" በሀሰተኛ ገፆች እንዳትታለሉ " - ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በሳፋሪኮም ስም ተመሳስለው በተከፈቱ ሀሰተኛ ገፆች እንዳይታለሉ በላከልን መልዕክት አሳውቋል።
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ትክክለኛ የማህበራዊ ገጾች አድራሻ በትዊተር እና ፌስቡክ 𝐒𝐚𝐟𝐚𝐫𝐢𝐜𝐨𝐦𝐄𝐭 ሲሆን ሊንክዲን ላይ ደግሞ 𝐒𝐚𝐟𝐚𝐫𝐢𝐜𝐨𝐦 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐜𝐨𝐦𝐦𝐮𝐧𝐢𝐜𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚 𝐏𝐋𝐂 ነው የሚለው።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ነን ለሚሉ ሌሎች የሐሰት ገጾች መረጃዎች አያጋሩ ሲልም አሳውቋል።
@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በሳፋሪኮም ስም ተመሳስለው በተከፈቱ ሀሰተኛ ገፆች እንዳይታለሉ በላከልን መልዕክት አሳውቋል።
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ትክክለኛ የማህበራዊ ገጾች አድራሻ በትዊተር እና ፌስቡክ 𝐒𝐚𝐟𝐚𝐫𝐢𝐜𝐨𝐦𝐄𝐭 ሲሆን ሊንክዲን ላይ ደግሞ 𝐒𝐚𝐟𝐚𝐫𝐢𝐜𝐨𝐦 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐜𝐨𝐦𝐦𝐮𝐧𝐢𝐜𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚 𝐏𝐋𝐂 ነው የሚለው።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ነን ለሚሉ ሌሎች የሐሰት ገጾች መረጃዎች አያጋሩ ሲልም አሳውቋል።
@tikvahethiopia
" ... ጥፋቱን ካደረሱ መካከል በዩኒቨርሲቲው የተማሩ ተማሪዎች አሉበት " - የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት
የወሎ ዩኒቨርሲቲን በአጭር ጊዜ ወደ መማር ማስተማር ስራ ለማስገባት እንደሚሰራ ተገልጿል።
ህወሓት ባደረሰው ዝርፊና ውድመት ወሎ ዩኒቨርሲቲ 10 ቢሊዮን ብር የሚገመት ጉዳት እንደደረሰበት ተገልጿል።
የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 በሰጡት ቃል ፥ " ህወሓት ተሳቢ መኪና አቅርቦ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉትን ትልልቅ የቴክኖሎጂ ቁሳቁሶች ፣ ላብራቶሪ ቁሳቁሶች ፣ የወርክሾፕ፣ የኢንጂነሪንግ ፣ የቴክኖሎጂ ፣ የህክምናና ጤና ሳይንስ ፣ የተፈጥሮ ሳይንስ ፣ የግብርና ኮሌጅ ቁሳቁሶችን ነቅሎ ጭኖ ወስዷል " ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንት ዶ/ር መንገሻ ፥ " ይህ የጥፋት ኃይል ዩኒቨርሲቲው በሚሊዮን ሚቆጠር ገንዘብ አውጥቶ የገነባቸውንና በጣም የሚጠቅሙ ቁሳቁሶች ዘርፎ መውሰድ አይደለም የሚገርመው ፤ መውሰድ ያልቻለውን ኢንስታሌሽን ( የኤሌክትሪክ ፣ የኢንተርኔት ፣ የወርክሾፕ) በአጠቃላይ በጣጥሶ ከሱ ቁጥጥር ውጭ የሆኑትን / በቀላሉ ትራንስፖርት ማድረግ የማይችላቸውን ባሉበት እንዲወድሙና ተቋሙ ወደፊት እንዳይጠቀምበት አድርጎ ነው የሄደው " ብለዋል።
ወሎ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ እጅግ ዘመናዊ የሚባል የአይሲቲ መሰረተልማት ካሉት ተቋማት አንዱ ሲሆን ህወሓት ወደ ዳታ ማዕከል በመግባት የሚጠቅሙ ኮምፒዩተሮችና መነቀል የሚችሉትን ትልልቅ ባትሪዎችንና ቺፖችን ነቅሎ ወስዷል።
ኢንስታሌሽን ጋር የተገናኙ ትልልቅ ቁሳቁሶች ባሉበት ዳግም አገልግሎት እንዳይሰጡ አድርጎ ማውደሙን ዶ/ር መንገሻ ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በሁሉም ካምፓሶች ብዙ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በገንዘብ ሲተመን 10 ቢሊዮን ብር ይደርሳል።
ጥፋቱን ካደረሱ የህወሓት ቡድን አባላት መካከል በዛው በዩኒቨርሲቲው የተማሪ ተማሪዎች መኖራቸውን ፕሬዜዳንቱ ተናግረዋል።
ዶ/ር መንገሻ ፥ " በጣም የሚገርመው እኛው ተቋም የሰለጠኑ የተማሩ፣ የመጀመሪያ ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን የያዙ ተማሪዎች አሳብዶ እዚህ ቡድን ውስጥ አስገብቶ ይህን ተቋም በማፍረስ ሂደት ላይ አስተዋጽኦ እንደነበራቸው በአካባቢው የነበሩ እራሳቸው እኛ እዚህ ተምረናል እያሉ ለፀጥታ ኃይሎች ቃል በቃል እንደነገሯቸው የኛ የፀጥታ ኃይሎች ምስርክነታቸውን ነግረውናል።
በጣም ሰፋ ያለ ቡድን ጠመንጃ የያዘ ቡድን ፣ መፍቻ የያዘ ቡድን እንደገና ጀሌ ቡድን በወረፋ እየመጣ ትልልቅ ተሳቢ መኪናዎችን ይዞ እየገባ መካኒክ እሱ የሚፈታውን ወደተሳቢ መኪና የሚጭን ጀሌ ጉልበት ያለው ጫኝ ይሄ ሁሉ ተደራጅቶ የመጣ ኃይል መሆኑን ነው በአካባቢው የነበሩ የተቋሙ የፀጥታ አባላት የአይን ምስክር ሆነው የነገሩን " ብለዋል።
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ ቀደመው የመማር ማስተማር ስራ እንዲገባ ለማድረግ የመንግስት ፣ የክልል እና የአካባቢው አስተዳደር እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት እደሚተባበሩን እርግጠኛ ነን ያሉት ዶ/ር መንገሻ " በእኛ ግምት መማር ማስተማሩን በአጭር ጊዜ ውስጥ መልሰን እናስጀምራለን" ብለዋል።
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ከ30 ሺህ ላይ ተማሪዎችን ሲያስተምር የነበረ የ2ኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንት ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
የወሎ ዩኒቨርሲቲን በአጭር ጊዜ ወደ መማር ማስተማር ስራ ለማስገባት እንደሚሰራ ተገልጿል።
ህወሓት ባደረሰው ዝርፊና ውድመት ወሎ ዩኒቨርሲቲ 10 ቢሊዮን ብር የሚገመት ጉዳት እንደደረሰበት ተገልጿል።
የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 በሰጡት ቃል ፥ " ህወሓት ተሳቢ መኪና አቅርቦ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉትን ትልልቅ የቴክኖሎጂ ቁሳቁሶች ፣ ላብራቶሪ ቁሳቁሶች ፣ የወርክሾፕ፣ የኢንጂነሪንግ ፣ የቴክኖሎጂ ፣ የህክምናና ጤና ሳይንስ ፣ የተፈጥሮ ሳይንስ ፣ የግብርና ኮሌጅ ቁሳቁሶችን ነቅሎ ጭኖ ወስዷል " ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንት ዶ/ር መንገሻ ፥ " ይህ የጥፋት ኃይል ዩኒቨርሲቲው በሚሊዮን ሚቆጠር ገንዘብ አውጥቶ የገነባቸውንና በጣም የሚጠቅሙ ቁሳቁሶች ዘርፎ መውሰድ አይደለም የሚገርመው ፤ መውሰድ ያልቻለውን ኢንስታሌሽን ( የኤሌክትሪክ ፣ የኢንተርኔት ፣ የወርክሾፕ) በአጠቃላይ በጣጥሶ ከሱ ቁጥጥር ውጭ የሆኑትን / በቀላሉ ትራንስፖርት ማድረግ የማይችላቸውን ባሉበት እንዲወድሙና ተቋሙ ወደፊት እንዳይጠቀምበት አድርጎ ነው የሄደው " ብለዋል።
ወሎ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ እጅግ ዘመናዊ የሚባል የአይሲቲ መሰረተልማት ካሉት ተቋማት አንዱ ሲሆን ህወሓት ወደ ዳታ ማዕከል በመግባት የሚጠቅሙ ኮምፒዩተሮችና መነቀል የሚችሉትን ትልልቅ ባትሪዎችንና ቺፖችን ነቅሎ ወስዷል።
ኢንስታሌሽን ጋር የተገናኙ ትልልቅ ቁሳቁሶች ባሉበት ዳግም አገልግሎት እንዳይሰጡ አድርጎ ማውደሙን ዶ/ር መንገሻ ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በሁሉም ካምፓሶች ብዙ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በገንዘብ ሲተመን 10 ቢሊዮን ብር ይደርሳል።
ጥፋቱን ካደረሱ የህወሓት ቡድን አባላት መካከል በዛው በዩኒቨርሲቲው የተማሪ ተማሪዎች መኖራቸውን ፕሬዜዳንቱ ተናግረዋል።
ዶ/ር መንገሻ ፥ " በጣም የሚገርመው እኛው ተቋም የሰለጠኑ የተማሩ፣ የመጀመሪያ ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን የያዙ ተማሪዎች አሳብዶ እዚህ ቡድን ውስጥ አስገብቶ ይህን ተቋም በማፍረስ ሂደት ላይ አስተዋጽኦ እንደነበራቸው በአካባቢው የነበሩ እራሳቸው እኛ እዚህ ተምረናል እያሉ ለፀጥታ ኃይሎች ቃል በቃል እንደነገሯቸው የኛ የፀጥታ ኃይሎች ምስርክነታቸውን ነግረውናል።
በጣም ሰፋ ያለ ቡድን ጠመንጃ የያዘ ቡድን ፣ መፍቻ የያዘ ቡድን እንደገና ጀሌ ቡድን በወረፋ እየመጣ ትልልቅ ተሳቢ መኪናዎችን ይዞ እየገባ መካኒክ እሱ የሚፈታውን ወደተሳቢ መኪና የሚጭን ጀሌ ጉልበት ያለው ጫኝ ይሄ ሁሉ ተደራጅቶ የመጣ ኃይል መሆኑን ነው በአካባቢው የነበሩ የተቋሙ የፀጥታ አባላት የአይን ምስክር ሆነው የነገሩን " ብለዋል።
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ ቀደመው የመማር ማስተማር ስራ እንዲገባ ለማድረግ የመንግስት ፣ የክልል እና የአካባቢው አስተዳደር እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት እደሚተባበሩን እርግጠኛ ነን ያሉት ዶ/ር መንገሻ " በእኛ ግምት መማር ማስተማሩን በአጭር ጊዜ ውስጥ መልሰን እናስጀምራለን" ብለዋል።
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ከ30 ሺህ ላይ ተማሪዎችን ሲያስተምር የነበረ የ2ኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንት ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Niger ትላንትና ቅዳሜ በምዕራብ ኒጀር ከቡርኪነፋሶ በኩል በአጀብ የገቡ የፈረንሳይ ወታደሮች ከተቃዋሚዎች ጋር በፈጠሩት ግጭት ቢያንስ 2 ሰዎች ሲገደሉ 18 መቁሰላቸውን የኒጀር መንግስት አስታውቋል። የፈረንሳይ ጦር ሰራዊት ደግሞ ፥ ወታደራዊ አጀቡ በገጠመው ተቃውሞ የተነሳ ከቡርኪናፋሶ ለአንድ ሳምንት ያህል መውጣት አቅቶት እንደነበርና በዛው መቆየቱን ገልጿል። የፈረንሳይ ወታደሮች አሸባሪዎች የሚወስዱትን…
" እስከ ቀጣዩ ሰኔ ወር ድረስ በምእራብ አፍሪካ አገራት ያለውን አብዛኛውን ጦር ወደ ፓሪስ የመመለስ እቅድ ተይዟል " - ኢማኑኤል ማክሮን
የፈረንሳይ ጦር ከ9 ዓመት በኋላ ከምዕራብ አፍሪካ አካባቢ ሊወጣ ነው።
ፈረንሳይ በምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ አገራት አክራሪ ጽንፈኞች የሽብር ድርጊቶችን እየፈጸሙ በመሆኑ ይሄንን ድርጊት ለማስቆም በሚል ወደ አካባቢው ጦሯን አስገብታ ነበር።
ማሊ ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ኒጀር እና ቻድ ደግሞ ከአምስት ሺህ በላይ የፈረንሳይ ጦር የሰፈረባቸው ሀገራት ናቸው፡፡
ፈረንሳይ ጦሯን በምን ምክንያት እንደምታስወጣ በግልጽ አላሳወቀችም።
በማሊ በሶስት ካምፖች ሰፍሮ ያለው የፈረንሳይ ጦር አሁን ላይ ቱምቡክቱ ላይ ካለው ወታደራዊ ጣቢያ ውጪ ቀሪው ጓዙን በመጠቅለል ላይ ነው።
የፈረንሳይ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እስከ ቀጣዩ ሰኔ ወር ድረስ በምእራብ አፍሪካ አገራት ያለውን አብዛኛውን ጦር ወደ ፓሪስ የመመለስ እቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡
በሳህል አካባቢ ሰፍሮ የነበረው የፈረንሳይ ጦር አካባቢውን ለቆ ሲወጣ የአውሮፓ ህብረት አባል አገር ሌላ ጦር በአካባቢው ሊሰፍር እንደሚችል ፕሬዘዳንት ማክሮን ተናግረዋል።
የአውሮፓ አገራት ሰላም አስከባሪ ጦር ወደ ሳህል ቀጠና የሚሰማራው ከምዕራብ አፍሪካ አገራት ወደ አውሮፓ በመሻገር የሽብር ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ያለመ ነው ተብሏል፡፡
የማሊና ቡርኪናፋሶ ዜጎች በተለያዩ ከተሞች የፈርንሳይ ጦር አገራቸውን ለቀው እንዲወጡ የሚጠይቁ ሰላማዊ ሰልፎች መካሄዳቸው ይታወሳል።
ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ / ሲጂቲኤን
@tikvahethiopia
የፈረንሳይ ጦር ከ9 ዓመት በኋላ ከምዕራብ አፍሪካ አካባቢ ሊወጣ ነው።
ፈረንሳይ በምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ አገራት አክራሪ ጽንፈኞች የሽብር ድርጊቶችን እየፈጸሙ በመሆኑ ይሄንን ድርጊት ለማስቆም በሚል ወደ አካባቢው ጦሯን አስገብታ ነበር።
ማሊ ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ኒጀር እና ቻድ ደግሞ ከአምስት ሺህ በላይ የፈረንሳይ ጦር የሰፈረባቸው ሀገራት ናቸው፡፡
ፈረንሳይ ጦሯን በምን ምክንያት እንደምታስወጣ በግልጽ አላሳወቀችም።
በማሊ በሶስት ካምፖች ሰፍሮ ያለው የፈረንሳይ ጦር አሁን ላይ ቱምቡክቱ ላይ ካለው ወታደራዊ ጣቢያ ውጪ ቀሪው ጓዙን በመጠቅለል ላይ ነው።
የፈረንሳይ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እስከ ቀጣዩ ሰኔ ወር ድረስ በምእራብ አፍሪካ አገራት ያለውን አብዛኛውን ጦር ወደ ፓሪስ የመመለስ እቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡
በሳህል አካባቢ ሰፍሮ የነበረው የፈረንሳይ ጦር አካባቢውን ለቆ ሲወጣ የአውሮፓ ህብረት አባል አገር ሌላ ጦር በአካባቢው ሊሰፍር እንደሚችል ፕሬዘዳንት ማክሮን ተናግረዋል።
የአውሮፓ አገራት ሰላም አስከባሪ ጦር ወደ ሳህል ቀጠና የሚሰማራው ከምዕራብ አፍሪካ አገራት ወደ አውሮፓ በመሻገር የሽብር ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ያለመ ነው ተብሏል፡፡
የማሊና ቡርኪናፋሶ ዜጎች በተለያዩ ከተሞች የፈርንሳይ ጦር አገራቸውን ለቀው እንዲወጡ የሚጠይቁ ሰላማዊ ሰልፎች መካሄዳቸው ይታወሳል።
ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ / ሲጂቲኤን
@tikvahethiopia
#TechZone
ውፍረትን እና ቦርጭን መቀነስ ይፈልጋሉ? 0929088890
ያሉበት ድረስ ከነፃ ማድረሻ ጋር!
ሙሉ ከወገብ በላይ(ቦዲ) - 899ብር
የቦርጭ ብቻ -599 ብር
ሙሉ በሙሉ ቦርጭን በአጭር ጊዜ የሚያጠፋ እና
ማራኪ-ቁመና የሚያላብስ ።
ተጨማሪ : የቴሌግራም አድራሻችን ይጎብኙ
( ክልል ከተሞች እንገኛለን ) @አ.አ = ቦሌ መዳሃንያለም
ውፍረትን እና ቦርጭን መቀነስ ይፈልጋሉ? 0929088890
ያሉበት ድረስ ከነፃ ማድረሻ ጋር!
ሙሉ ከወገብ በላይ(ቦዲ) - 899ብር
የቦርጭ ብቻ -599 ብር
ሙሉ በሙሉ ቦርጭን በአጭር ጊዜ የሚያጠፋ እና
ማራኪ-ቁመና የሚያላብስ ።
ተጨማሪ : የቴሌግራም አድራሻችን ይጎብኙ
( ክልል ከተሞች እንገኛለን ) @አ.አ = ቦሌ መዳሃንያለም
#DStv
አስኳላ-ምዕራፍ 2
በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ሲትኮም
ረቡዕ ማታ 01፡30 በድጋሚ 03:30 እንዲሁም ቅዳሜ ማታ 01:30 እና እሁድ ከሰዓት 10:00 ሰዓት ላይ ይቀርባል፡፡
በአቦል ቲቪ ቻናል ቁጥር (146) ላይ ብቻ ያገኙታል!
https://t.iss.one/DStvEthiopiaOfficial
አስኳላ-ምዕራፍ 2
በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ሲትኮም
ረቡዕ ማታ 01፡30 በድጋሚ 03:30 እንዲሁም ቅዳሜ ማታ 01:30 እና እሁድ ከሰዓት 10:00 ሰዓት ላይ ይቀርባል፡፡
በአቦል ቲቪ ቻናል ቁጥር (146) ላይ ብቻ ያገኙታል!
https://t.iss.one/DStvEthiopiaOfficial
#እንድታውቁት
አትላስ አካባቢ የሚገኘው ነባር ድልድይ በጥገና ስራ ላይ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ከአትላስ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘውን እና 35 ሜትር ርዝመትና 10 ሜትር ከፍታ ያለውን ነባር ድልድይ የድጋፍ ግንብ እየጠገነ ይገኛል፡፡
ይህ ድልድይ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ በርካታ ዓመታትን አስቆጥሯል።
አንዳንድ ኃላፊነት የጎደላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ወደ ወንዙ በሚለቁት ከፍተኛ መጠን ያለው ደረቅ ቆሻሻ ሳቢያ የወንዙ ተፈጥሯዊ የውሃ ፍሰት እየተስተጓጎለ በመምጣቱ በክረምት ወራት የወንዙ ውሃ ሲጨምር የድልድዩን ተሸካሚ ምሰሶ የሚያቅፈው የድጋፍ ግንብ እንዲቦረቦር ምክንያት እንደሆነ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ገልጿል።
አሁን ላይ ባለስልጣን መ/ቤቱ የድጋፍ ግንብ ጥገና ሥራውን ለማከናወን ያስችለው ዘንድ ከድልድዩ ስር የተከማቸውን ከፍተኛ መጠን ያለውን ደረቅ ቆሻሻ የማንሳት ስራ እያከናወነ መሆኑን አመልክቷል።
መንገዱ ከሚያስተናግደው ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት አንፃር አጭር ጊዜ ውስጥ የጥገና ስራውን ሙሉ ለሙሉ የሚያጠናቀቅ ይሆናል ብሏል።
የጥገና ስራው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከአትላስ ወደ ኡራኤል የሚጓዙ አሽከርካሪዎች በስፍራው የተቀመጡ ምልክቶችን በማስተዋል ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ እንዲያሽከረክሩ ማሳስቢያ ተላልፏል።
የአካባቢው ማህበረሰብ የጥገና ስራው ከተጠናቀቀ በኋላ ድልድዩ ስር ቆሻሻ ባለመድፋት የጋራ የሆነውን የመንገድ ሀብት በጋራ እንዲጠብቅ መልዕክት ተላልፏል።
@tikvahethiopia
አትላስ አካባቢ የሚገኘው ነባር ድልድይ በጥገና ስራ ላይ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ከአትላስ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘውን እና 35 ሜትር ርዝመትና 10 ሜትር ከፍታ ያለውን ነባር ድልድይ የድጋፍ ግንብ እየጠገነ ይገኛል፡፡
ይህ ድልድይ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ በርካታ ዓመታትን አስቆጥሯል።
አንዳንድ ኃላፊነት የጎደላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ወደ ወንዙ በሚለቁት ከፍተኛ መጠን ያለው ደረቅ ቆሻሻ ሳቢያ የወንዙ ተፈጥሯዊ የውሃ ፍሰት እየተስተጓጎለ በመምጣቱ በክረምት ወራት የወንዙ ውሃ ሲጨምር የድልድዩን ተሸካሚ ምሰሶ የሚያቅፈው የድጋፍ ግንብ እንዲቦረቦር ምክንያት እንደሆነ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ገልጿል።
አሁን ላይ ባለስልጣን መ/ቤቱ የድጋፍ ግንብ ጥገና ሥራውን ለማከናወን ያስችለው ዘንድ ከድልድዩ ስር የተከማቸውን ከፍተኛ መጠን ያለውን ደረቅ ቆሻሻ የማንሳት ስራ እያከናወነ መሆኑን አመልክቷል።
መንገዱ ከሚያስተናግደው ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት አንፃር አጭር ጊዜ ውስጥ የጥገና ስራውን ሙሉ ለሙሉ የሚያጠናቀቅ ይሆናል ብሏል።
የጥገና ስራው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከአትላስ ወደ ኡራኤል የሚጓዙ አሽከርካሪዎች በስፍራው የተቀመጡ ምልክቶችን በማስተዋል ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ እንዲያሽከረክሩ ማሳስቢያ ተላልፏል።
የአካባቢው ማህበረሰብ የጥገና ስራው ከተጠናቀቀ በኋላ ድልድዩ ስር ቆሻሻ ባለመድፋት የጋራ የሆነውን የመንገድ ሀብት በጋራ እንዲጠብቅ መልዕክት ተላልፏል።
@tikvahethiopia
#Update
በሀርቡ ከተማ ተቋርጦ የነበረውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተመልሶ ተገናኝቷል።
በሀርቡ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የተመለሰው ዛሬ ታህሳስ 4 ቀን 2014 ዓ.ም ነው።
የጃማ እና ወረኢሉ ከተሞችን ኃይል ለመስጠት በሚያስችል ደረጃ የጥገና ስራ የተጠናቀቀ መሆኑን ተነግሯል።
#EEU
@tikvahethiopia
በሀርቡ ከተማ ተቋርጦ የነበረውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተመልሶ ተገናኝቷል።
በሀርቡ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የተመለሰው ዛሬ ታህሳስ 4 ቀን 2014 ዓ.ም ነው።
የጃማ እና ወረኢሉ ከተሞችን ኃይል ለመስጠት በሚያስችል ደረጃ የጥገና ስራ የተጠናቀቀ መሆኑን ተነግሯል።
#EEU
@tikvahethiopia
#Hayke
ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ሀይቅ ከተማ ከፍተኛ ጉዳት ካስተናገዱ ከተሞች አንዷን መሆኗን ከአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ያገኘነው መረጃ ያሳል።
በጦርነት ምክንያት በከተማው ላይ የሰዎች ህይወት ጠፍቷል፤ የግልና የመንግስት ንብረቶችን እንዳልነበሩ ሆነዋል፤ በከባድ መሳሪያ የተደበደቡ የሲቪል ሰዎች ቤቶችም ስለመኖራቸውም ተገልጿል።
በከተማይቱ ጨረቃው መንደር (ቀበሌ 02 እና 04) በአንድ ቤት ውስጥ ብቻ 3 ሰዎች ሞተው እዛው ግቢ ውስጥ መቀበራቸውን ነዋሪዎች አሳውቀዋል።
የሀይቅ ከተማ ከህወሓት ወረራ ከተለቀቀች አንድ ሳምንት እየተቃረባት ሲሆን እስካሁን ድረስ በተጣራ መረጃ 48 ንፁሃን ሰዎች መሞታቸውን የከተማይቱ ባለስልጣናት ለሬድዮ ጣቢያው ሪፖርት አድርገዋል።
በተጨማሪ ሆስፒታሎች፣ ት/ቤቶች ሌሎች ህብረተሰቡ የሚጠቀምባቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን በውስጣቸው የነበሩ ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል።
በሀይቅ ከተማ ብዙዎቹ የመንግስት ተቋማት መረጃ የሚባል ነገር እንዳይኖራቸው ኮምፒውተሮች በጠቅላላ ወድመዋል፤ የተረፉት መዘረፋቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አመልክተዋል።
የተዘረፈው በአብዛኛው በህወሓት ኃይሎች ሲሆን የአካባቢው ህብረተሰብ ንብረቶችን ለማትረፍ ሲል ወደ ቤቱ ይዟቸው የሄዱ አሉ፤ በአንዳንድ የህበረተሰቡ አባላት የተዘረፉም አሉ።
የሀይቅ ከተማ ባለልስጣናት የተዘረፉትን የማስመለስ ስራ እንዲሁም የህወሓት ኃይሎች እንዳይዘርፏቸው በማለት ወደቤት የተወሰዱትን ንብረቶች ለማስመለስ እየተሰራ መሆኑን ለሬድዮ ጣቢያ አሳውቀዋል።
በሌላ በኩል በደሴ እና ኮምቦልቻ እንዲሁም በሰሜን ሸዋ የተለያዩ ከተሞች ሸዋሮቢት ፣ አጣየ ፣ ደብረሲና ወደቀደመው መደበኛ እንቅስቃሴ ለመመለስ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
@tikvahethiopia
ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ሀይቅ ከተማ ከፍተኛ ጉዳት ካስተናገዱ ከተሞች አንዷን መሆኗን ከአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ያገኘነው መረጃ ያሳል።
በጦርነት ምክንያት በከተማው ላይ የሰዎች ህይወት ጠፍቷል፤ የግልና የመንግስት ንብረቶችን እንዳልነበሩ ሆነዋል፤ በከባድ መሳሪያ የተደበደቡ የሲቪል ሰዎች ቤቶችም ስለመኖራቸውም ተገልጿል።
በከተማይቱ ጨረቃው መንደር (ቀበሌ 02 እና 04) በአንድ ቤት ውስጥ ብቻ 3 ሰዎች ሞተው እዛው ግቢ ውስጥ መቀበራቸውን ነዋሪዎች አሳውቀዋል።
የሀይቅ ከተማ ከህወሓት ወረራ ከተለቀቀች አንድ ሳምንት እየተቃረባት ሲሆን እስካሁን ድረስ በተጣራ መረጃ 48 ንፁሃን ሰዎች መሞታቸውን የከተማይቱ ባለስልጣናት ለሬድዮ ጣቢያው ሪፖርት አድርገዋል።
በተጨማሪ ሆስፒታሎች፣ ት/ቤቶች ሌሎች ህብረተሰቡ የሚጠቀምባቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን በውስጣቸው የነበሩ ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል።
በሀይቅ ከተማ ብዙዎቹ የመንግስት ተቋማት መረጃ የሚባል ነገር እንዳይኖራቸው ኮምፒውተሮች በጠቅላላ ወድመዋል፤ የተረፉት መዘረፋቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አመልክተዋል።
የተዘረፈው በአብዛኛው በህወሓት ኃይሎች ሲሆን የአካባቢው ህብረተሰብ ንብረቶችን ለማትረፍ ሲል ወደ ቤቱ ይዟቸው የሄዱ አሉ፤ በአንዳንድ የህበረተሰቡ አባላት የተዘረፉም አሉ።
የሀይቅ ከተማ ባለልስጣናት የተዘረፉትን የማስመለስ ስራ እንዲሁም የህወሓት ኃይሎች እንዳይዘርፏቸው በማለት ወደቤት የተወሰዱትን ንብረቶች ለማስመለስ እየተሰራ መሆኑን ለሬድዮ ጣቢያ አሳውቀዋል።
በሌላ በኩል በደሴ እና ኮምቦልቻ እንዲሁም በሰሜን ሸዋ የተለያዩ ከተሞች ሸዋሮቢት ፣ አጣየ ፣ ደብረሲና ወደቀደመው መደበኛ እንቅስቃሴ ለመመለስ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
@tikvahethiopia
ፊንላንድ 4.1 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ አደርጋለሁ ብላለች።
ፊንላንድ በኢትዮጵያ 🇪🇹 ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ለህይወት አድን የሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል ተጨማሪ 4.1 ሚሊዮን ዩሮ ለዓለም የምግብ ፕሮግራም-ኢትዮጵያ እንደምትሰጥ አሳውቃለች።
ከዚህም ባለፈ ፊንላንድ በኢትዮጵያ የድርጅቱን የትምህርት ቤት የምግብ ፕሮግራም ለመደገፍ የ1 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ እንደምትሰጥ ገልፃለች።
@tikvahethiopia
ፊንላንድ በኢትዮጵያ 🇪🇹 ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ለህይወት አድን የሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል ተጨማሪ 4.1 ሚሊዮን ዩሮ ለዓለም የምግብ ፕሮግራም-ኢትዮጵያ እንደምትሰጥ አሳውቃለች።
ከዚህም ባለፈ ፊንላንድ በኢትዮጵያ የድርጅቱን የትምህርት ቤት የምግብ ፕሮግራም ለመደገፍ የ1 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ እንደምትሰጥ ገልፃለች።
@tikvahethiopia
ጋዜጠኞቹ ታሰሩ።
የኢትዮጵየ ፌደራል ፖሊስ በህ/ተ/ም/ቤት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው " ሸኔ " በዓለም አቀፍ ደረጃ አስተዋውቀዋል ያላቸውን የአሶሽየትድ ፕረስ ጋዜጠኞችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎች፦
- አሚር አማን፣
- ቶማስ እንግዳ እና አዲሱ ሙሉነህ ናቸው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵየ ፌደራል ፖሊስ በህ/ተ/ም/ቤት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው " ሸኔ " በዓለም አቀፍ ደረጃ አስተዋውቀዋል ያላቸውን የአሶሽየትድ ፕረስ ጋዜጠኞችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎች፦
- አሚር አማን፣
- ቶማስ እንግዳ እና አዲሱ ሙሉነህ ናቸው።
@tikvahethiopia
#UNESCO #WHO
" ... ድርጅቶቹ ያለአድሎ ኃላፊነታቸውን ሊወጡና የህወሃት ቡድን የፈጸመውን ውድመት በይፋ ማውገዝ ይጠበቅባቸው ነበር " - አቶ ዮሴፍ ካሳዬ
ዛሬ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ካሳዬ በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ተጠሪ ከሆኑት ዶ/ር ዮሚኮ ዮኮዝኪ እና የዓለም ጤና ድርጅት ተጠሪ ዶ/ር በርማ ኤች. ሳምቦ ጋር ተወያይተዋል።
በወቅቱም አቶ ዮሴፍ ፥ የህወሓት የሽብር ቡድን የትግራይ ክልልን ጨምሮ በአፋር እና አማራ ክልሎች የባህላዊ ቅርሶች እና የጤና መሰረተ ልማቶች ላይ የፈጸመውን ውድመት ለማውገዝ ድርጅቶቹ ቸልተኝነት ማሳየታቸው ገልጸውላቸዋል።
አቶ ዮሴፍ ፥ " ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ንብረቶች ላይ የደረሰው ውድመት እና የንብረት ዘረፋ ከፍተኛ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው " ያሉ ሲሆን " የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጉዳዩን በቸልታ ማለፉ ህወሃት በተግባሩ እንዲገፋበት አበረታቶታል " ብለዋል።
ኢትዮጵያ እንደ ተመድ መስራች አባልነቷ ከሁሉም የተመድ ድርጅቶች ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት እንዳላት አንስተው፣ ድርጅቶቹም ያለአድሎ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡና የህወሃት ቡድን የፈጸመውን ውድመት በይፋ ማውገዝ ይጠበቅባቸው እንደነበረ አጽንዖት ሰጥተው ገልጸዋል።
የስራ ኃላፊዎቹ በበኩላቸው ከዋና ዳይሬክተሩ ጋር ስላደረጉት ውይይት ምስጋናቸውን ገልፀው፣ ያላቸውን ኃላፊነት ግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የኢትዮጵያን ጉዳይ በአንክሮ ለመመልከት ቃል መግባታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
" ... ድርጅቶቹ ያለአድሎ ኃላፊነታቸውን ሊወጡና የህወሃት ቡድን የፈጸመውን ውድመት በይፋ ማውገዝ ይጠበቅባቸው ነበር " - አቶ ዮሴፍ ካሳዬ
ዛሬ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ካሳዬ በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ተጠሪ ከሆኑት ዶ/ር ዮሚኮ ዮኮዝኪ እና የዓለም ጤና ድርጅት ተጠሪ ዶ/ር በርማ ኤች. ሳምቦ ጋር ተወያይተዋል።
በወቅቱም አቶ ዮሴፍ ፥ የህወሓት የሽብር ቡድን የትግራይ ክልልን ጨምሮ በአፋር እና አማራ ክልሎች የባህላዊ ቅርሶች እና የጤና መሰረተ ልማቶች ላይ የፈጸመውን ውድመት ለማውገዝ ድርጅቶቹ ቸልተኝነት ማሳየታቸው ገልጸውላቸዋል።
አቶ ዮሴፍ ፥ " ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ንብረቶች ላይ የደረሰው ውድመት እና የንብረት ዘረፋ ከፍተኛ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው " ያሉ ሲሆን " የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጉዳዩን በቸልታ ማለፉ ህወሃት በተግባሩ እንዲገፋበት አበረታቶታል " ብለዋል።
ኢትዮጵያ እንደ ተመድ መስራች አባልነቷ ከሁሉም የተመድ ድርጅቶች ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት እንዳላት አንስተው፣ ድርጅቶቹም ያለአድሎ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡና የህወሃት ቡድን የፈጸመውን ውድመት በይፋ ማውገዝ ይጠበቅባቸው እንደነበረ አጽንዖት ሰጥተው ገልጸዋል።
የስራ ኃላፊዎቹ በበኩላቸው ከዋና ዳይሬክተሩ ጋር ስላደረጉት ውይይት ምስጋናቸውን ገልፀው፣ ያላቸውን ኃላፊነት ግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የኢትዮጵያን ጉዳይ በአንክሮ ለመመልከት ቃል መግባታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA : አሜሪካ በድሮን ጥቃት በካቡል ለገደለቻቸው ንፁሃን አፍጋነስታውያን ዘመዶች ካሳ እከፍላለሁ ብላለች። ከጥቂት ወራት በፊት ካቡል የአሜሪካ ጦር በድሮን ጥቃት ንፁሃንን መገድሉ፤ በኃላ እርምጃው በስህተት የተፈፀመ እንደሆነ መግለፁ ፤ ይቅርታም መጠየቁ አይዘነጋም። በወቅቱ አሜሪካ ጨቅላ ህፃናትን ጨምሮ አጠቃላይ 10 ሰዎችን ነበር የገደለችው። አሜሪካ ለገደለችው 10 ሰዎች ዘመዶች የገንዘብ ካሳ…
" አደጋውን ያደረሱት የሠራዊቱ አባላት አይቀጡም " - ፔንታገን
ባለፈው ነሃሴ ወር በአፍጋኒስታን በአሜሪካ ድሮን ለተገደሉ 10 ሰላማዊ ሰዎች የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር፣ ፔንታገን አደጋውን ያደረሱትን የሠራዊቱን አባላት እንደማይቀጣ አስታወቀ፡፡
ከዚህ ውሳኔ የተደረሰው የመከላከያ ሚኒስትሩ ሎይድ ኦስተን ከሁለት የበላይ አዛዦች የቀረበላቸውን አስተያየት ካጸደቁ በኋላ መሆኑ ተነግሯል፡፡
የፔንታገን ቃል አቀባይ ጆርን ከርቢ ለቪኦኤ ለቀረበላቸው ጥያቄ እንደተናገሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ በጉዳይ ላይ ተጨማሪ የተጠያቂነት ምርመራ እንደማይፈቅዱ ማስታወቃቸውን ገልጸዋል፡፡
ፔንታገን ገለልተኛ መርማሪ መድቦ ሁኔታውን ካጣራ በኋላ እኤአ ነሀሴ 29 የተፈጸመው አደጋ “አስዛኝ ስህተት ነው” ብሏል፡፡
“ የተፈጸመው ስህተት የተሳሳተ መረጃን አምኖ ከመቀበል እንጂ ከንዝህላልነት ወንጀል የተከሰተ ነው ብሎ እንደማያምንም ” ፔንታገን አስታውቋል፡፡
በወቅቱ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ከሀሚድ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ 13 አሜሪካውያንን ጨምሮ 170 የአፍጋን ሰዎችን በገደለበት ማግስት በተካሄደ የድሮን ጥቃት ሰባት ህጻናትን ጨምሮ 10 ሰዎች መሞታቸው ይታወቃል፡፡ ~ ቪኦኤ
@tikvahethiopia
ባለፈው ነሃሴ ወር በአፍጋኒስታን በአሜሪካ ድሮን ለተገደሉ 10 ሰላማዊ ሰዎች የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር፣ ፔንታገን አደጋውን ያደረሱትን የሠራዊቱን አባላት እንደማይቀጣ አስታወቀ፡፡
ከዚህ ውሳኔ የተደረሰው የመከላከያ ሚኒስትሩ ሎይድ ኦስተን ከሁለት የበላይ አዛዦች የቀረበላቸውን አስተያየት ካጸደቁ በኋላ መሆኑ ተነግሯል፡፡
የፔንታገን ቃል አቀባይ ጆርን ከርቢ ለቪኦኤ ለቀረበላቸው ጥያቄ እንደተናገሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ በጉዳይ ላይ ተጨማሪ የተጠያቂነት ምርመራ እንደማይፈቅዱ ማስታወቃቸውን ገልጸዋል፡፡
ፔንታገን ገለልተኛ መርማሪ መድቦ ሁኔታውን ካጣራ በኋላ እኤአ ነሀሴ 29 የተፈጸመው አደጋ “አስዛኝ ስህተት ነው” ብሏል፡፡
“ የተፈጸመው ስህተት የተሳሳተ መረጃን አምኖ ከመቀበል እንጂ ከንዝህላልነት ወንጀል የተከሰተ ነው ብሎ እንደማያምንም ” ፔንታገን አስታውቋል፡፡
በወቅቱ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ከሀሚድ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ 13 አሜሪካውያንን ጨምሮ 170 የአፍጋን ሰዎችን በገደለበት ማግስት በተካሄደ የድሮን ጥቃት ሰባት ህጻናትን ጨምሮ 10 ሰዎች መሞታቸው ይታወቃል፡፡ ~ ቪኦኤ
@tikvahethiopia
#UAE
ዩኤኢ የሪፐር ድሮኖች እንዲሁም የተዋጊ ጄቶችን ግዢ ልትተወው ነው ?
የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ (UAE) ከ23 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ገንዘብ አሜሪካን ሰራሽ ኤፍ-35 ተዋጊ ጄቶችን ፣ ሪፐር ድሮኖችንና ሌሎች እጅግ የዘመኑ ጥይቶችን ለመግዛት ያላትን ስምምነት ልትተወው መሆኑን ዎል ስትሪት ጆርናል ዛሬ ዘግቧል።
የባህረ ሰላጤዋ የአሜሪካ አጋር የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ (UAE) የአሜሪካ የደህንነት መስፈርቶች በጣም ከባድ ናቸው የሚል ቅሬታ ማቅረቧን ስማቸው ያልተገለፀ የአሜሪካ ባለስልጣናትን ዋቢ በማድረግ ዎል ስትሪት ጆርናል አስነብቧል።
ጉዳዩን በተመለከተ የኤፍ-35 ኮንትራክተር ሎክሄድ ማርቲን ኮርፕ (LMT.N)፣ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያቤት እንዲሁም የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ወዲያው ምላሽ አልሰጡም።
ሮይተርስ ፥ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቴስ 50 ኤፍ-35 ጄቶች እና እስከ 18 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (ድሮኖች) ለመግዛት ከአሜሪካ ጋር ስምምነት መፈራረማቸውን ጉዳዩን ከሚያውቁ ሰዎች በጥር ወር መስማቱን ገልጿል።
ለአሜሪካ በጣም ቅርብ ከሆኑ የመካከለኛው ምስራቅ አጋሮች አንዷ የሆነችው የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (UAE) በሎክሄድ ማርቲን የተሰሩትን ኤፍ-35 የጦር ጄቶች ለመግዛት ፍላጎቷን ስትገልጽ ነበር ፤ በተለይ በ2020 ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መመስረቷ ኤፍ-35 የጦር ጄቶችን በእጇ እንድታስገባ እንደሚያግዛት ሲነገር ነበር።
እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ ብቸኛ የኤፍ- 35 የጦር ጄቶች ተጠቃሚ ናት።
@tikvahethiopia
ዩኤኢ የሪፐር ድሮኖች እንዲሁም የተዋጊ ጄቶችን ግዢ ልትተወው ነው ?
የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ (UAE) ከ23 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ገንዘብ አሜሪካን ሰራሽ ኤፍ-35 ተዋጊ ጄቶችን ፣ ሪፐር ድሮኖችንና ሌሎች እጅግ የዘመኑ ጥይቶችን ለመግዛት ያላትን ስምምነት ልትተወው መሆኑን ዎል ስትሪት ጆርናል ዛሬ ዘግቧል።
የባህረ ሰላጤዋ የአሜሪካ አጋር የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ (UAE) የአሜሪካ የደህንነት መስፈርቶች በጣም ከባድ ናቸው የሚል ቅሬታ ማቅረቧን ስማቸው ያልተገለፀ የአሜሪካ ባለስልጣናትን ዋቢ በማድረግ ዎል ስትሪት ጆርናል አስነብቧል።
ጉዳዩን በተመለከተ የኤፍ-35 ኮንትራክተር ሎክሄድ ማርቲን ኮርፕ (LMT.N)፣ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያቤት እንዲሁም የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ወዲያው ምላሽ አልሰጡም።
ሮይተርስ ፥ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቴስ 50 ኤፍ-35 ጄቶች እና እስከ 18 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (ድሮኖች) ለመግዛት ከአሜሪካ ጋር ስምምነት መፈራረማቸውን ጉዳዩን ከሚያውቁ ሰዎች በጥር ወር መስማቱን ገልጿል።
ለአሜሪካ በጣም ቅርብ ከሆኑ የመካከለኛው ምስራቅ አጋሮች አንዷ የሆነችው የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (UAE) በሎክሄድ ማርቲን የተሰሩትን ኤፍ-35 የጦር ጄቶች ለመግዛት ፍላጎቷን ስትገልጽ ነበር ፤ በተለይ በ2020 ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መመስረቷ ኤፍ-35 የጦር ጄቶችን በእጇ እንድታስገባ እንደሚያግዛት ሲነገር ነበር።
እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ ብቸኛ የኤፍ- 35 የጦር ጄቶች ተጠቃሚ ናት።
@tikvahethiopia
" የተመድ የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት ያደርገዋል የተባለው ስብሰባ የተቋሙን ገለልተኝነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው " - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የተመድ የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት በመጪው አርብ ያደርገዋል የተባለው ስብሰባ የተቋሙን ገለልተኝነት በጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ፡፡
በምክር ቤቱ የተወከሉ በርካታ የአፍሪካ አገራት እያሉ በስብሰባው የሚካፈል አንዳችም የአፍሪካ አገር አለመኖሩ የውጭ ጣልቃ ገብነቱ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ላይ የተቃጣ መሆኑን ያሳያል ብሏል፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ እንዳሉት እንደተባለው በትግራይ ውስጥ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ቢፈፀም እንኳ መንግስት አለ የተባለውን ችግር በማጣራት እና የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ ላይ ባለበት ሁኔታ ስብሰባው መደረግ አልነበረበትም፡፡
ስብሰባው የተወሰኑ መንግስታትን ፍላጎት ለማስፈፀም የሚካሄድ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ተቋሙም በነዚህ መንግስታት ተፅዕኖ ስር ወድቋል ነው ያሉት፡፡
አቶ ከበደ ዴሲሳ ፥ "የተመድ የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አሸባሪው ህወሓት በአማራና በአፋር ክልሎች የፈፀማቸውን አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዝምታ አልፏቸዋል " ብለዋል።
በተጨማሪም " የዓለም የጤና ድርጅት እና ዩኔስኮም በተጠቀሱት ክልሎች በርካታ የጤና ተቋማት እና ትምህርት ቤቶች እንዲሁም የዓለም መካነ ቅርሶች ሲወድሙ ድርጊቱን በማውገዝ ፈንታ በዝምታ ማለፍን መርጠዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የነዚህን ተቋማት መርህን ያልተከተለ አሰራር እና አቋም በጥብቅ ትቃወማለች ሲሉ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ መናገራቸውን ኢብኮ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የተመድ የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት በመጪው አርብ ያደርገዋል የተባለው ስብሰባ የተቋሙን ገለልተኝነት በጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ፡፡
በምክር ቤቱ የተወከሉ በርካታ የአፍሪካ አገራት እያሉ በስብሰባው የሚካፈል አንዳችም የአፍሪካ አገር አለመኖሩ የውጭ ጣልቃ ገብነቱ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ላይ የተቃጣ መሆኑን ያሳያል ብሏል፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ እንዳሉት እንደተባለው በትግራይ ውስጥ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ቢፈፀም እንኳ መንግስት አለ የተባለውን ችግር በማጣራት እና የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ ላይ ባለበት ሁኔታ ስብሰባው መደረግ አልነበረበትም፡፡
ስብሰባው የተወሰኑ መንግስታትን ፍላጎት ለማስፈፀም የሚካሄድ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ተቋሙም በነዚህ መንግስታት ተፅዕኖ ስር ወድቋል ነው ያሉት፡፡
አቶ ከበደ ዴሲሳ ፥ "የተመድ የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አሸባሪው ህወሓት በአማራና በአፋር ክልሎች የፈፀማቸውን አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዝምታ አልፏቸዋል " ብለዋል።
በተጨማሪም " የዓለም የጤና ድርጅት እና ዩኔስኮም በተጠቀሱት ክልሎች በርካታ የጤና ተቋማት እና ትምህርት ቤቶች እንዲሁም የዓለም መካነ ቅርሶች ሲወድሙ ድርጊቱን በማውገዝ ፈንታ በዝምታ ማለፍን መርጠዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የነዚህን ተቋማት መርህን ያልተከተለ አሰራር እና አቋም በጥብቅ ትቃወማለች ሲሉ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ መናገራቸውን ኢብኮ ዘግቧል።
@tikvahethiopia