Ethiopian Human Rights Commission - 1.pdf
265.7 KB
ኢሰመኮ፦
የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ ከአዋጁ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን አያያዝ የእስር ሁኔታና የታሳሪዎችን ሁኔታ ለመከታተል በሚያስችለው መልኩ መረጃ ማሰባበሰብ አለመቻሉን አሳውቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ እና በየካ ክ/ ከተሞች የሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎችንና ማቆያዎችን ጎብኝቷል፤ ታሳሪዎችንና ቤተሰቦቻቸውን አነጋግሯል፤ በክፍለ ከተማና በወረዳ ደረጃ ካሉ ከፖሊስ አባላት እና አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ መረጃዎችን አሰባስቧል፡፡
በአንጻሩ የአዲስ ከተማ፣ የልደታ፣ የጉለሌ፣ የቦሌ እና የአራዳ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች ከበላይ ትእዛዝ ካልመጣልን መረጃ አንሰጥም፣ እስረኛም መጎብኘት አትችሉም በማለታቸው ኮሚሽኑ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር እና ኃላፊነት እንዳይወጣ ምክንያት ሆነዋል፡፡
በኮሚሽኑ ክትትል የታሰሩ ሰዎችን ብዛት በሚመለከት የተሟላ መረጃ ለማግኘት እንዳልቻለ አሳውቋል።
ኮሚሽኑ በአንጻራዊነት የተሟላ መረጃ ያገኘው ከቂርቆስ ክ/ከተማ ሲሆን መረጃው በተሰጠበት ኅዳር 2/2014 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ 714 ሰዎች መታሰራቸውንና ከነዚህ ውስጥ 124ቱ ሴቶች እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
በሌሎች ክ/ከተሞች በተመሳሳይ ሁኔታ እስሮች ሲከናወኑ ስለነበርና በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሂደት አሁንም የቀጠለ በመሆኑ በአዲስ አበባ ብቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መታሰራቸው ይገመታል።
በድሬዳዋ ደግሞ እስከ 300 የሚሆኑ ሰዎች ታስረዋል።
የተወሰኑ ሰዎች በሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት መረጃ መሰረት የሚታሰሩ ሲሆን አብዛኛዎቹ ግን ከህብረተሰቡ ተገኘ በተባለ ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር እንደሚውሉና ከመካከላቸው የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ሰዎች ብዛት ከፍተኛ ነው።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል (PDF)
@tikvahethiopia
የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ ከአዋጁ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን አያያዝ የእስር ሁኔታና የታሳሪዎችን ሁኔታ ለመከታተል በሚያስችለው መልኩ መረጃ ማሰባበሰብ አለመቻሉን አሳውቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ እና በየካ ክ/ ከተሞች የሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎችንና ማቆያዎችን ጎብኝቷል፤ ታሳሪዎችንና ቤተሰቦቻቸውን አነጋግሯል፤ በክፍለ ከተማና በወረዳ ደረጃ ካሉ ከፖሊስ አባላት እና አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ መረጃዎችን አሰባስቧል፡፡
በአንጻሩ የአዲስ ከተማ፣ የልደታ፣ የጉለሌ፣ የቦሌ እና የአራዳ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች ከበላይ ትእዛዝ ካልመጣልን መረጃ አንሰጥም፣ እስረኛም መጎብኘት አትችሉም በማለታቸው ኮሚሽኑ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር እና ኃላፊነት እንዳይወጣ ምክንያት ሆነዋል፡፡
በኮሚሽኑ ክትትል የታሰሩ ሰዎችን ብዛት በሚመለከት የተሟላ መረጃ ለማግኘት እንዳልቻለ አሳውቋል።
ኮሚሽኑ በአንጻራዊነት የተሟላ መረጃ ያገኘው ከቂርቆስ ክ/ከተማ ሲሆን መረጃው በተሰጠበት ኅዳር 2/2014 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ 714 ሰዎች መታሰራቸውንና ከነዚህ ውስጥ 124ቱ ሴቶች እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
በሌሎች ክ/ከተሞች በተመሳሳይ ሁኔታ እስሮች ሲከናወኑ ስለነበርና በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሂደት አሁንም የቀጠለ በመሆኑ በአዲስ አበባ ብቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መታሰራቸው ይገመታል።
በድሬዳዋ ደግሞ እስከ 300 የሚሆኑ ሰዎች ታስረዋል።
የተወሰኑ ሰዎች በሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት መረጃ መሰረት የሚታሰሩ ሲሆን አብዛኛዎቹ ግን ከህብረተሰቡ ተገኘ በተባለ ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር እንደሚውሉና ከመካከላቸው የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ሰዎች ብዛት ከፍተኛ ነው።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል (PDF)
@tikvahethiopia
#Somalia #Ethiopia #Sudan #SouthSudan
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን እና የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ባሉ አሁናዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ላይ ተወያይተዋል።
ውይይቱን በተመለከተ አንቶኒ ብሊንከን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ ፥ ውጤታማ ውይይት መደረጉን ገልፀዋል ።
ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በበኩላቸው ቀጠናዊ ሰላም እና ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በሌሎችም ቀጠናዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ከአንቶኒ ብሊንከን ጋር መወያየታቸውን በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።
ዶ/ር ወርቅነህ ፥ " በቀጣይም ከአሜሪካ ጋር በበርካታ ዘርፎች አብረን እንሰራለን " ያሉ ሲሆን " አሜሪካ የኢጋድ ወሳኝ አጋር ናት "ብለዋል።
Photo : Secretary Antony Blinken
@tikvahethiopia
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን እና የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ባሉ አሁናዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ላይ ተወያይተዋል።
ውይይቱን በተመለከተ አንቶኒ ብሊንከን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ ፥ ውጤታማ ውይይት መደረጉን ገልፀዋል ።
ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በበኩላቸው ቀጠናዊ ሰላም እና ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በሌሎችም ቀጠናዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ከአንቶኒ ብሊንከን ጋር መወያየታቸውን በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።
ዶ/ር ወርቅነህ ፥ " በቀጣይም ከአሜሪካ ጋር በበርካታ ዘርፎች አብረን እንሰራለን " ያሉ ሲሆን " አሜሪካ የኢጋድ ወሳኝ አጋር ናት "ብለዋል።
Photo : Secretary Antony Blinken
@tikvahethiopia
👍1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Attention ከአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ (ፎርጅድ) እና መታወቂያ ለማይገባው ሰው የሰጠ ከ3 እስከ 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ በመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ውይይት አድርጓል። በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም እና…
#Attention
(ከአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የተላከ)
በህገ ወጥ መንገድ የተዘጋጀ ( #ፎርጅድ ) መታወቂያ ይዞ መንቀሳቀስ ከ3 - 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በላከልን የፁሁፍ መልዕክት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
(ከአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የተላከ)
በህገ ወጥ መንገድ የተዘጋጀ ( #ፎርጅድ ) መታወቂያ ይዞ መንቀሳቀስ ከ3 - 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በላከልን የፁሁፍ መልዕክት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
👍1
የልዩ ዕድል ሎተሪ የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች ፦
1ኛ. 20,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 1535477
2ኛ. 10,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0165840
3ኛ. 5,000,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0411256
4ኛ. 3,000,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1543809
5ኛ. 1,500,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 0503560
6ኛ. 750,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0837825
7ኛ. 300,000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 1907437
8ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 20,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 30688
9ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 10,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 02294
10ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 5,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 96608
11ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 3696
12ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 5789
13ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 846
14ኛ. 20,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 300 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 67
15ኛ. 200,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 4 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡
ምንጭ፦ ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር
@tikvahethiopia
1ኛ. 20,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 1535477
2ኛ. 10,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0165840
3ኛ. 5,000,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0411256
4ኛ. 3,000,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1543809
5ኛ. 1,500,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 0503560
6ኛ. 750,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0837825
7ኛ. 300,000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 1907437
8ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 20,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 30688
9ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 10,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 02294
10ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 5,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 96608
11ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 3696
12ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 5789
13ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 846
14ኛ. 20,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 300 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 67
15ኛ. 200,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 4 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡
ምንጭ፦ ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር
@tikvahethiopia
👍6❤1
#AddisAbaba
4 ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ በንብረት ግምጃ ቤት ውስጥ የተቀመጡ ከ 1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
ህዳር 8 ቀን 2014 ዓ/ም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ በህዝብ ጥቆማ እና ፖሊስ ባደረገው ብርበራ ከ1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
በቤተ ክህነቱ ግቢ በሚገኝ የንብረት ግምጃ ቤት በሚገኝ የፅህፈት እና የፅዳት እቃዎች ማስቀመጫ ውስጥ በተደረገው ብርበራ የተገኙት 1ሺህ 363 የብሬን እና 493 የሽጉጥ ጥይቶች ናቸው፡፡
በተጨማሪም 2 የጥይት ማስቀመጫ ሳጥኖች እና 1 የክላሽን-ኮቭ ጠብመንጃ ካዝና ተይዟል፡፡
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 1 ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ ሲሆን ህብረተሰቡ በስልክ፣ በአካል እና ሌሎች የመገናኛ አማራጮችን በመጠቀም እየሰጠ የሚገኘው ጥቆማ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ፥ " አሸባሪው የህወሃት ቡድን ለሽብር ተግባሩ የሚጠቀምባቸውን የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በተለያዩ የኃይማኖት ተቋማት ውስጥ ሲያከማች እና በኃይማኖት ሽፋን የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ግለሰቦችን በተላላኪነት እያሰማራ በበርካታ ንፁሃን ላይ አሰቃቂ እልቂት ሲፈፅም እንደቆየ ይታወሳል " ብሏል።
@tikavhethiopia
4 ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ በንብረት ግምጃ ቤት ውስጥ የተቀመጡ ከ 1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
ህዳር 8 ቀን 2014 ዓ/ም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ በህዝብ ጥቆማ እና ፖሊስ ባደረገው ብርበራ ከ1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
በቤተ ክህነቱ ግቢ በሚገኝ የንብረት ግምጃ ቤት በሚገኝ የፅህፈት እና የፅዳት እቃዎች ማስቀመጫ ውስጥ በተደረገው ብርበራ የተገኙት 1ሺህ 363 የብሬን እና 493 የሽጉጥ ጥይቶች ናቸው፡፡
በተጨማሪም 2 የጥይት ማስቀመጫ ሳጥኖች እና 1 የክላሽን-ኮቭ ጠብመንጃ ካዝና ተይዟል፡፡
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 1 ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ ሲሆን ህብረተሰቡ በስልክ፣ በአካል እና ሌሎች የመገናኛ አማራጮችን በመጠቀም እየሰጠ የሚገኘው ጥቆማ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ፥ " አሸባሪው የህወሃት ቡድን ለሽብር ተግባሩ የሚጠቀምባቸውን የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በተለያዩ የኃይማኖት ተቋማት ውስጥ ሲያከማች እና በኃይማኖት ሽፋን የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ግለሰቦችን በተላላኪነት እያሰማራ በበርካታ ንፁሃን ላይ አሰቃቂ እልቂት ሲፈፅም እንደቆየ ይታወሳል " ብሏል።
@tikavhethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Sidama ከነገ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የሰአት እላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ክልከላዎች ተላለፉ። የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል። በዚህ መሰረት ፦ - ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ…
#Oromia
በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚኖረውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ሲባል በክልሉ የሰዎችና ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ መነሳቱ ተገልጿል።
የክልሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሰዎችም ሆኑ ተሸከርካሪዎች ሕግና ስርዓትን አክብረው በማንኛውም ሰዓት መንቀሳቀስ እንደሚችሉ አሳውቋል።
በተለያዩ ቦታዎች ላይ ፍተሻዎች ስለሚኖሩ ማንኛውም በክልሉ የሚዘዋወር ሰው መታወቂያ መያዝ እንዳለበት ማሳሰቢያ ተላልፏል።
#ኢብኮ
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚኖረውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ሲባል በክልሉ የሰዎችና ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ መነሳቱ ተገልጿል።
የክልሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሰዎችም ሆኑ ተሸከርካሪዎች ሕግና ስርዓትን አክብረው በማንኛውም ሰዓት መንቀሳቀስ እንደሚችሉ አሳውቋል።
በተለያዩ ቦታዎች ላይ ፍተሻዎች ስለሚኖሩ ማንኛውም በክልሉ የሚዘዋወር ሰው መታወቂያ መያዝ እንዳለበት ማሳሰቢያ ተላልፏል።
#ኢብኮ
@tikvahethiopia
👍3
" የትምህርት ስራ ከብሔርና ከፖለቲካ ነፃ ማድረግ ይገባል " ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ማህብርሰብ ጋር እየተወያዩ ነው ።
ሚኒስተሩ ከዩንቨርስቲው ማህበረሰብ ጋር የሚደርጉት ውይይት የአዲስአበባ ዮንቨርስቲን ችግሩች ለመፍታትና በቀጠይ የዩንቨርስቲውን አቅም ለማሳደግ ስራ ለመስራት እንደሆነ ተገልጿል።
ፕ/ር ብርሃኑ ፤ የትምህርት ስራ ከብሔርና ከፖለቲካ ነፃ ማድረግ እንደሚገባ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል።
በውይይት መድረኩ ከዩንቨርስቲው የተለያዩ የትምህርት ክፍል የመጡ ተወካዩች ለትምህርት ሚኒስተሩ በቀጣይ መደርግ ያለባቸውን እና የነበሩ ከፍተቶች ተነስቷል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን(ጋዜጠኛ ነፃነት ጌታቸው)
@tikvahethiopia
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ማህብርሰብ ጋር እየተወያዩ ነው ።
ሚኒስተሩ ከዩንቨርስቲው ማህበረሰብ ጋር የሚደርጉት ውይይት የአዲስአበባ ዮንቨርስቲን ችግሩች ለመፍታትና በቀጠይ የዩንቨርስቲውን አቅም ለማሳደግ ስራ ለመስራት እንደሆነ ተገልጿል።
ፕ/ር ብርሃኑ ፤ የትምህርት ስራ ከብሔርና ከፖለቲካ ነፃ ማድረግ እንደሚገባ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል።
በውይይት መድረኩ ከዩንቨርስቲው የተለያዩ የትምህርት ክፍል የመጡ ተወካዩች ለትምህርት ሚኒስተሩ በቀጣይ መደርግ ያለባቸውን እና የነበሩ ከፍተቶች ተነስቷል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን(ጋዜጠኛ ነፃነት ጌታቸው)
@tikvahethiopia
👍3
ችሎት !
አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ እንዲገደል የግድያ ቦታ አመቻችታለች ተብላ የተከሰሰችው ላምሮት ከማል በተሻሻለው አንቀጽ በ5 ሺህ ብር ዋስትና እንድትወጣ ታዘዘ።
የዋስትና ትዛዙን የሰጠው የከፍተኛው ፍርድ ቤት 2ኛ የፀረሽብርና የህገመንግስት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
ፍርድ ቤቱ በወንጀለኛ መቅጫ ስነስርአት ህግ 113 ንዑስ ቁጥር 2 መሰረት የጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት የተከሰሰችበት የሽብር ወንጀል አንቀጽን በማሻሻል በቸልተኝነት የሚፈጸም የወንጀል ህግ አንቀጽ 575 መሰረት እንድትከላከል በተሰጠ ውሳኔ መነሻ አንቀጹ ዋስትና አያስከለክም ሲል ነው ዋስትና የተፈቀደላት።
ፍርድ ቤት በዚህ አንቀጽ የመከላከያ ማስረጃዋን ለመመልከት ለህዳር 23 እና 24 ቀን 2014ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።
የመረጃ ባለቤት ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ እንዲገደል የግድያ ቦታ አመቻችታለች ተብላ የተከሰሰችው ላምሮት ከማል በተሻሻለው አንቀጽ በ5 ሺህ ብር ዋስትና እንድትወጣ ታዘዘ።
የዋስትና ትዛዙን የሰጠው የከፍተኛው ፍርድ ቤት 2ኛ የፀረሽብርና የህገመንግስት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
ፍርድ ቤቱ በወንጀለኛ መቅጫ ስነስርአት ህግ 113 ንዑስ ቁጥር 2 መሰረት የጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት የተከሰሰችበት የሽብር ወንጀል አንቀጽን በማሻሻል በቸልተኝነት የሚፈጸም የወንጀል ህግ አንቀጽ 575 መሰረት እንድትከላከል በተሰጠ ውሳኔ መነሻ አንቀጹ ዋስትና አያስከለክም ሲል ነው ዋስትና የተፈቀደላት።
ፍርድ ቤት በዚህ አንቀጽ የመከላከያ ማስረጃዋን ለመመልከት ለህዳር 23 እና 24 ቀን 2014ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።
የመረጃ ባለቤት ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
👍2
#Ethiopia
የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ ልኡክ ጄፈሪ ፊልትማን ጋር መወያየታቸውን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ይፋ ባደረገው መረጃ ፤ በውይይቱ ወቅት ከአሸባሪው ሕወሐት ጋር የሚደረገው ጦርነት ስለሚቆምበት መንገድ የአሜሪካ ሐሳብ ምን እንደሆነ በልዩ ልኡኩ በኩል የተነሣ ሲሆን፣ አቶ ደመቀ የኢትዮጵያን አቋም አስረድተዋል።
አቶ ደመቀ መኮንን #በኮምቦልቻ እና #በላሊበላ ለሰብአዊ ርዳታ የሚውሉ በረራዎች መፈቀዳቸውን የገለፁ ሲሆን ወደ ትግራይም 369 ርዳታ የጫኑ መኪናዎች እንዲገቡ መፈቀዱን ገልፀዋል።
በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎችን ሁኔታ በተመለከተም ውይይት አድርገዋል።
አቶ ደመቀ ፥ " አሸባሪው ሕወሐት አሁንም ቢሆን በአፋርና በአማራ ክልሎች ጥቃት እየፈጸመና ከፍተኛ ሰብአዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድመት እንዲሁም ሥነ ልቡናዊ ጉዳት እያደረሰ ነው " ያሉ ሲሆን ህወሓት ከሁለቱ ክልሎች ለቅቆ እንዲወጣ ግፊት ሊደረግበት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ ልኡክ ጄፈሪ ፊልትማን ጋር መወያየታቸውን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ይፋ ባደረገው መረጃ ፤ በውይይቱ ወቅት ከአሸባሪው ሕወሐት ጋር የሚደረገው ጦርነት ስለሚቆምበት መንገድ የአሜሪካ ሐሳብ ምን እንደሆነ በልዩ ልኡኩ በኩል የተነሣ ሲሆን፣ አቶ ደመቀ የኢትዮጵያን አቋም አስረድተዋል።
አቶ ደመቀ መኮንን #በኮምቦልቻ እና #በላሊበላ ለሰብአዊ ርዳታ የሚውሉ በረራዎች መፈቀዳቸውን የገለፁ ሲሆን ወደ ትግራይም 369 ርዳታ የጫኑ መኪናዎች እንዲገቡ መፈቀዱን ገልፀዋል።
በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎችን ሁኔታ በተመለከተም ውይይት አድርገዋል።
አቶ ደመቀ ፥ " አሸባሪው ሕወሐት አሁንም ቢሆን በአፋርና በአማራ ክልሎች ጥቃት እየፈጸመና ከፍተኛ ሰብአዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድመት እንዲሁም ሥነ ልቡናዊ ጉዳት እያደረሰ ነው " ያሉ ሲሆን ህወሓት ከሁለቱ ክልሎች ለቅቆ እንዲወጣ ግፊት ሊደረግበት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
👍1
#Adama
ሀሰተኛ መታወቂያ ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦች በእስራት እና በገንዘብ ተቀጡ።
በአዲስ አበባ እና በአዳማ ከተማ በተለያዩ ቀበሌዎች ስም በተዘጋጁ ሀሰተኛ መታወቂያ ሲንቀሳቀሱ የተያዙ 13 ሰዎች በእስራት እና በገንዘብ ተቀጡ።
የአዳማ ከተማ ፖሊስ የመረጃ ባለሞያ ረ/ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 በሰጡት ቃል በእስራት እና በገንዘብ የተቀጡት በአዲስ አበባ ቀበሌዎች ስም ሀሰተኛ መታወቂያ ያሰሩት 10 ግለሰቦች በአዳማ ከተማ ቀበሌዎች ስም ሀሰተኛ መታወቂያ ያሰሩ 3 ግለሰቦች ናቸው።
ረ/ኢኒስፔክተር ወርቅነሽ አሁን ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር እና ፍተሻ ግለሰቦቹ ሊያዙ መቻላቸውን ገልፀዋል።
በአዳማ ቦኩ ክ/ከተማ ልዩ ቦታው " ባቡር ጣቢያ " አካባቢአንደኛ ተከሳሽ (ወንድ)፣ ሁለተኛ ተከሳሽ (ወንድ) እና ሶስተኛ ተከሳሽ (ሴት) በህገወጥ መንገድ በተዘጋጀ መታወቂያ ወደ ድሬዳዋ ሊንቀሳቀሱ ሲሉ ተይዘዋል።
ሀሰተኛ መታወቂያው በቦሌ ክ/ከተማ ጠገቻ አራራ ቀበሌ ስም የተዘጋጀ እና ግለሰቦቹ በገንዘብ ያወጡት መሆኑና ቀበሌውን ሆነ አካባቢውን እንደማያውቁት ረ/ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ተናግረዋል።
አዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡት ሶስቱ ግለሰቦች ፍርድ ቤት በሰነድ እና በሰው ማስረጃ ተረጋገጦ የቀረበለትን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ ትላንት እያንዳንዳቸው በ3 ዓመት እስራት እና በ1500 ብር የገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል።
በተጨማሪ በህገወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች መታወቂያ በማውጣት ወደ ሀረር ነው የምንጓዘው በሚል 10 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው መዝገባቸው ሲጣራ ቆይቶ እያንዳዳቸው በ4 ዓመት እስራት እና በ5 ሺህ ገንዘብ ተቀጥተዋል።
@tikvahethiopia
ሀሰተኛ መታወቂያ ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦች በእስራት እና በገንዘብ ተቀጡ።
በአዲስ አበባ እና በአዳማ ከተማ በተለያዩ ቀበሌዎች ስም በተዘጋጁ ሀሰተኛ መታወቂያ ሲንቀሳቀሱ የተያዙ 13 ሰዎች በእስራት እና በገንዘብ ተቀጡ።
የአዳማ ከተማ ፖሊስ የመረጃ ባለሞያ ረ/ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 በሰጡት ቃል በእስራት እና በገንዘብ የተቀጡት በአዲስ አበባ ቀበሌዎች ስም ሀሰተኛ መታወቂያ ያሰሩት 10 ግለሰቦች በአዳማ ከተማ ቀበሌዎች ስም ሀሰተኛ መታወቂያ ያሰሩ 3 ግለሰቦች ናቸው።
ረ/ኢኒስፔክተር ወርቅነሽ አሁን ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር እና ፍተሻ ግለሰቦቹ ሊያዙ መቻላቸውን ገልፀዋል።
በአዳማ ቦኩ ክ/ከተማ ልዩ ቦታው " ባቡር ጣቢያ " አካባቢአንደኛ ተከሳሽ (ወንድ)፣ ሁለተኛ ተከሳሽ (ወንድ) እና ሶስተኛ ተከሳሽ (ሴት) በህገወጥ መንገድ በተዘጋጀ መታወቂያ ወደ ድሬዳዋ ሊንቀሳቀሱ ሲሉ ተይዘዋል።
ሀሰተኛ መታወቂያው በቦሌ ክ/ከተማ ጠገቻ አራራ ቀበሌ ስም የተዘጋጀ እና ግለሰቦቹ በገንዘብ ያወጡት መሆኑና ቀበሌውን ሆነ አካባቢውን እንደማያውቁት ረ/ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ተናግረዋል።
አዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡት ሶስቱ ግለሰቦች ፍርድ ቤት በሰነድ እና በሰው ማስረጃ ተረጋገጦ የቀረበለትን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ ትላንት እያንዳንዳቸው በ3 ዓመት እስራት እና በ1500 ብር የገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል።
በተጨማሪ በህገወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች መታወቂያ በማውጣት ወደ ሀረር ነው የምንጓዘው በሚል 10 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው መዝገባቸው ሲጣራ ቆይቶ እያንዳዳቸው በ4 ዓመት እስራት እና በ5 ሺህ ገንዘብ ተቀጥተዋል።
@tikvahethiopia
👍3