#Update
ሩሲያ በዩክሬን ጊዜያዊ የተኩስ አቁም አድርጋለች።
ያወጀችው ጊዜያዊ ተኩስ አቁም ለዜጎች ሰብዓዊ መተላለፊያ ለማመቻቸት ያለመ ነው ተብሏል።
በኬቭ ፣ ማሪፖል ፣ ካርኪቭ እና ሱሚ ከተሞች #ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግም ተገልጿል።
@tikvahethiopia
ሩሲያ በዩክሬን ጊዜያዊ የተኩስ አቁም አድርጋለች።
ያወጀችው ጊዜያዊ ተኩስ አቁም ለዜጎች ሰብዓዊ መተላለፊያ ለማመቻቸት ያለመ ነው ተብሏል።
በኬቭ ፣ ማሪፖል ፣ ካርኪቭ እና ሱሚ ከተሞች #ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግም ተገልጿል።
@tikvahethiopia
" እኛ የእናተ ባርያ ነን ? " - ጠ/ሚ ኢምራን ካሃን
ምዕራባውያን የአፍሪካ ሀገራትንና ሌሎችንም የዓለም ሀገራት ሩስያን እንዲያወግዙ ጥሪ እያቀረቡ ናቸው።
ከእነዚህ ሀገራት መካከል አንዷ ፓኪስታን ናት። በምዕራባውያኑ ፓኪስታን ሩስያን አውግዢ የሚል ጥያቄ ከቀናት በፊት ቀርቦላታል።
የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራትን ጨምሮ የ22 ዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች መሪዎች እኤአ መጋቢት 1 ፓኪስታን በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ሩሲያ በዩክሬን ላይ የምታደርገውን " ወረራ " የሚያወግዝ ውሳኔ ሀሳብ እንድትደግፍ በጋራ ድብዳቤ ፅፈው ነበር።
ፓኪስታን ግን በጉባኤው ገለልተኛ አቋም ይዛ ነበር የወጣችው።
ይህን ተከትሎ የፓኪስታን ጠ/ሚ ኢምራን ካን ሀገራቸው የሩስያን ድርጊት እንድታወግዝ ግፊት ለማድረግ የሞከሩትን የምዕራባውያን ልዑካንን አጥብቀው ተችተዋል።
ኢምራን ካሃን ፥ " ስለኛ ምንድነው የምታስቡት ? እኛ የእናተ ባርያ ነን ... አድርጉ ሁሉ የምትሉንን የምናደርግ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
አክለው " የአውሮፓ ህብረት አምባሳደሮችን መጠየቅ እፈልጋለሁ፤ ለህንድ እንዲህ አይነት ደብዳቤ ፅፋችኃል ? " ሲሉ ሌላ ጥያቄ አቅርበዋል።
ካሃን ህንድና ፓኪስታን ለሁለት ጊዜ ጦርነት በገቡበት በካሽሚር ጉዳይ የአውሮፓ ሀገራት ህንድ ያደረገችውን ድርጊት አልገሰፁም ሲሉም ኮንነዋል።
ጠቅለይ ሚኒስትሩ ፥ ፓኪስታን በአፍጋኒስታን የነበረውን የምእራቡ ህብረትን ኔቶ ስለደገፈች ተጎድታለች ፥ ከምስጋና ይልቅ ትችት ነው የገጠማት ብለዋል።
" ከሩሲያ ጋር ወዳጆች ነን፣ ከአሜሪካም ጋር ወዳጆች ነን፤ ከቻይና እና ከአውሮፓ ጋርም ወዳጆች ነን፤ በየትኛውም ካምፕ ውስጥ አይደለንም " ያሉት ኢምራን ካሃን ፓኪስታን ገለልተኛነቷን ይዛ ትቀጥላለች የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም ከሚሞክሩት ጋር ትሰራለች ብለዋል።
@tikvahethiopia
ምዕራባውያን የአፍሪካ ሀገራትንና ሌሎችንም የዓለም ሀገራት ሩስያን እንዲያወግዙ ጥሪ እያቀረቡ ናቸው።
ከእነዚህ ሀገራት መካከል አንዷ ፓኪስታን ናት። በምዕራባውያኑ ፓኪስታን ሩስያን አውግዢ የሚል ጥያቄ ከቀናት በፊት ቀርቦላታል።
የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራትን ጨምሮ የ22 ዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች መሪዎች እኤአ መጋቢት 1 ፓኪስታን በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ሩሲያ በዩክሬን ላይ የምታደርገውን " ወረራ " የሚያወግዝ ውሳኔ ሀሳብ እንድትደግፍ በጋራ ድብዳቤ ፅፈው ነበር።
ፓኪስታን ግን በጉባኤው ገለልተኛ አቋም ይዛ ነበር የወጣችው።
ይህን ተከትሎ የፓኪስታን ጠ/ሚ ኢምራን ካን ሀገራቸው የሩስያን ድርጊት እንድታወግዝ ግፊት ለማድረግ የሞከሩትን የምዕራባውያን ልዑካንን አጥብቀው ተችተዋል።
ኢምራን ካሃን ፥ " ስለኛ ምንድነው የምታስቡት ? እኛ የእናተ ባርያ ነን ... አድርጉ ሁሉ የምትሉንን የምናደርግ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
አክለው " የአውሮፓ ህብረት አምባሳደሮችን መጠየቅ እፈልጋለሁ፤ ለህንድ እንዲህ አይነት ደብዳቤ ፅፋችኃል ? " ሲሉ ሌላ ጥያቄ አቅርበዋል።
ካሃን ህንድና ፓኪስታን ለሁለት ጊዜ ጦርነት በገቡበት በካሽሚር ጉዳይ የአውሮፓ ሀገራት ህንድ ያደረገችውን ድርጊት አልገሰፁም ሲሉም ኮንነዋል።
ጠቅለይ ሚኒስትሩ ፥ ፓኪስታን በአፍጋኒስታን የነበረውን የምእራቡ ህብረትን ኔቶ ስለደገፈች ተጎድታለች ፥ ከምስጋና ይልቅ ትችት ነው የገጠማት ብለዋል።
" ከሩሲያ ጋር ወዳጆች ነን፣ ከአሜሪካም ጋር ወዳጆች ነን፤ ከቻይና እና ከአውሮፓ ጋርም ወዳጆች ነን፤ በየትኛውም ካምፕ ውስጥ አይደለንም " ያሉት ኢምራን ካሃን ፓኪስታን ገለልተኛነቷን ይዛ ትቀጥላለች የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም ከሚሞክሩት ጋር ትሰራለች ብለዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kombolcha📍 የኮምቦልቻ ከተማ ከሶስት ቀን ቡኃላ የምግብ ዘይት ስርጭት ይከናወናል ብሏል። የከተማው ንግድ ገበያ ልማት ጽ/ቤት ከ3 ቀን በኃላ በሁሉም ክፍለ ከተሞች እና ቀበሌዎች በተመጣጣኝ ዋጋ የዘይት ስርጭት እንደሚያደርግ አስታውቋል። ፅ/ቤቱ ከሚያደርገው የቁጥጥር ሥራ በተጨማሪ አቅርቦቱ ላይ ያለውን ችግር ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ስለሆነ ነዋሪዎች በተፈጠረው ያልተገባ የዋጋ ንረት አላስፈላጊ…
#Dessie📍
ደሴ ከተማን ሙሉ በሙሉ ማዳረስ የሚያስችል ከ605 ሺህ ሊትር በላይ ዘይት ከፌቤላ የዘይት ማምረቻ ኢንዱስትሪ ጋር በመተባበር በተያዘው ሳምንት ለነዋሪዎች እንደሚከፋፍል የከተማዋ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
የዘይት አቅርቦቱ በ 'ሸማች ማህበር' በኩል ይቀርባል የተባለ ሲሆን በገበያው ላይ የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለመከላከል የቁጥጥር ስራም እየተሰራ ነው ተብሏል።
በከተማዋ በሸማች ማህበራት በኩል የሚቀርበው የዘይት ዋጋ ፡-
1. ባለ 3 ሊትር 👉 290 ብር ከ06 ሳንቲም
2. ባለ 5 ሊትር 👉 474 ብር ከ40 ሳንቲም
3. ባለ10 ሊትር 👉 936 ብር ከ69 ሳንቲም
4. ባለ 20 ሊትር 👉 1 ሺህ 834 ብር ከ66 ሳንቲም
5. ባለ 25 ሊትር 👉 2 ሺህ 277 ብር ከ90 ሳንቲም መሆኑ ተገልጿል፡፡
@tikvahethiopia
ደሴ ከተማን ሙሉ በሙሉ ማዳረስ የሚያስችል ከ605 ሺህ ሊትር በላይ ዘይት ከፌቤላ የዘይት ማምረቻ ኢንዱስትሪ ጋር በመተባበር በተያዘው ሳምንት ለነዋሪዎች እንደሚከፋፍል የከተማዋ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
የዘይት አቅርቦቱ በ 'ሸማች ማህበር' በኩል ይቀርባል የተባለ ሲሆን በገበያው ላይ የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለመከላከል የቁጥጥር ስራም እየተሰራ ነው ተብሏል።
በከተማዋ በሸማች ማህበራት በኩል የሚቀርበው የዘይት ዋጋ ፡-
1. ባለ 3 ሊትር 👉 290 ብር ከ06 ሳንቲም
2. ባለ 5 ሊትር 👉 474 ብር ከ40 ሳንቲም
3. ባለ10 ሊትር 👉 936 ብር ከ69 ሳንቲም
4. ባለ 20 ሊትር 👉 1 ሺህ 834 ብር ከ66 ሳንቲም
5. ባለ 25 ሊትር 👉 2 ሺህ 277 ብር ከ90 ሳንቲም መሆኑ ተገልጿል፡፡
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ችሎት
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ የታሰሩበት 33 አባላቱ ዛሬ ፍርድ ቤት መቅረባቸውን አስታወቀ።
ከ33ቱ መካከል ሁለቱ ለለ14 ቀን ሲቀጠሩ ቀሪዎቹ 31 አባላቱ ለሀሙስ መጋቢት 1 ተቀጥረዋል ብሏል።
ተከሳሾቹ ዛሬ ፍ/ቤት የቀረቡት ለሁለት ቡድን ተከፍለው ሲሆን 31ዱ እስረኞች ከልደታ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ በሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው የቀረቡት።
ሁለቱ ደግሞ ጊዮርጊስ የሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው የቀረቡት።
ፖሊስ ለፍርድ ቤት ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት በአድዋ እና ካራማራ ክብረ በዓላት ብጥብጥ እና ሁከት ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ በመገኘታቸው ነው ብሏል።
ያንብቡ ፦ telegra.ph/Balderas-03-07
@tikvahethiopia
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ የታሰሩበት 33 አባላቱ ዛሬ ፍርድ ቤት መቅረባቸውን አስታወቀ።
ከ33ቱ መካከል ሁለቱ ለለ14 ቀን ሲቀጠሩ ቀሪዎቹ 31 አባላቱ ለሀሙስ መጋቢት 1 ተቀጥረዋል ብሏል።
ተከሳሾቹ ዛሬ ፍ/ቤት የቀረቡት ለሁለት ቡድን ተከፍለው ሲሆን 31ዱ እስረኞች ከልደታ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ በሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው የቀረቡት።
ሁለቱ ደግሞ ጊዮርጊስ የሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው የቀረቡት።
ፖሊስ ለፍርድ ቤት ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት በአድዋ እና ካራማራ ክብረ በዓላት ብጥብጥ እና ሁከት ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ በመገኘታቸው ነው ብሏል።
ያንብቡ ፦ telegra.ph/Balderas-03-07
@tikvahethiopia
#AddisAbaba📍
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ ክፍለ ከተማ በሶስት መጋዘን አለአግባብ የተከማቸ የምግብ ዘይት በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀ።
አስተዳዳደሩ በዛሬው እለት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ስሙ " ሙሉጌታ መናፈሻ " ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በህብረተሰቡ ጥቆማ በሶስት መጋዘን በርካታ መጠን ያለው የምግብ ዘይት ክምችት በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል
በቁጥጥር ስር የዋለው የምግብ ዘይት በፎቶ አስደግፎ ለህዝብ አሰራጭቷል።
የተያዘው የምግብ ዘይት በመጠን ምን ያህል እንደሆነ ባይገለፅም በርካታ መጠን ነው ያለው ተብሏል። ነገር ግን የምግብ ዘይቱን ማን እንዳከማቸው ፤ ድርጅት ከሆነም የትኛው ድርጅት ይህን ድርጊት እንደፈፀመ ፤ በሶስቱም መጋዘን የተገኘው ክምችት የአንድ ድርጅት ወይ ግለሰብ ነው አይደለም ስለሚለው የተብራራ ነገር የለም።
የምግብ ዘይቱ በቁጥጥር ስር የዋለው አጠቃላይ የኑሮ ውድነት እንዲባባስ ሰው ሰራሽ የዋጋ ውድነት በመፍጠርና ምርቶችን በመደበቅ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ህገወጥ ደላሎችንና ነጋዴዎችን ለመቆጣጠር በተቋቋመ ግብረ ሃይል ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሆኑ ተገልጿል።
አሁንም የአ/አ ነዋሪዎች ጥቆማ በመስጠት ርብርብ እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ ቀርቧል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ ክፍለ ከተማ በሶስት መጋዘን አለአግባብ የተከማቸ የምግብ ዘይት በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀ።
አስተዳዳደሩ በዛሬው እለት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ስሙ " ሙሉጌታ መናፈሻ " ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በህብረተሰቡ ጥቆማ በሶስት መጋዘን በርካታ መጠን ያለው የምግብ ዘይት ክምችት በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል
በቁጥጥር ስር የዋለው የምግብ ዘይት በፎቶ አስደግፎ ለህዝብ አሰራጭቷል።
የተያዘው የምግብ ዘይት በመጠን ምን ያህል እንደሆነ ባይገለፅም በርካታ መጠን ነው ያለው ተብሏል። ነገር ግን የምግብ ዘይቱን ማን እንዳከማቸው ፤ ድርጅት ከሆነም የትኛው ድርጅት ይህን ድርጊት እንደፈፀመ ፤ በሶስቱም መጋዘን የተገኘው ክምችት የአንድ ድርጅት ወይ ግለሰብ ነው አይደለም ስለሚለው የተብራራ ነገር የለም።
የምግብ ዘይቱ በቁጥጥር ስር የዋለው አጠቃላይ የኑሮ ውድነት እንዲባባስ ሰው ሰራሽ የዋጋ ውድነት በመፍጠርና ምርቶችን በመደበቅ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ህገወጥ ደላሎችንና ነጋዴዎችን ለመቆጣጠር በተቋቋመ ግብረ ሃይል ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሆኑ ተገልጿል።
አሁንም የአ/አ ነዋሪዎች ጥቆማ በመስጠት ርብርብ እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ ቀርቧል።
@tikvahethiopia
#Russia
ሩስያ በሀገሯ ፣ በኩባንያዎችና በህዝቧ ላይ " ወዳጃዊ ያልሆኑ " ድርጊቶችን የፈፀሙና እርምጃ የወሰዱ / ወዳጅ ያልሆኑ ሀገራትን እና ግዛቶችን ዝርዝር በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጋለች።
እነዚህም ፦
🇺🇦 ዩክሬን
🇺🇸 አሜሪካ
🇬🇧 ዩናይትድ ኪንግደም
🇪🇺 የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት
🇦🇺 አውስትራሊያ
🇨🇦 ካናዳ
🇮🇸 አይስላንድ
🇯🇵 ጃፓን
🇲🇨 ሞናኮ
🇲🇪 ሞንቴኔግሮ
🇳🇿 ኒውዚላንድ
🇳🇴 ኖርዌይ
🇹🇼 ታይዋን (ቻይና እንደ ተገንጣይ ግዛቷ የምትቆጥራት ሲሆን እሷ ግን ነፃ እና ሉዓላዊ ሀገር ነኝ በሚል እራሷን ችላ ነው የምትተዳደረው)
🇸🇲 ሳን ማሪኖ
🇸🇬 ሲንጋፖር
🇰🇷 ደቡብ ኮሪያ
🇨🇭 ስዊዘርላንድ
🇦🇱 አልባንያ
🇦🇩 አንዶራ
🇱🇮 ሌይቼንስቴይን
🇫🇲 ማክሮኔዢያ
🇲🇰 ሰሜን ሜቄዶንያ ናቸው።
ከላይ የተጠቀሱት ሀገራት እንዲሁም ግዛቶች በሩሲያ ላይ ማዕቀብ ጥለዋል ወይም በሚጣለው ማዕቀብ ላይ ተቀላቅለዋል የተባሉ ናቸው።
@tikvahethiopia
ሩስያ በሀገሯ ፣ በኩባንያዎችና በህዝቧ ላይ " ወዳጃዊ ያልሆኑ " ድርጊቶችን የፈፀሙና እርምጃ የወሰዱ / ወዳጅ ያልሆኑ ሀገራትን እና ግዛቶችን ዝርዝር በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጋለች።
እነዚህም ፦
🇺🇦 ዩክሬን
🇺🇸 አሜሪካ
🇬🇧 ዩናይትድ ኪንግደም
🇪🇺 የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት
🇦🇺 አውስትራሊያ
🇨🇦 ካናዳ
🇮🇸 አይስላንድ
🇯🇵 ጃፓን
🇲🇨 ሞናኮ
🇲🇪 ሞንቴኔግሮ
🇳🇿 ኒውዚላንድ
🇳🇴 ኖርዌይ
🇹🇼 ታይዋን (ቻይና እንደ ተገንጣይ ግዛቷ የምትቆጥራት ሲሆን እሷ ግን ነፃ እና ሉዓላዊ ሀገር ነኝ በሚል እራሷን ችላ ነው የምትተዳደረው)
🇸🇲 ሳን ማሪኖ
🇸🇬 ሲንጋፖር
🇰🇷 ደቡብ ኮሪያ
🇨🇭 ስዊዘርላንድ
🇦🇱 አልባንያ
🇦🇩 አንዶራ
🇱🇮 ሌይቼንስቴይን
🇫🇲 ማክሮኔዢያ
🇲🇰 ሰሜን ሜቄዶንያ ናቸው።
ከላይ የተጠቀሱት ሀገራት እንዲሁም ግዛቶች በሩሲያ ላይ ማዕቀብ ጥለዋል ወይም በሚጣለው ማዕቀብ ላይ ተቀላቅለዋል የተባሉ ናቸው።
@tikvahethiopia
#AmharaRegion
ድማሚት ፈንድቶ የ7 ህፃናት ህይወት ጠፋ።
በምዕራብ ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ግራር ውኃ በተባለ ቀበሌ ለመንገድ አገልግሎት የተቀመጠ ድማሚት ፈንድቶ የ7 ህጻናት ህይወት ማለፉን አሚኮ የወረዳውን ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
አደጋው የተከሰተው በቀን 27/2014 ዓ.ም ከምሽቱ 11:30 ገደማ ነው።
አደጋው የተከሰተው በሱር ኮንስትራክሽን አማካኝነት ሲሰራ በነበር የመንገድ ፕሮጀክት የቁሳቁስ ካምፕ ላይ ሲሆን በዚህ ውስጥ የአካባቢው ህጻናት ለጭዋታ ሲገቡና ሲወጡ እንደነበር ፓሊስ ገልጿል።
ፖሊስ ኅብረተሰቡ ህጻናት ወደ ካምፑ እንዳይገቡና ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
ድማሚት ፈንድቶ የ7 ህፃናት ህይወት ጠፋ።
በምዕራብ ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ግራር ውኃ በተባለ ቀበሌ ለመንገድ አገልግሎት የተቀመጠ ድማሚት ፈንድቶ የ7 ህጻናት ህይወት ማለፉን አሚኮ የወረዳውን ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
አደጋው የተከሰተው በቀን 27/2014 ዓ.ም ከምሽቱ 11:30 ገደማ ነው።
አደጋው የተከሰተው በሱር ኮንስትራክሽን አማካኝነት ሲሰራ በነበር የመንገድ ፕሮጀክት የቁሳቁስ ካምፕ ላይ ሲሆን በዚህ ውስጥ የአካባቢው ህጻናት ለጭዋታ ሲገቡና ሲወጡ እንደነበር ፓሊስ ገልጿል።
ፖሊስ ኅብረተሰቡ ህጻናት ወደ ካምፑ እንዳይገቡና ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
#Update
መንግስት 40 ሚሊየን ሊትር ዘይት በአጭር ጊዜ ወደ ሀገር ቤት አስገባለሁ አለ።
በዛሬው ዕለት የንግድ እና ቃጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ 40 ሚሊየን ሊትር ዘይት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ቤት ይገባል ብሏል።
ሚኒስቴሩ ከሰሞኑን በዘይት ምርቶች ላይ የተስተዋለው የዋጋ ጭማሪ የአለም አቀፍ ገበያው ላይ በመጣው ለውጥ ምክንያት ነው ብሏል።
በዚህም ለውጥ ምክንያት የተፈጠረውን የምርት እጥረት መነሻ በማድረግ በንግድ ማህበረሰብ ዘንድ የተፈጠረው ውዥንብር የዋጋ ጭማሪውን አባብሶታል ሲልም ገልጿል።
የአቅርቦት እጥረቱን ለማቃለል በአጭር ጊዜ መፍትሄ 40 ሚሊየን ሊትር ዘይት አስገባለሁኝ ብሏል።
በረዥም ጊዜ መፍትሄነት የምርት አቅርቦቱንና ፍላጎቱን ማጣጣም እንዲቻል የገበያ ሁኔታውን የሚያጠና ቡድን መዋቀሩን ሚኒስቴሩ መግለፁን ኤፍ .ቢ .ሲ . ዘግቧል
@tikvahethiopia
መንግስት 40 ሚሊየን ሊትር ዘይት በአጭር ጊዜ ወደ ሀገር ቤት አስገባለሁ አለ።
በዛሬው ዕለት የንግድ እና ቃጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ 40 ሚሊየን ሊትር ዘይት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ቤት ይገባል ብሏል።
ሚኒስቴሩ ከሰሞኑን በዘይት ምርቶች ላይ የተስተዋለው የዋጋ ጭማሪ የአለም አቀፍ ገበያው ላይ በመጣው ለውጥ ምክንያት ነው ብሏል።
በዚህም ለውጥ ምክንያት የተፈጠረውን የምርት እጥረት መነሻ በማድረግ በንግድ ማህበረሰብ ዘንድ የተፈጠረው ውዥንብር የዋጋ ጭማሪውን አባብሶታል ሲልም ገልጿል።
የአቅርቦት እጥረቱን ለማቃለል በአጭር ጊዜ መፍትሄ 40 ሚሊየን ሊትር ዘይት አስገባለሁኝ ብሏል።
በረዥም ጊዜ መፍትሄነት የምርት አቅርቦቱንና ፍላጎቱን ማጣጣም እንዲቻል የገበያ ሁኔታውን የሚያጠና ቡድን መዋቀሩን ሚኒስቴሩ መግለፁን ኤፍ .ቢ .ሲ . ዘግቧል
@tikvahethiopia
#Update
ሩስያ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች ከተሟሉ በዩክሬን የምታካሂደውን ወታደራዊ ኦፕሬሽን #ወዲያው እንደምታቆም አስታወቀች።
ሩስያ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች ፦
1ኛ. ወታደራዊ እርምጃ እንድታቆም።
2ኛ. ገለልተኛ አቋም እንድትይዝ ህገመንግስቷን እንድትቀይር (እንደ #NATO አይነት ጥምረት ውስጥ እንዳትገባ እንድታረጋግጥ)
3ኛ. ክሬሚያን እንደ ሩሲያ ግዛት እንድትቀበል።
4ኛ. የዶንቴስክ እና የሉሀንስክ ተገንጣይ ሪፐብሊኮችን እንደ ነፃ ሀገር እንድትቀበል የሚሉት ናቸው።
እነዚህ ከተሟሉ ሩስያ ዩክሬን ውስጥ ምታካሂደውን ወታደራዊ ዘመቻ ወዲያውኑ እንደምታቆም ገልፃለች።
የክሬምሊን ቃልአቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በስልክ ለሮይተርስ በሰጡት ቃል ፤ ዩክሬን ቅድመ ሁኔታዎቹን እንደምታውቅ እና ተፈፃሚ የሚሆኑ ከሆነ የወታደራዊ ዘመቻው ወዲያውኑ እንደሚቆም እንደተነገራት ገልፀዋል።
ከዩክሬን ወገን በኩል ወዲያው የተሰጠ ምላሽ የለም።
በሌላ በኩል ፥ የሩስያ እና ዩክሬን ሶስተኛው ዙር ድርድር ዛሬ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopia
ሩስያ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች ከተሟሉ በዩክሬን የምታካሂደውን ወታደራዊ ኦፕሬሽን #ወዲያው እንደምታቆም አስታወቀች።
ሩስያ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች ፦
1ኛ. ወታደራዊ እርምጃ እንድታቆም።
2ኛ. ገለልተኛ አቋም እንድትይዝ ህገመንግስቷን እንድትቀይር (እንደ #NATO አይነት ጥምረት ውስጥ እንዳትገባ እንድታረጋግጥ)
3ኛ. ክሬሚያን እንደ ሩሲያ ግዛት እንድትቀበል።
4ኛ. የዶንቴስክ እና የሉሀንስክ ተገንጣይ ሪፐብሊኮችን እንደ ነፃ ሀገር እንድትቀበል የሚሉት ናቸው።
እነዚህ ከተሟሉ ሩስያ ዩክሬን ውስጥ ምታካሂደውን ወታደራዊ ዘመቻ ወዲያውኑ እንደምታቆም ገልፃለች።
የክሬምሊን ቃልአቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በስልክ ለሮይተርስ በሰጡት ቃል ፤ ዩክሬን ቅድመ ሁኔታዎቹን እንደምታውቅ እና ተፈፃሚ የሚሆኑ ከሆነ የወታደራዊ ዘመቻው ወዲያውኑ እንደሚቆም እንደተነገራት ገልፀዋል።
ከዩክሬን ወገን በኩል ወዲያው የተሰጠ ምላሽ የለም።
በሌላ በኩል ፥ የሩስያ እና ዩክሬን ሶስተኛው ዙር ድርድር ዛሬ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba📍
በአዲስ አበባ ከተማ የተፈጠረውን የምግብ ዘይት እጥረት ለመፍታት 6.6 ሚሊዮን ሊትር ዘይት እየተሰራጨ መሆኑን እና ህብረተሰቡ ከነገ ጀምሮ በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት በኩል ማግኘት እንደሚችል ተገልጿል።
ይህንን የገለፀው የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ነው።
ለከተማው የተሰራጨው ምግብ ዘይት ከፊቤላ 3.1 ሚሊዮን ሊትር የሚጠጋ ፤ ከሸሙ ፋብሪካ 1.5 ሚሊዮን ሊትር የሚሆን ፤ ከንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን 2.4 ሚሊዮን ሊትር እንደሆነ ቢሮው ጠቁሟል።
በሌላ በኩል ቢሮው የዳቦ ጭማሪ ችግር ለመፍታት የሸገር ዳቦ ፋብሪካ በሙሉ አቅሙ እንዲያመርት እየተደረገ ነው ያለ ሲሆን በእያንዳንዱ ዳቦ ላይ 1 ብር ከ15 ሳንቲም ድጎማ በማድረግ በ2 ብር ከ10 ሳንቲ ለተጠቃሚ እየቀረበ መሆኑን አሳውቋል።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ የተፈጠረውን የምግብ ዘይት እጥረት ለመፍታት 6.6 ሚሊዮን ሊትር ዘይት እየተሰራጨ መሆኑን እና ህብረተሰቡ ከነገ ጀምሮ በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት በኩል ማግኘት እንደሚችል ተገልጿል።
ይህንን የገለፀው የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ነው።
ለከተማው የተሰራጨው ምግብ ዘይት ከፊቤላ 3.1 ሚሊዮን ሊትር የሚጠጋ ፤ ከሸሙ ፋብሪካ 1.5 ሚሊዮን ሊትር የሚሆን ፤ ከንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን 2.4 ሚሊዮን ሊትር እንደሆነ ቢሮው ጠቁሟል።
በሌላ በኩል ቢሮው የዳቦ ጭማሪ ችግር ለመፍታት የሸገር ዳቦ ፋብሪካ በሙሉ አቅሙ እንዲያመርት እየተደረገ ነው ያለ ሲሆን በእያንዳንዱ ዳቦ ላይ 1 ብር ከ15 ሳንቲም ድጎማ በማድረግ በ2 ብር ከ10 ሳንቲ ለተጠቃሚ እየቀረበ መሆኑን አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba📍
የምግብ ዘይት በ #መፀዳጃ_ቤት ውስጥ ተከማችቶ ተገኘ።
በአዲስ አበባ ከተማ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ በወረዳ 03 ያለአግባብ የተከማቸ የምግብ ዘይት በህዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል።
ክ/ከተማው በ11 ሱቆች ላይ ተደረገ ባለው ፍተሻ 442 ሊትር ዘይት በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን አሳውቋል።
ፍተሻ የተደረገው በወቅታዊ የዋጋ ንረት ምክንያት ካሉ 6 ቀጠናዎች በ3ቱ ቀጠናዎች ላይ ብቻ መሆኑ ተጠቁሟል።
ክ/ከተማው በቁጥጥር ስር የዋለው የምግብ ዘይት ባልተገባ ቦታ መፀዳጃ ቤት ውስጥ ተደብቆ መገኘቱን የገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ እንደዚህ አይነት ድርጊት የሚፈፅሙትን "ሌባን ሌባ " ሲል እንዲያጋልጥ ጥሪ አቀርቧል።
በአግባቡ በስራቸው ላይ የሚገኙ ነጋዴዎች አሁን በያዙት ልክ ዘይትን ወደ ፊት በማምጣት መሸጥ ይኖረባቸዋል የተባለ ሲሆን ህገወጥ ስራዎችን በሚሰሩ ነጋዴዎች ላይ የንግድ ፍቃድ መሰረዝን ጨምሮ ጠበቅ ያሉ እርምጃዎች ይወሰዳል ሲል ክፍለ ከተማው አስጠንቅቋል።
@tikvahethiopia
የምግብ ዘይት በ #መፀዳጃ_ቤት ውስጥ ተከማችቶ ተገኘ።
በአዲስ አበባ ከተማ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ በወረዳ 03 ያለአግባብ የተከማቸ የምግብ ዘይት በህዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል።
ክ/ከተማው በ11 ሱቆች ላይ ተደረገ ባለው ፍተሻ 442 ሊትር ዘይት በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን አሳውቋል።
ፍተሻ የተደረገው በወቅታዊ የዋጋ ንረት ምክንያት ካሉ 6 ቀጠናዎች በ3ቱ ቀጠናዎች ላይ ብቻ መሆኑ ተጠቁሟል።
ክ/ከተማው በቁጥጥር ስር የዋለው የምግብ ዘይት ባልተገባ ቦታ መፀዳጃ ቤት ውስጥ ተደብቆ መገኘቱን የገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ እንደዚህ አይነት ድርጊት የሚፈፅሙትን "ሌባን ሌባ " ሲል እንዲያጋልጥ ጥሪ አቀርቧል።
በአግባቡ በስራቸው ላይ የሚገኙ ነጋዴዎች አሁን በያዙት ልክ ዘይትን ወደ ፊት በማምጣት መሸጥ ይኖረባቸዋል የተባለ ሲሆን ህገወጥ ስራዎችን በሚሰሩ ነጋዴዎች ላይ የንግድ ፍቃድ መሰረዝን ጨምሮ ጠበቅ ያሉ እርምጃዎች ይወሰዳል ሲል ክፍለ ከተማው አስጠንቅቋል።
@tikvahethiopia