TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቪድዮ ፦ በአሜሪካ ሀገር ቴክሳስ በምትሰኝ ግዛት በምትገኘው " አለን " ከተማ አንድ ታጣቂ በገበያ አዳራሽ ውስጥ በፈጸመው ጥቃት ስምንት (8) ሰዎችን በጥይት ገድሏል።

በታጣቂው ከተገደሉት ውስጥ #ሕጻናት ይገኙበታል።

ከተገደሉት በተጨማሪ ሰባት (7) ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው በሆስፒታል ህክምና እየደረገላቸው ሲሆን፣ ከመካከላቸው 3ቱ በጽኑ የተጎዱ ናቸው።

ታጣቂው በጅምላ ባገኘው ሰው ላይ በከፈተው ተኩስ ግድያውን የፈጸመ ሲሆን፣ በገበያ አዳራሹ ውስጥ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች ድጋፍ እንዲወጡ ተደርገዋል።

ታጣቂው እዚያው ጥቃቱን በፈጸመበት ስፍራ በፖሊሶች ተተኩሶበት የተገደለ ሲሆን፣ ጥቃቱን የፈጸመው ብቻውን እንደሆነ እንደሚታመን ቢቢሲ ዘግቧል።

እንደ Gun Violence Archive ድረገፅ መረጃ በአሜሪካ ሀገር ከጦር መሳሪያዎች ጋር በተያያዘ በየዓመቱ #አርባ_ሺህ (40,000) ሰዎች የሚሞቱ ሲሆን ይህ በመሳሪያዎች እራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎችን ያካታታል።

ቪድዮ ፦ Fox News

@tikvahethiopia