TIKVAH-ETHIOPIA
#EMA የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለሚዲያዎች የሰጡት ቃለምልልስ ከምርጫ በፊት እንዳይሰራጭ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አሳሰበ። ቃለምልልሱ በዚህ በጥሞና ወቅት መተላለፍ የለበትም ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ እድሪስ ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፥ ምንም እንኳን ቃለ መጠይቁ የመንግስት የስራ ክንውኖች ላይ ያተኮረና…
#Update
የታገደው የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ቃለምልልስ ዛሬ ይሰራጫል ተብሏል።
የ "ጥሞና ወቅት" ላይ እንዳይተላለፍ የተባለው የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ቃለ ምልልስ ዛሬ ምሽት 3 ሰዓት ላይ ነው በተለያዩ ሚዲያዎች ይተላለፋል የተባለው።
ቃለምልልሱ ዛሬ እንደሚተላለፍ የሰማነው ከጠ/ሚር ፅ/ቤት ይፋዊ ከሆነው የፌስቡክ ገፅ ላይ ነው።
ይህ ቃለምልልስ ፥ ከምርጫ በፊት እንዳይሰራጭ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አሳስቦ እንደነበር አይዘነጋም።
በወቅቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ቃለ መጠይቁ የመንግስት የስራ ክንውኖች ላይ ያተኮረ እና የምርጫ ቅስቀሳ እንዳልሆነ በመግለፅ ነገር ግን በጥሞና ወቅት ሊተላለፍ አይገባም ሲል ማሳሰቢያ ሰጥቶ ቃለምልልሱን ለማሳተላለፍ ማስታወቂያ ሲያስነግሩ የነበሩ ሚዲያዎች በሙሉ ማስታወቂያውን አቁመው ነበር።
@tikvahethiopia
የታገደው የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ቃለምልልስ ዛሬ ይሰራጫል ተብሏል።
የ "ጥሞና ወቅት" ላይ እንዳይተላለፍ የተባለው የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ቃለ ምልልስ ዛሬ ምሽት 3 ሰዓት ላይ ነው በተለያዩ ሚዲያዎች ይተላለፋል የተባለው።
ቃለምልልሱ ዛሬ እንደሚተላለፍ የሰማነው ከጠ/ሚር ፅ/ቤት ይፋዊ ከሆነው የፌስቡክ ገፅ ላይ ነው።
ይህ ቃለምልልስ ፥ ከምርጫ በፊት እንዳይሰራጭ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አሳስቦ እንደነበር አይዘነጋም።
በወቅቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ቃለ መጠይቁ የመንግስት የስራ ክንውኖች ላይ ያተኮረ እና የምርጫ ቅስቀሳ እንዳልሆነ በመግለፅ ነገር ግን በጥሞና ወቅት ሊተላለፍ አይገባም ሲል ማሳሰቢያ ሰጥቶ ቃለምልልሱን ለማሳተላለፍ ማስታወቂያ ሲያስነግሩ የነበሩ ሚዲያዎች በሙሉ ማስታወቂያውን አቁመው ነበር።
@tikvahethiopia
"Maal Mallisaa"
ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ከመሞቱ በፊት ሰርቶ ያጠናቀቀው 3ኛ አልበሙ ሊወጣ እየተጠናቀቀ መሆኑ ተሰምቷል።
የአዲሱ አልበም ማስታወቂያዎች በመዲናችን አዲስ አበባ እየተለጠፉ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአልበሙን መውጣት በሚጠባበቁት ዘንድ ልዩ ትኩረትን ስቧል።
የአልበሙ ስያሜ "Maal Mallisaa" እንደሚሰኝም ታውቋል።
የአዲሱ አልበም መውጫ ቀን መቼ ነው? የሚለው ለጊዜው ትክክለኛው ቀን አልታወቀም።
ድምፃዊ ሃጫሉ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ/ም ምሽት መገደሉ ይታወሳል።
ከወራት በፊት #Grammy_Award እ.አ.አ 2020 - 2021 የዓለም የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ካጣቸው አርቲስቶች እና የሙዚቃ ሰዎች ዝርዝር ዉስጥ የሀገራችን ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን አካቶት እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።
Photo Credit : Haacaaluu Hundeessaa (FB Page)
@tikvahethiopia
ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ከመሞቱ በፊት ሰርቶ ያጠናቀቀው 3ኛ አልበሙ ሊወጣ እየተጠናቀቀ መሆኑ ተሰምቷል።
የአዲሱ አልበም ማስታወቂያዎች በመዲናችን አዲስ አበባ እየተለጠፉ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአልበሙን መውጣት በሚጠባበቁት ዘንድ ልዩ ትኩረትን ስቧል።
የአልበሙ ስያሜ "Maal Mallisaa" እንደሚሰኝም ታውቋል።
የአዲሱ አልበም መውጫ ቀን መቼ ነው? የሚለው ለጊዜው ትክክለኛው ቀን አልታወቀም።
ድምፃዊ ሃጫሉ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ/ም ምሽት መገደሉ ይታወሳል።
ከወራት በፊት #Grammy_Award እ.አ.አ 2020 - 2021 የዓለም የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ካጣቸው አርቲስቶች እና የሙዚቃ ሰዎች ዝርዝር ዉስጥ የሀገራችን ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን አካቶት እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።
Photo Credit : Haacaaluu Hundeessaa (FB Page)
@tikvahethiopia
#ምርጫ2013
በ 'ድምጽ መስጫ ወረቀት እጥረት' ምክንያት በጋምቤላ ክልል ባሉ በተወሰኑ ጣቢያዎች ሰኔ 14/2013 ዓ.ም ተቋርጦ የነበረው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ትላንት ተካሂዷል።
የድምፅ ቆጠራው ተጠናቆ ጊዜያዊ ውጤቱ በየምርጫ ጣቢያ ለህዝብ ይፋ እየተደረገ ነው።
ጊዜያዊ ውጤቱ ይፋ እየተደረገ ያለው በሰባት ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች እንደሆነ ተገልጿል።
ድምጽ የተሰጠባቸው ሳጥኖች ወደምርጫ ክልሎች በመጓጓዝ ላይ ይገኛሉ።
መረጃው የኢዜአ ነው።
@tikvahethiopia
በ 'ድምጽ መስጫ ወረቀት እጥረት' ምክንያት በጋምቤላ ክልል ባሉ በተወሰኑ ጣቢያዎች ሰኔ 14/2013 ዓ.ም ተቋርጦ የነበረው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ትላንት ተካሂዷል።
የድምፅ ቆጠራው ተጠናቆ ጊዜያዊ ውጤቱ በየምርጫ ጣቢያ ለህዝብ ይፋ እየተደረገ ነው።
ጊዜያዊ ውጤቱ ይፋ እየተደረገ ያለው በሰባት ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች እንደሆነ ተገልጿል።
ድምጽ የተሰጠባቸው ሳጥኖች ወደምርጫ ክልሎች በመጓጓዝ ላይ ይገኛሉ።
መረጃው የኢዜአ ነው።
@tikvahethiopia
#ምርጫ2013
በቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሰንገን ኦባሳንጆ የሚመራው በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢዎች ቡድን የምርጫ ትዝብቱን #የመጀመሪያ ሪፖርት ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ያቀርባል።
ሪፖርቱን #በቀጥታ በቴሌግራም Voice Chat መከታተል የምትችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
@tikvahethiopia
በቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሰንገን ኦባሳንጆ የሚመራው በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢዎች ቡድን የምርጫ ትዝብቱን #የመጀመሪያ ሪፖርት ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ያቀርባል።
ሪፖርቱን #በቀጥታ በቴሌግራም Voice Chat መከታተል የምትችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
@tikvahethiopia
#LIVE
በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ሪፖርቱን ከስካይ ላይት ሆቴል እያቀረበ ነው።
ከላይ ያለውን Voice Chat 'Join' በማለት በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ።
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ሪፖርቱን ከስካይ ላይት ሆቴል እያቀረበ ነው።
ከላይ ያለውን Voice Chat 'Join' በማለት በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ።
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#LIVE በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ሪፖርቱን ከስካይ ላይት ሆቴል እያቀረበ ነው። ከላይ ያለውን Voice Chat 'Join' በማለት በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ። #TikvahFamily @tikvahethiopia
የAU የመጀመሪያ /ቀዳሚ የምርጫ 2013 ትዝብት ሪፖርት👆
በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን የምርጫ 2013 የመጀመሪያ/ቀዳሚ ሪፖርት ዛሬ አቅርቧል።
ሪፖርቱን የቡድኑ መሪ ኦሊሰንገን ኦባሳንጆ በንባብ አሰምተዋል።
ቡድኑ በ5 ክልሎችና 2 ከተሞች የምርጫውን አባላቱን ልኮ ምርጫውን መታዘቡን አስታውቋል፡፡
በአንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች እንግልትና ወከባ ፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ስጋቶች ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችን የማዋከብና የማንገላታት ችግሮች ፣ የቁሳቁስ እጥረት ችግር ምርጫው ላይ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አሳውቋል።
ከዚህ በተረፈ ግን ምርጫው ሰላማዊ ፣ ተአማኒ በሆነ ሁኔታ መከናወኑን ገልጿል።
የምርጫ ውጤት በሚመለከተው አካል ይፋ እስኪሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲጠባበቅ ቡድኑ ጥሪ አቅርቧል።
ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን የምርጫ 2013 የመጀመሪያ/ቀዳሚ ሪፖርት ዛሬ አቅርቧል።
ሪፖርቱን የቡድኑ መሪ ኦሊሰንገን ኦባሳንጆ በንባብ አሰምተዋል።
ቡድኑ በ5 ክልሎችና 2 ከተሞች የምርጫውን አባላቱን ልኮ ምርጫውን መታዘቡን አስታውቋል፡፡
በአንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች እንግልትና ወከባ ፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ስጋቶች ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችን የማዋከብና የማንገላታት ችግሮች ፣ የቁሳቁስ እጥረት ችግር ምርጫው ላይ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አሳውቋል።
ከዚህ በተረፈ ግን ምርጫው ሰላማዊ ፣ ተአማኒ በሆነ ሁኔታ መከናወኑን ገልጿል።
የምርጫ ውጤት በሚመለከተው አካል ይፋ እስኪሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲጠባበቅ ቡድኑ ጥሪ አቅርቧል።
ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የ40/60 መቶ በመቶ ከፋዮች ተፈረደላቸው።
40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መቶ በመቶ የከፈሉ ከ700 በላይ ተመዝጋቢዎች ተወሰነላቸው።
በቀድሞ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም እጣ የወጣባቸው የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፣ መቶ በመቶ ክፍያ የፈጸሙ ቅድሚያ ለነሱ ሳይሰጥ እጣ መውጣቱን በመቃወም በፍርድ ቤት አሳግደው ነበር።
ሲከራከሩ ከርመው ዛሬ ሰኔ 16 ቀን 2013 ዓ.ም የታገደው ቤት እንዲሰጣቸው ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tikvahethiopia
40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መቶ በመቶ የከፈሉ ከ700 በላይ ተመዝጋቢዎች ተወሰነላቸው።
በቀድሞ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም እጣ የወጣባቸው የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፣ መቶ በመቶ ክፍያ የፈጸሙ ቅድሚያ ለነሱ ሳይሰጥ እጣ መውጣቱን በመቃወም በፍርድ ቤት አሳግደው ነበር።
ሲከራከሩ ከርመው ዛሬ ሰኔ 16 ቀን 2013 ዓ.ም የታገደው ቤት እንዲሰጣቸው ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tikvahethiopia
#ሪፖርት
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን በተመለከተ ቃላቸውን ሰጥተውናል።
በአጠቅላይ ምርጫው ሰላማዊ መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ፣ የተለያየ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውድድሩን ህግ በማክበር ፍፁም ነው ባይባልም የተሻለ ውድድር ስሜት የተፈጠረበት እና የህዝብ መነሳሳት የታየበት አበረታች የሚባል ሂደት ነበር ብለዋል።
ነገር ግን ምርጫው እንከን አልባ እና ፍፁም ነበር ማለት እንዳልሆነ ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ አሳውቀውናል።
ምርጫው ላይ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ እንደሆነም አንስተዋል።
ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ ፥ "የትኛውም ምርጫ ፍፁም ሆኖም አያውቅም፣ ሊሆንም አይችልም፤ ምርጫ ሂደት ነው የምንማርበት ነው ከዚህ ምርጫ የተሻለ አፈፃፀም ደግሞ በሚቀጥለው ይታያል ብዬ አስባለሁ" ብለዋል።
* የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን በተመለከተ ቃላቸውን ሰጥተውናል።
በአጠቅላይ ምርጫው ሰላማዊ መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ፣ የተለያየ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውድድሩን ህግ በማክበር ፍፁም ነው ባይባልም የተሻለ ውድድር ስሜት የተፈጠረበት እና የህዝብ መነሳሳት የታየበት አበረታች የሚባል ሂደት ነበር ብለዋል።
ነገር ግን ምርጫው እንከን አልባ እና ፍፁም ነበር ማለት እንዳልሆነ ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ አሳውቀውናል።
ምርጫው ላይ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ እንደሆነም አንስተዋል።
ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ ፥ "የትኛውም ምርጫ ፍፁም ሆኖም አያውቅም፣ ሊሆንም አይችልም፤ ምርጫ ሂደት ነው የምንማርበት ነው ከዚህ ምርጫ የተሻለ አፈፃፀም ደግሞ በሚቀጥለው ይታያል ብዬ አስባለሁ" ብለዋል።
* የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia