" CNN ኢትዮጵያ እና ዓለምን ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል " - ቢልለኔ ስዩም
CNN አዲስ አበባ ተከባለች በማለት የዓለም ማህበረሰብን ከዋሸ አንድ ወር እንደሆነው የጠ/ሚር ፅህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬተሪ ቢልለኔ ስዩም በተረጋገጠ የትዊተር ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አማፅያንን ከዋና ዋና ስፍራዎች እያጸዳ ባለበት ወቅት ፣ CNN በመረጃ ማዛባት ያለመረጋጋት መሳሪያ ሆኖ በማገልገሉ ኢትዮጵያ እና ዓለምን ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባዋል ብለዋል።
@tikvahethiopia
CNN አዲስ አበባ ተከባለች በማለት የዓለም ማህበረሰብን ከዋሸ አንድ ወር እንደሆነው የጠ/ሚር ፅህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬተሪ ቢልለኔ ስዩም በተረጋገጠ የትዊተር ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አማፅያንን ከዋና ዋና ስፍራዎች እያጸዳ ባለበት ወቅት ፣ CNN በመረጃ ማዛባት ያለመረጋጋት መሳሪያ ሆኖ በማገልገሉ ኢትዮጵያ እና ዓለምን ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባዋል ብለዋል።
@tikvahethiopia
#iTena
ህብረተሰቡ መሰረታዊ የጤና ትምህርት በነፃ የሚያገኝበት ማዕከል ተመረቀ፡፡
" የጤና ትምህርት ለሁሉም " በሚል መሪ ቃል በተጀመረው የማኅበረሰብ የጤና ስልጠና ማዕከል ለህብረተሰቡ ውስብስብ ባልሆኑ እና አሳታፊ በሆኑ መንገዶች የጤና እውቀት ማስጨበጫ ይሰጣልም ተብሏል፡፡
iTena(አይ ጤና) በተሰኘው ተቋም የሚሰጠው ይህ አገልግሎት ከዚህ ቀደም የጤና ትምህርት የጤና ባለሙያ መሆን ለሚፈልግ ሰው ብቻ መሰጠቱን የሚያስቀር መሆኑም የተቋሙ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እየሩሳሌም ማሞ ገልፀዋል።
በማዕከሉ ወሳኝ የጤና ትምህርት ናቸው ተብሎ በሚታመንባቸው ፦
- የጤናማ አመጋገብ ስርዓቶች፣
- የስነ ተዋልዶ እና የቤተሰብ ምጣኔ ትምህርቶች፣
- እንደ ስኳር እና የደም ግፊት አይነት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ፣
- እንደ ሰሞነኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ አይነት ተላላፊ በሽታዎች እና ሌሎችም ትኩረት ተደርጎ ይሰጣል ብለዋል።
በተጨማሪ ከበሽታ መከላከያ ትምህርቶች ባሻገር በተለያዩ በሽታዎች ለተጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎች በሽታው የባሰ ጉዳት እንዳያደርስባቸው ማድረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች እና አጠቃላይ ማንቃት ላይ ያተኮሩ ትምህርቶች እንደሚሰጡም አሳውቀዋል።
ይህም በቀላሉ ሊድኑ በሚችሉ በሽታዎች ሕይወታቸው የሚያልፍ ዜጎችን ቁጥር ለመቀነስ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ነው የተነገረው፡፡
iTena(አይ ጤና) በ አራት ሃኪሞች የተመሰረተ እና ለማህበረሰቡ የቆመ ድርጅት መሆኑን የሚገልፅ ሲሆን ከዚህ አገልግሎት በተጨማሪም የህክምና ጥሪ ማዕከል፣ የቤት ለቤት ህክምና እነዲሁም እና ተቋማት ላይ ያተኮረ የጤና አገልግሎትን በመስጠት ላይ እገኛለሁ ብሏል፡፡
(በጋዜጠኛ አሸናፊ)
@tikvahethiopia
ህብረተሰቡ መሰረታዊ የጤና ትምህርት በነፃ የሚያገኝበት ማዕከል ተመረቀ፡፡
" የጤና ትምህርት ለሁሉም " በሚል መሪ ቃል በተጀመረው የማኅበረሰብ የጤና ስልጠና ማዕከል ለህብረተሰቡ ውስብስብ ባልሆኑ እና አሳታፊ በሆኑ መንገዶች የጤና እውቀት ማስጨበጫ ይሰጣልም ተብሏል፡፡
iTena(አይ ጤና) በተሰኘው ተቋም የሚሰጠው ይህ አገልግሎት ከዚህ ቀደም የጤና ትምህርት የጤና ባለሙያ መሆን ለሚፈልግ ሰው ብቻ መሰጠቱን የሚያስቀር መሆኑም የተቋሙ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እየሩሳሌም ማሞ ገልፀዋል።
በማዕከሉ ወሳኝ የጤና ትምህርት ናቸው ተብሎ በሚታመንባቸው ፦
- የጤናማ አመጋገብ ስርዓቶች፣
- የስነ ተዋልዶ እና የቤተሰብ ምጣኔ ትምህርቶች፣
- እንደ ስኳር እና የደም ግፊት አይነት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ፣
- እንደ ሰሞነኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ አይነት ተላላፊ በሽታዎች እና ሌሎችም ትኩረት ተደርጎ ይሰጣል ብለዋል።
በተጨማሪ ከበሽታ መከላከያ ትምህርቶች ባሻገር በተለያዩ በሽታዎች ለተጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎች በሽታው የባሰ ጉዳት እንዳያደርስባቸው ማድረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች እና አጠቃላይ ማንቃት ላይ ያተኮሩ ትምህርቶች እንደሚሰጡም አሳውቀዋል።
ይህም በቀላሉ ሊድኑ በሚችሉ በሽታዎች ሕይወታቸው የሚያልፍ ዜጎችን ቁጥር ለመቀነስ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ነው የተነገረው፡፡
iTena(አይ ጤና) በ አራት ሃኪሞች የተመሰረተ እና ለማህበረሰቡ የቆመ ድርጅት መሆኑን የሚገልፅ ሲሆን ከዚህ አገልግሎት በተጨማሪም የህክምና ጥሪ ማዕከል፣ የቤት ለቤት ህክምና እነዲሁም እና ተቋማት ላይ ያተኮረ የጤና አገልግሎትን በመስጠት ላይ እገኛለሁ ብሏል፡፡
(በጋዜጠኛ አሸናፊ)
@tikvahethiopia
#በድጋሚ
ቴሌግራም ላይ Tikvah-Marketና Tikvah-Mart በሚል በአጭበርባሪዎች የተከፈቱ እንጂ ትክክልኛ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ስር ያሉ አይደሉም።
ገፆቹ በመቶ ሺዎች ሚቆጠሩ ሰዎች ያሉባቸው መሆኑን የተመለከትን ሲሆን ሁሉም ድርጊታቸው ከቲክቫህ ጋር የማይገናኝ እና ስራቸውም በስማችን ማጭበርበር ነው።
ውድ ቤተሰቦቻችን ከመሰል አጭበርባሪዎች ራሳችሁን እንድትጠብቁ በድጋሚ አደራ እንላለን።
በዚሁ አጋጣሚ በየዕለቱን የቲክቫህ አባል እየሆናችሁ ለምትገኙ በሺዎች የምትቆጠሩ ቤተሰቦቻችን በኛ ስር ያሉት ትክክለኛ ገፆች የሚከተሉት ናቸው ፦
🕊 @tikvahethiopia (ከ1.2 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሉት)
🕊 @tikvahethmagazine (ከ240 ሺ በላይ አባላት ያሉት)
🕊 @tikvahethsport (ከ145 ሺህ በላይ አባላት ያሉት)
🕊@tikvahuniversity (ከ103 ሺ በላይ አባላት ያሉት)
🕊 @tikvahethAFAANOROMOO (ከ19 ሺ በላይ አባላት ያሉት)
🕊 ቲዊተር twitter.com/tikvahethiopia?s=09
NB : ቲክቫህ ኢትዮጵያ Face book ሆነ አሁን ላይ አገልግሎት የሚሰጥ የYou Tube አካውንት በስሙ የለም።
ቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ሰብዓዊነትን ያስቀደሙ እና ሀገራቸው ኢትዮጵያን የሚያከብሩ እንዲሁም የሚወዱ ዜጎች መሰባሰቢያ መድረክ ሲሆን በወቅታዊ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ክንውኖች ዙሪያ የእርስ በእርስ መረጃ ልውውጥ ይደረግበታል።
ከየትኛውም የፖለቲካ ፣ የብሄር፣ የሃይማኖት ውግንና የራቀ ሲሆን ኢትዮጵያን እንደሀገር ያከበሩና ሀገሪቱን አደጋ ላይ የማይጥሉ የተለያዩ አመለካከቶች እንዲሁም አስተሳሰቦች ያሏቸውን ቤተሰቦቹን የሚያሰባስብ ነው።
@tikvahethiopia
ቴሌግራም ላይ Tikvah-Marketና Tikvah-Mart በሚል በአጭበርባሪዎች የተከፈቱ እንጂ ትክክልኛ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ስር ያሉ አይደሉም።
ገፆቹ በመቶ ሺዎች ሚቆጠሩ ሰዎች ያሉባቸው መሆኑን የተመለከትን ሲሆን ሁሉም ድርጊታቸው ከቲክቫህ ጋር የማይገናኝ እና ስራቸውም በስማችን ማጭበርበር ነው።
ውድ ቤተሰቦቻችን ከመሰል አጭበርባሪዎች ራሳችሁን እንድትጠብቁ በድጋሚ አደራ እንላለን።
በዚሁ አጋጣሚ በየዕለቱን የቲክቫህ አባል እየሆናችሁ ለምትገኙ በሺዎች የምትቆጠሩ ቤተሰቦቻችን በኛ ስር ያሉት ትክክለኛ ገፆች የሚከተሉት ናቸው ፦
🕊 @tikvahethiopia (ከ1.2 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሉት)
🕊 @tikvahethmagazine (ከ240 ሺ በላይ አባላት ያሉት)
🕊 @tikvahethsport (ከ145 ሺህ በላይ አባላት ያሉት)
🕊@tikvahuniversity (ከ103 ሺ በላይ አባላት ያሉት)
🕊 @tikvahethAFAANOROMOO (ከ19 ሺ በላይ አባላት ያሉት)
🕊 ቲዊተር twitter.com/tikvahethiopia?s=09
NB : ቲክቫህ ኢትዮጵያ Face book ሆነ አሁን ላይ አገልግሎት የሚሰጥ የYou Tube አካውንት በስሙ የለም።
ቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ሰብዓዊነትን ያስቀደሙ እና ሀገራቸው ኢትዮጵያን የሚያከብሩ እንዲሁም የሚወዱ ዜጎች መሰባሰቢያ መድረክ ሲሆን በወቅታዊ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ክንውኖች ዙሪያ የእርስ በእርስ መረጃ ልውውጥ ይደረግበታል።
ከየትኛውም የፖለቲካ ፣ የብሄር፣ የሃይማኖት ውግንና የራቀ ሲሆን ኢትዮጵያን እንደሀገር ያከበሩና ሀገሪቱን አደጋ ላይ የማይጥሉ የተለያዩ አመለካከቶች እንዲሁም አስተሳሰቦች ያሏቸውን ቤተሰቦቹን የሚያሰባስብ ነው።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ሆቴሎች፤ ለገና በዓል ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ እንግዶች ቅናሽ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበላቸው።
የአዲስ አበባ ሆቴል ባለንብረቶች ንግድ ዘርፍ ማህበር፤ ለመጪው የገና በዓል ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ እንግዶች በስሩ የሚገኙ ሆቴሎች ልዩ ቅናሽ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረቡን www.ethiopiainsider.com ዘግቧል።
ማህበሩ ጥሪውን ያቀረበው 170 ገደማ ለሆኑ ሆቴሎች መሆኑን ተገልጿል።
ማህበሩ በዚህ ሳምንት አጋማሽ ባሰራጨው ደብዳቤ፤ የማህበሩ አባል የሆኑ ሁሉም ሆቴሎች ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ እንግዶች የተለየ ቅናሽ እና አቀባበል እንዲያደርጉ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ሆቴሎች፤ ለገና በዓል ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ እንግዶች ቅናሽ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበላቸው።
የአዲስ አበባ ሆቴል ባለንብረቶች ንግድ ዘርፍ ማህበር፤ ለመጪው የገና በዓል ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ እንግዶች በስሩ የሚገኙ ሆቴሎች ልዩ ቅናሽ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረቡን www.ethiopiainsider.com ዘግቧል።
ማህበሩ ጥሪውን ያቀረበው 170 ገደማ ለሆኑ ሆቴሎች መሆኑን ተገልጿል።
ማህበሩ በዚህ ሳምንት አጋማሽ ባሰራጨው ደብዳቤ፤ የማህበሩ አባል የሆኑ ሁሉም ሆቴሎች ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ እንግዶች የተለየ ቅናሽ እና አቀባበል እንዲያደርጉ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#HappeningNow በቴፒ ከተማ የእርቀ ሠላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። በደ/ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሸካ ዞን በተለይ በየኪ ወረዳ እና ቴፒ ከተማ ተፈጥሮ የነበረውን የጸጥታ ችግር በእርቀ ሠላም ኮንፈረንስ ለመፍታት ያለመው የእርቅ እና የሰላም መድረክ በቴፒ ከተማ በአሁን ሰዓት እየተካሄደ ይገኛል። @tikvahethiopia
#TEPI
የቴፒ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ዓመታት በፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች ሀዘኑን ገልፆ ለደረሰው ጉዳትና እና ህዝብ ላይ ለደረሰው በደል ይቅርታ ጠይቋል።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ገላቲያስ ሻሜ ዛሬ በከተማው በነበረ የሰላም ኮንፈረንስ መድረክ ላይ ንግግር አድርገዋል።
ከንቲባ አቶ ገላቲያስ ሻሜ ባሰሙት ንግግር ፥ ባለፉት ዓመታት በተፈጠረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልጸው ለደረሰው ጉዳናት፣ የህዝብ በደል ይቅርታ ጠይቀዋል።
ከመለያየትና መቃቃር ለውጥ እንደማይመጣ ያነሱት ከንቲባው በመፈቃቀርና በመቻቻል ከሠራን ቴፒ ከተማ እንዲሁም ዞኑ ለሁሉም ይበቃል ብለዋል።
በቴፒና አካባቢዋ ሠላም እንዲሰፍን ከፍተኛ ሚና ለተወጡ ባለድርሻ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው ዕለት የጦር መሳሪያ ታጥቀው ጫካ ሸፍተው ከነበሩት ውስጥ ሁለቱ የታጠቁትን መሣሪያ ለፀጥታ ኮማንድ ፖስት አስረክበው ፤ በህዝቡ ፊት ቀርበው ይቅርታ ጠይቀው ከህዝቡ ጋር መቀላቀላቸው ተገልጿል።
ሌሎችም በዚህ መልኩ የታጠቁትን ለኮማንድ ፖስቱ በሠላም እያስረከቡ ከህዝቡ ጋር እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቀርቧል።
ተጨማሪ የዛሬው የሰላም ኮንፈረንስ በተመለከተ ከደቡብ ምዕራብ ክልል ኮሚኒኬሽን የተገኘውን መረጃ በዚህ https://telegra.ph/SWER-12-04 መመልከት ይቻላል።
@tikvahethiopia
የቴፒ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ዓመታት በፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች ሀዘኑን ገልፆ ለደረሰው ጉዳትና እና ህዝብ ላይ ለደረሰው በደል ይቅርታ ጠይቋል።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ገላቲያስ ሻሜ ዛሬ በከተማው በነበረ የሰላም ኮንፈረንስ መድረክ ላይ ንግግር አድርገዋል።
ከንቲባ አቶ ገላቲያስ ሻሜ ባሰሙት ንግግር ፥ ባለፉት ዓመታት በተፈጠረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልጸው ለደረሰው ጉዳናት፣ የህዝብ በደል ይቅርታ ጠይቀዋል።
ከመለያየትና መቃቃር ለውጥ እንደማይመጣ ያነሱት ከንቲባው በመፈቃቀርና በመቻቻል ከሠራን ቴፒ ከተማ እንዲሁም ዞኑ ለሁሉም ይበቃል ብለዋል።
በቴፒና አካባቢዋ ሠላም እንዲሰፍን ከፍተኛ ሚና ለተወጡ ባለድርሻ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው ዕለት የጦር መሳሪያ ታጥቀው ጫካ ሸፍተው ከነበሩት ውስጥ ሁለቱ የታጠቁትን መሣሪያ ለፀጥታ ኮማንድ ፖስት አስረክበው ፤ በህዝቡ ፊት ቀርበው ይቅርታ ጠይቀው ከህዝቡ ጋር መቀላቀላቸው ተገልጿል።
ሌሎችም በዚህ መልኩ የታጠቁትን ለኮማንድ ፖስቱ በሠላም እያስረከቡ ከህዝቡ ጋር እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቀርቧል።
ተጨማሪ የዛሬው የሰላም ኮንፈረንስ በተመለከተ ከደቡብ ምዕራብ ክልል ኮሚኒኬሽን የተገኘውን መረጃ በዚህ https://telegra.ph/SWER-12-04 መመልከት ይቻላል።
@tikvahethiopia
ላሊበላ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት መውደሙ ተገለፀ።
የታሪካዊቷ እና የበርካታ ቱሪስቶች መዳረሻ የሆነችው ላሊበላ ከተማ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተገልጿል።
የጋይንት ጋሸና ግንባር ኮማንድ ፖስት የህወሓት ቡድን የኤርፖርቱን መሰረተ ልማት እጅግ አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ ማውደሙን አሳውቋል።
የላሊበላ ከተማ በሀገር መከላከያ ሠራዊት ፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻና ፋኖ ከቀናት በፊት በቁጥጥር ስር መዋሏ መገለፁ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
የታሪካዊቷ እና የበርካታ ቱሪስቶች መዳረሻ የሆነችው ላሊበላ ከተማ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተገልጿል።
የጋይንት ጋሸና ግንባር ኮማንድ ፖስት የህወሓት ቡድን የኤርፖርቱን መሰረተ ልማት እጅግ አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ ማውደሙን አሳውቋል።
የላሊበላ ከተማ በሀገር መከላከያ ሠራዊት ፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻና ፋኖ ከቀናት በፊት በቁጥጥር ስር መዋሏ መገለፁ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት በህወሓት ተይዘው የነበሩ ተጨማሪ ቦታዎች ነፃ ማውጣቱ ተገልጿል። የፀጥታ ኃይሎች ጥምረቱ ፦ - የመሐል ሜዳ፣ - ጨፋ ሮቢት፣ - ሐርቡና መኮይ ከተሞችና አካባቢውን ነጻ እንዳወጣ የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አሳውቋል። የኢትዮጵየ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ " ጥምር የጸጥታ ኃይሎቹ በጥልቀት ገብተው…
#Update
ተጨማሪ ከተሞች ነፃ መውጣታቸው ተገልጿል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ " በጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት በ "ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" ባካሄደው ኦፐሬሽን ተጨማሪ ከተሞችን ከአሸባሪው ሕወሐት ነጻ አውጥቷል ፤ በጥልቀት በመግባትም የአሸባሪውን ጀሌዎች የመማረክና የመደምሰስ ተግባሩን ቀጥሏል " ሲል አሳውቋል።
በዚህ መሠረት በጋሸና ግንባር ቀውዝባና ጭላ ከተሞችና አካባቢያቸው ነጻ ወጥተዋል።
በወረኢሉ ግንባር በተደረገው ኦፐሬሽን አጅባር፣ ተንታ እና ዶባ ከተሞችና አካባቢያቸው ነጻ ወጥተዋል።
በከሚሴ ግንባር ማጀቴን ፣ ጭረቲን ፣ ከሚሴን ፣ ርቄን ፣ ወለዲን ፣ አልቡኮ ከተሞችን እና የቃሉ ወረዳን አብዛኛውን ክፍል በመቆጣጠር፣ ጥምር ጦሩ ወደ ኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ እየገሰገሰ እንደሚገኝ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፥ " ዛሬ እና ትናንት በተደረጉት ከፍተኛ የማጥቃት ኦፐሬሽኖች አብዛኛው የአሸባሪው ኃይል ከመቼውም ጊዜ በላይ እንዲበተን ተደርጓል " ያለ ሲሆን አስቀድሞ ነጻ በወጡት በምሥራቅ፣ በምዕራብና በመሐል ግንባር በሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች መንግሥታዊ አስተዳደር ተመልሶ በመደራጀት ሥራውን ጀምሯል ብሏል።
@tikvahethiopia
ተጨማሪ ከተሞች ነፃ መውጣታቸው ተገልጿል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ " በጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት በ "ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" ባካሄደው ኦፐሬሽን ተጨማሪ ከተሞችን ከአሸባሪው ሕወሐት ነጻ አውጥቷል ፤ በጥልቀት በመግባትም የአሸባሪውን ጀሌዎች የመማረክና የመደምሰስ ተግባሩን ቀጥሏል " ሲል አሳውቋል።
በዚህ መሠረት በጋሸና ግንባር ቀውዝባና ጭላ ከተሞችና አካባቢያቸው ነጻ ወጥተዋል።
በወረኢሉ ግንባር በተደረገው ኦፐሬሽን አጅባር፣ ተንታ እና ዶባ ከተሞችና አካባቢያቸው ነጻ ወጥተዋል።
በከሚሴ ግንባር ማጀቴን ፣ ጭረቲን ፣ ከሚሴን ፣ ርቄን ፣ ወለዲን ፣ አልቡኮ ከተሞችን እና የቃሉ ወረዳን አብዛኛውን ክፍል በመቆጣጠር፣ ጥምር ጦሩ ወደ ኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ እየገሰገሰ እንደሚገኝ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፥ " ዛሬ እና ትናንት በተደረጉት ከፍተኛ የማጥቃት ኦፐሬሽኖች አብዛኛው የአሸባሪው ኃይል ከመቼውም ጊዜ በላይ እንዲበተን ተደርጓል " ያለ ሲሆን አስቀድሞ ነጻ በወጡት በምሥራቅ፣ በምዕራብና በመሐል ግንባር በሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች መንግሥታዊ አስተዳደር ተመልሶ በመደራጀት ሥራውን ጀምሯል ብሏል።
@tikvahethiopia
ዕለታዊ የኮቪድ-19 ሪፖርት #Ethiopia ፦
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 7 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 6,125 የላብራቶሪ ምርመራ 144 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።
የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 214 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily
@tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 7 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 6,125 የላብራቶሪ ምርመራ 144 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።
የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 214 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily
@tikvahethiopia
" አደጋው ዛሬ የተፈጠረ በማስመሰል የሃሰት እና የሽብር መረጃ ለማህበረሰቡ የማዛመት ስራ እየተሰራ ነው " - አንበሳ የከተማ አውቶቡስ
አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ማምሻውን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የድርጅቱ አውቶብስ ላይ አደጋ መድረሱንና የሰው ህይወት ማለፉን የሚገልፅ የሃሰት መረጃ እየተሰራጨ እንደሚገኝ አሳውቋል።
ድርጅቱ ፥ " መረጃው ከእውነት የራቀ እና ከሁለት አመታት በፊት የተፈጠረውን አደጋ ዛሬ የተፈጠረ በማስመሰል የሃሰት እና የሽብር መረጃ ለማህበረሰቡ የማዛመት ስራ እየተሰራ ነው፤ ማህበረሰቡም ይህን እንዲያውቅ " ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
ከዚህ በተጨማሪ ሀገሪቱ የገጠማትን ፈተና የተዛባ መረጃ በመንዛት ግጭቱን ለማባባስና የሃሰት ወሬዎችን በማናፈስ ሁከት ለመፍጠር የሚጥሩ በርካታ ግለሰቦችም ሆነ ሚዲያዎች ስላሉ ሁሉም ሰው ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ከማጋራትም ሆነ በመረጃዎቹ ከመረበሽ መቆጠብ አለበት ብሏል።
አላስፈላጊ ሽብር ለመፍጠር የሃሰት መረጃ የሚያሰራጩ ሚዲያዎችም ሆነ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ማምሻውን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የድርጅቱ አውቶብስ ላይ አደጋ መድረሱንና የሰው ህይወት ማለፉን የሚገልፅ የሃሰት መረጃ እየተሰራጨ እንደሚገኝ አሳውቋል።
ድርጅቱ ፥ " መረጃው ከእውነት የራቀ እና ከሁለት አመታት በፊት የተፈጠረውን አደጋ ዛሬ የተፈጠረ በማስመሰል የሃሰት እና የሽብር መረጃ ለማህበረሰቡ የማዛመት ስራ እየተሰራ ነው፤ ማህበረሰቡም ይህን እንዲያውቅ " ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
ከዚህ በተጨማሪ ሀገሪቱ የገጠማትን ፈተና የተዛባ መረጃ በመንዛት ግጭቱን ለማባባስና የሃሰት ወሬዎችን በማናፈስ ሁከት ለመፍጠር የሚጥሩ በርካታ ግለሰቦችም ሆነ ሚዲያዎች ስላሉ ሁሉም ሰው ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ከማጋራትም ሆነ በመረጃዎቹ ከመረበሽ መቆጠብ አለበት ብሏል።
አላስፈላጊ ሽብር ለመፍጠር የሃሰት መረጃ የሚያሰራጩ ሚዲያዎችም ሆነ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
@tikvahethiopia