ ጠይቀዋል።
ዛሬ ጥዋት የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት በደቡብ አፍሪካ የሚደረገውን የሰላም ንግግር ግብዣ መቀበሉን ማሳወቁ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
አሚና መሀመድ ኬንያ ናቸው።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሀመድ ኬንያ የሚገኙ ሲሆን ዛሬ ከኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ጋር በ " ስቴት ሀውስ " ተገናኝተው ተወያይተዋል።
ስቴት ሀውስ ፤ ፕሬዝዳንቱ እና ምክትል ዋና ፀሀፊዋ ፤ " ኬንያ እንደ ተፅእኖ ፈጣሪ ሀገር በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ሁኔታ ላይ ስላላት ጉልህ ሚና ተወያይተዋል " ሲል አሳውቋል።
በተጨማሪ የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢኮኖሚ እና በኑሮ ላይ እያሳደረ ስለለው ተፅእኖ እንዲሁም በቀጠናው ስላለው ድርቅና ረሃብ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በዚሁ ውይይት ወቅት ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ፤ ሀገራት አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የበኩሉን ሚና እንዲጫወት ጠይቀዋል።
@tikvahethiopia
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሀመድ ኬንያ የሚገኙ ሲሆን ዛሬ ከኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ጋር በ " ስቴት ሀውስ " ተገናኝተው ተወያይተዋል።
ስቴት ሀውስ ፤ ፕሬዝዳንቱ እና ምክትል ዋና ፀሀፊዋ ፤ " ኬንያ እንደ ተፅእኖ ፈጣሪ ሀገር በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ሁኔታ ላይ ስላላት ጉልህ ሚና ተወያይተዋል " ሲል አሳውቋል።
በተጨማሪ የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢኮኖሚ እና በኑሮ ላይ እያሳደረ ስለለው ተፅእኖ እንዲሁም በቀጠናው ስላለው ድርቅና ረሃብ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በዚሁ ውይይት ወቅት ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ፤ ሀገራት አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የበኩሉን ሚና እንዲጫወት ጠይቀዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አሚና መሀመድ ኬንያ ናቸው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሀመድ ኬንያ የሚገኙ ሲሆን ዛሬ ከኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ጋር በ " ስቴት ሀውስ " ተገናኝተው ተወያይተዋል። ስቴት ሀውስ ፤ ፕሬዝዳንቱ እና ምክትል ዋና ፀሀፊዋ ፤ " ኬንያ እንደ ተፅእኖ ፈጣሪ ሀገር በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ሁኔታ ላይ ስላላት ጉልህ ሚና ተወያይተዋል " ሲል አሳውቋል። በተጨማሪ…
በሌላ መረጃ ፦
ምንም እንኳን በኬንያ " ስቴት ሀውስ " ኦፊሴላዊ መረጃ ባያሰራጭም ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊየም ሩቶ በነገው ዕለት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ለመገኘት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተሰምቷል።
ℹ️ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ልዩ መርሃ ግብር ነገ ከአመሻሽ ጀምሮ እንደሚያካሂድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማወቅ የቻለ ሲሆን ከዚህ ቀደም ብሎ ነገ ጥዋት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
NB. ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ባለፉት ሳምንታት የሙከራ ኔትዎርክ አገልግሎቱን በአወዳይ፣ ጎንደር ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሐረማያ፣ ባሕር ዳር፣ አዳማ፣ ቢሾፍቱ፣ ሞጆ እና ደብረ ብርሃን ማስጀመሩ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
ምንም እንኳን በኬንያ " ስቴት ሀውስ " ኦፊሴላዊ መረጃ ባያሰራጭም ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊየም ሩቶ በነገው ዕለት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ለመገኘት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተሰምቷል።
ℹ️ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ልዩ መርሃ ግብር ነገ ከአመሻሽ ጀምሮ እንደሚያካሂድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማወቅ የቻለ ሲሆን ከዚህ ቀደም ብሎ ነገ ጥዋት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
NB. ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ባለፉት ሳምንታት የሙከራ ኔትዎርክ አገልግሎቱን በአወዳይ፣ ጎንደር ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሐረማያ፣ ባሕር ዳር፣ አዳማ፣ ቢሾፍቱ፣ ሞጆ እና ደብረ ብርሃን ማስጀመሩ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሌላ መረጃ ፦ ምንም እንኳን በኬንያ " ስቴት ሀውስ " ኦፊሴላዊ መረጃ ባያሰራጭም ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊየም ሩቶ በነገው ዕለት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ለመገኘት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተሰምቷል። ℹ️ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ልዩ መርሃ ግብር ነገ ከአመሻሽ ጀምሮ እንደሚያካሂድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ…
#Kenya #Ethiopia
የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የመጀመሪያ የአፍሪካ ሀገር ጉዟቸውን ወደ #ኢትዮጵያ እንደሚያደርጉ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል።
ነገ በአዲስ አበባ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚታደሙ የተነገረላቸው ሩቶ ፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ይመክራሉ።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ምርጫ ማሸነፋቸው በIEBC በተገለፀበት ዕለት ከዓለም ሀገራት መሪዎች ሁሉ በቅድሚያ የ " እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት ያስተላለፉላቸው መሪ እንደነበሩ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የመጀመሪያ የአፍሪካ ሀገር ጉዟቸውን ወደ #ኢትዮጵያ እንደሚያደርጉ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል።
ነገ በአዲስ አበባ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚታደሙ የተነገረላቸው ሩቶ ፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ይመክራሉ።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ምርጫ ማሸነፋቸው በIEBC በተገለፀበት ዕለት ከዓለም ሀገራት መሪዎች ሁሉ በቅድሚያ የ " እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት ያስተላለፉላቸው መሪ እንደነበሩ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
#ሼር
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት መስከረም 30 /2015 ከሚጀምረው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ጋር በተያያዘ የዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቨርሲቲ ካምፓሶች አድራሻ አሰራጭቷል ፤ ከላይ ይመልከቱ።
@tikvahethiopia
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት መስከረም 30 /2015 ከሚጀምረው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ጋር በተያያዘ የዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቨርሲቲ ካምፓሶች አድራሻ አሰራጭቷል ፤ ከላይ ይመልከቱ።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሌላ መረጃ ፦ ምንም እንኳን በኬንያ " ስቴት ሀውስ " ኦፊሴላዊ መረጃ ባያሰራጭም ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊየም ሩቶ በነገው ዕለት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ለመገኘት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተሰምቷል። ℹ️ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ልዩ መርሃ ግብር ነገ ከአመሻሽ ጀምሮ እንደሚያካሂድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ…
#Update
" ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ " ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫውን ተከታትለን የምንልክላችሁ ይሆናል።
በሌላ በኩል ፤ ሳፋሪኮም በአዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን ደንበኞች በአቅራቢያቸው ካሉ የሳፋሪኮም መለያ ከተለጠፈባቸው ሱቆች በመሄድ ሲም ካርድ መግዛትና አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ገልጿል።
@tikvahethiopia
" ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ " ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫውን ተከታትለን የምንልክላችሁ ይሆናል።
በሌላ በኩል ፤ ሳፋሪኮም በአዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን ደንበኞች በአቅራቢያቸው ካሉ የሳፋሪኮም መለያ ከተለጠፈባቸው ሱቆች በመሄድ ሲም ካርድ መግዛትና አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kenya #Ethiopia የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የመጀመሪያ የአፍሪካ ሀገር ጉዟቸውን ወደ #ኢትዮጵያ እንደሚያደርጉ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል። ነገ በአዲስ አበባ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚታደሙ የተነገረላቸው ሩቶ ፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ይመክራሉ። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ዶ/ር…
#Update
የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶክተር ዊሊያም ሩቶ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዜዳንቱ አዲስ አበባ ሲደርሱ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተቀብለዋቸዋል።
ሩቶ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚያደርጉ የተገለፀ ሲሆን ሁለቱ መሪዎች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል።
ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ፕሬዜዳንት ሆነው ከተመረጡ በኃላ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሀገር ጉዟቸውን ወደ #ኢትዮጵያ በማድረግ ነው ጀምረዋል።
ፎቶ ፦ ኢብኮ
@tikvahethiopia
የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶክተር ዊሊያም ሩቶ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዜዳንቱ አዲስ አበባ ሲደርሱ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተቀብለዋቸዋል።
ሩቶ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚያደርጉ የተገለፀ ሲሆን ሁለቱ መሪዎች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል።
ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ፕሬዜዳንት ሆነው ከተመረጡ በኃላ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሀገር ጉዟቸውን ወደ #ኢትዮጵያ በማድረግ ነው ጀምረዋል።
ፎቶ ፦ ኢብኮ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ " ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫውን ተከታትለን የምንልክላችሁ ይሆናል። በሌላ በኩል ፤ ሳፋሪኮም በአዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን ደንበኞች በአቅራቢያቸው ካሉ የሳፋሪኮም መለያ ከተለጠፈባቸው ሱቆች በመሄድ ሲም ካርድ መግዛትና አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ገልጿል። @tikvahethiopia
#Live
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ አገልግሎት መጀመሩን እየሰጠ በሚገኘው መግለጫ በይፋ አሳውቋል።
መግለጫውን በዙም መከታተል የሚቻል ሲሆን ጥያቄ / አስተያየት ያላችሁ ጥያቄያችሁን / አስተያየታችሁን በዙም #በቀጥታ ማቅረብ ትችላላችሁ።
ሊንክ ፦ https://safaricom-co-ke.zoom.us/webinar/register/WN_45w3LkggTpan9rlQJhO9dg
@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ አገልግሎት መጀመሩን እየሰጠ በሚገኘው መግለጫ በይፋ አሳውቋል።
መግለጫውን በዙም መከታተል የሚቻል ሲሆን ጥያቄ / አስተያየት ያላችሁ ጥያቄያችሁን / አስተያየታችሁን በዙም #በቀጥታ ማቅረብ ትችላላችሁ።
ሊንክ ፦ https://safaricom-co-ke.zoom.us/webinar/register/WN_45w3LkggTpan9rlQJhO9dg
@tikvahethiopia