TIKVAH-ETHIOPIA
#ADAMA #BAHIRDAR ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራውን በባሕር ዳር እና በአዳማ ከተሞች ጀምሯል። ይህ የደንበኞች ሙከራ ከድሬዳዋ፣ ሐረር እና ሐረማያ በመቀጠል የሳፋሪኮምን ኔትወርክ ለመሞከር ባሕር ዳርን እና አዳማን 4ኛ እና 5ኛ የኢትዮጵያ ከተሞች አድርጓቸዋል። የሲም ካርድ ሽያጭ ምዝገባ፣ የአየር ሰዓት እና የስልክ ቀፎዎች ግዢ እንዲሁም የደንበኞች…
#Bishoftu #Mojo #Debrebrihan
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራውን በቢሾፍቱ፣ ሞጆ እና ደብረ ብርሃን ከተሞች መጀመሩን አሳውቋል።
ይህ የደንበኞች ሙከራ የሳፋሪኮምን ኔትወርክ እየሞከሩ ያሉትን ከተሞች ቁጥር #ስምንት የሚያደርሰው ሲሆን ባለፉት ሦስት ሳምንታት ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሐረማያ፣ ባሕር ዳር እና አዳማ ላይ ሙከራው መጀመሩ ይታወቃል።
ደንበኞች የሲም ካርድ ሽያጭ ምዝገባ፣ የአየር ሰዓት እና የስልክ ቀፎዎች ግዢ እንዲሁም የደንበኞች ድጋፍ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፦
#ቢሾፍቱ 📍
በቢሾፍቱ ሁለት የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈባቸው መደብሮች (ከኦዳ ነቤ ሆቴል ጎን እና ከመዘጋጃው ፊትለፊት)፤
#ሞጆ📍
በሞጆ አንድ መናኸሪያ አካባቢ የሚገኝ የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈበት መደብር፤
#ደብረብርሃን 📍
ከዘርዕ ያዕቆብ አደባባይ ወረድ ብሎ ባለው ኖክ ማደያ አካባቢ የሚገኝ የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈበት መደብር ደንበኞችን ለማገልገል ክፍት መሆኑን ገልጿል።
በቢሾፍቱ፣ በሞጆ እና በደብረ ብርሃን ከተሞች አገልግሎት በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙከራ ኔትወርክ ደንበኞች ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሁፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ እንደሚችሉ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አሳውቆናል።
#SafaricomEthiopia
@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራውን በቢሾፍቱ፣ ሞጆ እና ደብረ ብርሃን ከተሞች መጀመሩን አሳውቋል።
ይህ የደንበኞች ሙከራ የሳፋሪኮምን ኔትወርክ እየሞከሩ ያሉትን ከተሞች ቁጥር #ስምንት የሚያደርሰው ሲሆን ባለፉት ሦስት ሳምንታት ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሐረማያ፣ ባሕር ዳር እና አዳማ ላይ ሙከራው መጀመሩ ይታወቃል።
ደንበኞች የሲም ካርድ ሽያጭ ምዝገባ፣ የአየር ሰዓት እና የስልክ ቀፎዎች ግዢ እንዲሁም የደንበኞች ድጋፍ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፦
#ቢሾፍቱ 📍
በቢሾፍቱ ሁለት የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈባቸው መደብሮች (ከኦዳ ነቤ ሆቴል ጎን እና ከመዘጋጃው ፊትለፊት)፤
#ሞጆ📍
በሞጆ አንድ መናኸሪያ አካባቢ የሚገኝ የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈበት መደብር፤
#ደብረብርሃን 📍
ከዘርዕ ያዕቆብ አደባባይ ወረድ ብሎ ባለው ኖክ ማደያ አካባቢ የሚገኝ የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈበት መደብር ደንበኞችን ለማገልገል ክፍት መሆኑን ገልጿል።
በቢሾፍቱ፣ በሞጆ እና በደብረ ብርሃን ከተሞች አገልግሎት በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙከራ ኔትወርክ ደንበኞች ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሁፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ እንደሚችሉ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አሳውቆናል።
#SafaricomEthiopia
@tikvahethiopia
" ፍትህን እስከምናገኝ ድረስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት እንከፍላለን " - ካውንስሉ
በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ከርስቲያን ኩሪፍቱ ማዕከል ላይ የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ኢ-ህገ መንግስታዊ ጥሰት እየፈጸመ እንደሆነ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል አሳወቀ።
ድርጊቱን በመቃወምም መግለጫ አውጥቷል።
ካውንስሉ ፤ የኩሪፍቱ ማዕከል በህጋዊ መንገድ ለቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ ሰነድ ያለው ይዞታ መሆኑን ገልጿል።
የከተማ አስተዳደሩ ግን ከቤተ ክርስቲያኒቱን ቦታ ላይ 40 ሺህ ካሬ ሜትር የሚሆነውን በኃይል ለሁለት ለግለሰቦች በመስጠት ኢ ህገመንግስታዊ በደል እንደፈጸመ ጠቁሟል።
ይህንን ጉዳይ አስመልከቶ ከዚህ ቀደም ቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዩን ለፍርድ ቤት አቅርባ ፍርድ ቤት ቦታው የቃለ ሕይወት ይዞታ መሆኑን ውሳኔ አስተላልፎ ነበር።
የከተማ አስተዳደሩ የግንባታን ሂደት ሆን ብሎ እያስተጓጎለ ስለነበረ ጉዳዩን ለሚመለከታቸው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና ለፌደራል መንግስት ቀርቦ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ኮሚቴ ተዋቅሮ እየታየ ባለበት ሁኔታ ትላንት ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩ የቤተ ከርስቲያቱ ይዞታ ውስጥ ወታደሮችን እና የመሬት አስተዳደር ባለሙያዎችን ይዞ በመግባት ችካል በማስቀመጥ የቤተ ከርስቲያኒቱን ይዞታ ለግለሰብ በማስተላለፍ ህገ ወጥ ተግባር እንደፈጸመ ካውንስሉ በይፋ አሳውቋል።
ሁኔታው ከባድ እና በወንጌላውያን አምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ ሐይማኖታዊ ጥላቻ ባላቸው ግለሰቦች የተቀነባበረ እንደሆነ ካውንስሉ አመልክቷል።
ጥያቄው ልማት ከሆነ ለምን ቤተ ክርስቲያኒቱ እንድታለማ ቅድሚያ አይሰጣትም ? የሚለው ሐሳብ ላይ መግባባት ኖሮ ቤተ ከርስቲያኒቱ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ሙሉ በሙሉ ጊቢውን ወደ ልማት በመቀየር እየሰራች እንደነበር ተጠቁሟል።
ይህ በሆነት ሁኔታ ነው ለአመታት በይዞታነት የያዘችውን ንብረት በሐይል በመቀማት የተወሰደው።
ካውንስሉ ፤ " የወንጌል አማኞች በዚህ የህልውናችን ጉዳይ ህግ መንግስታዊ መብታችን እስከሚከበር ድረስ ለሚመለከታቸው ለክልሉ እና ለፌደራል መንግስት አካላት ጥያቄያችንን ከማቅረብ ባሻገር ፍትህን እስከምናገኝ ድረስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት እንከፍላለን " ሲል አሳውቋል።
#Bishoftu
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ከርስቲያን ኩሪፍቱ ማዕከል ላይ የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ኢ-ህገ መንግስታዊ ጥሰት እየፈጸመ እንደሆነ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል አሳወቀ።
ድርጊቱን በመቃወምም መግለጫ አውጥቷል።
ካውንስሉ ፤ የኩሪፍቱ ማዕከል በህጋዊ መንገድ ለቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ ሰነድ ያለው ይዞታ መሆኑን ገልጿል።
የከተማ አስተዳደሩ ግን ከቤተ ክርስቲያኒቱን ቦታ ላይ 40 ሺህ ካሬ ሜትር የሚሆነውን በኃይል ለሁለት ለግለሰቦች በመስጠት ኢ ህገመንግስታዊ በደል እንደፈጸመ ጠቁሟል።
ይህንን ጉዳይ አስመልከቶ ከዚህ ቀደም ቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዩን ለፍርድ ቤት አቅርባ ፍርድ ቤት ቦታው የቃለ ሕይወት ይዞታ መሆኑን ውሳኔ አስተላልፎ ነበር።
የከተማ አስተዳደሩ የግንባታን ሂደት ሆን ብሎ እያስተጓጎለ ስለነበረ ጉዳዩን ለሚመለከታቸው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና ለፌደራል መንግስት ቀርቦ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ኮሚቴ ተዋቅሮ እየታየ ባለበት ሁኔታ ትላንት ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩ የቤተ ከርስቲያቱ ይዞታ ውስጥ ወታደሮችን እና የመሬት አስተዳደር ባለሙያዎችን ይዞ በመግባት ችካል በማስቀመጥ የቤተ ከርስቲያኒቱን ይዞታ ለግለሰብ በማስተላለፍ ህገ ወጥ ተግባር እንደፈጸመ ካውንስሉ በይፋ አሳውቋል።
ሁኔታው ከባድ እና በወንጌላውያን አምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ ሐይማኖታዊ ጥላቻ ባላቸው ግለሰቦች የተቀነባበረ እንደሆነ ካውንስሉ አመልክቷል።
ጥያቄው ልማት ከሆነ ለምን ቤተ ክርስቲያኒቱ እንድታለማ ቅድሚያ አይሰጣትም ? የሚለው ሐሳብ ላይ መግባባት ኖሮ ቤተ ከርስቲያኒቱ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ሙሉ በሙሉ ጊቢውን ወደ ልማት በመቀየር እየሰራች እንደነበር ተጠቁሟል።
ይህ በሆነት ሁኔታ ነው ለአመታት በይዞታነት የያዘችውን ንብረት በሐይል በመቀማት የተወሰደው።
ካውንስሉ ፤ " የወንጌል አማኞች በዚህ የህልውናችን ጉዳይ ህግ መንግስታዊ መብታችን እስከሚከበር ድረስ ለሚመለከታቸው ለክልሉ እና ለፌደራል መንግስት አካላት ጥያቄያችንን ከማቅረብ ባሻገር ፍትህን እስከምናገኝ ድረስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት እንከፍላለን " ሲል አሳውቋል።
#Bishoftu
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update! " መሬቱ ጭራሽ በNGO እጅ ገብቶ አያውቅም ከመጀመሪያው ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኗ እጅ የነበረ ነው " - ቤተ ክርስቲያኗ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን 40 በመቶ የሚሆነው የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር " በጉልበት ሊወስደው ነው " ስትል በተደጋጋሚ መግለጿ ይታወቃል። ለቤተ ክርስቲያኗ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጥ ቲክቫህ ትላንት የጠየቅነው የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር…
" የሚዲያ ዘመቻችሁን እንድታቆሙ እንጠይቃለን " - የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር
የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ፥ " በሕገ-ወጥ መንገድ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይለማ የቆየ 280,000 ካሬ ሜትር ለልማት እንዲውል ማድረግ ሕገ- መንግስትን ማስከበር እና ማክበር እንጂ የሚያስወቅስ ጉዳይ አይደለም " አለ።
ይህን ያለው ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ ነው።
አስተዳደሩ ፥ " ሕግ እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ማስከበር የአንድ የመንግስት አካል ሃላፊነት ሆኖ እያለ ለ40 ዓመታት ያለ ልማት ( ያለ ህዝብ ጥቅም) የቆየ 280,000 ካሬ ሜትር ስኩዌር (የህዝብ እና የቀጣይ ትውልድ ውስን ሐብትን በሕገ -ወጥ መንገድ በየትኛውም መንገድ በሚዲያ ጫናም ሆነ በጉልበት ይዞ መገኘት ወንጀል ነው " ብሎታል።
" በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ኩሪፍቱ ሃይቅ ዙርያ የሆነው እንደሱ ነው " ሲል አክሏል።
ከተማ አስተዳደሩ ፥ " የመንግስት እና የሀዝብ ውስን ሃብትን የመጠበቅ ፥የማስተዳደር እና ለልማት እንዲዉል የማድረግ ህዝባዊ ፣ መንግስታዊ ግዴታ እና ተጠያቂነት አለበት " ያለ ሲሆን " ተደጋግሞ የሚደረግብን የሚዲያ ጥላቻ እና ዘመቻ የህዝብን ጥቅም ከማረጋጋጥ ጉዞዋችን ቅንጣት የማይገታን መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን " ብሏል።
" የከ/መስተዳድሩ ይህን መሬት ለልማት እንዳያውል በሃይማኖት ሽፋን ሕገ- ወጥ ሁከት እና ዘመቻ እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት በሙሉ ከድርጊታቸሁ እንድትታቀቡ " ሲልም አሳስቧል።
" ከዚህ ውጪ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ የሕግ-የበላይነት ለማስከበር እንገደዳለን " ሲልም አስጠንቅቋል።
" የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ይህንን ተረድተዉ የተጀመረውን ሃገራዊ እና የሕዝቦችን ተጠቃሚነት ጉዞ የሚያደናቅፍ የሚዲያ ዘመቻውን እንድያቆምልን እንጠይቃለን " ብሏል።
#Bishoftu
@tikvahethiopia
የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ፥ " በሕገ-ወጥ መንገድ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይለማ የቆየ 280,000 ካሬ ሜትር ለልማት እንዲውል ማድረግ ሕገ- መንግስትን ማስከበር እና ማክበር እንጂ የሚያስወቅስ ጉዳይ አይደለም " አለ።
ይህን ያለው ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ ነው።
አስተዳደሩ ፥ " ሕግ እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ማስከበር የአንድ የመንግስት አካል ሃላፊነት ሆኖ እያለ ለ40 ዓመታት ያለ ልማት ( ያለ ህዝብ ጥቅም) የቆየ 280,000 ካሬ ሜትር ስኩዌር (የህዝብ እና የቀጣይ ትውልድ ውስን ሐብትን በሕገ -ወጥ መንገድ በየትኛውም መንገድ በሚዲያ ጫናም ሆነ በጉልበት ይዞ መገኘት ወንጀል ነው " ብሎታል።
" በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ኩሪፍቱ ሃይቅ ዙርያ የሆነው እንደሱ ነው " ሲል አክሏል።
ከተማ አስተዳደሩ ፥ " የመንግስት እና የሀዝብ ውስን ሃብትን የመጠበቅ ፥የማስተዳደር እና ለልማት እንዲዉል የማድረግ ህዝባዊ ፣ መንግስታዊ ግዴታ እና ተጠያቂነት አለበት " ያለ ሲሆን " ተደጋግሞ የሚደረግብን የሚዲያ ጥላቻ እና ዘመቻ የህዝብን ጥቅም ከማረጋጋጥ ጉዞዋችን ቅንጣት የማይገታን መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን " ብሏል።
" የከ/መስተዳድሩ ይህን መሬት ለልማት እንዳያውል በሃይማኖት ሽፋን ሕገ- ወጥ ሁከት እና ዘመቻ እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት በሙሉ ከድርጊታቸሁ እንድትታቀቡ " ሲልም አሳስቧል።
" ከዚህ ውጪ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ የሕግ-የበላይነት ለማስከበር እንገደዳለን " ሲልም አስጠንቅቋል።
" የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ይህንን ተረድተዉ የተጀመረውን ሃገራዊ እና የሕዝቦችን ተጠቃሚነት ጉዞ የሚያደናቅፍ የሚዲያ ዘመቻውን እንድያቆምልን እንጠይቃለን " ብሏል።
#Bishoftu
@tikvahethiopia
#ኢሬቻ2017
የኢሬቻ ' ሆራ ፊንፊኔ ' እና ' ሆራ አርሰዲ ' በዓልን ለሚያከብሩ ታዳሚዎች ትራንስፖርት መዘጋጀቱን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ገልጿል።
በአዲስ አበባ በ5ቱም መግቢያ በሮች ወደ በዓሉ ማክበሪያ ቦታ የሚያደርሱ ከአዲስ አበባ ሲቲ ባስ 907 የከተማ አውቶብሶች፣ 400 የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አውቶብሶች መዘጋጀታቸውን ተገልጿል።
ቢሾፍቱ ለሚከበረው የኢሬቻ በዓል 150 የሚሆኑ ሀገር አቋራጭና መለስተኛ አውቶቢሶች ዝግጁ እንዲሆኑ መደረጉን ተመላክቷል።
በአጠቃላይ ታክሲዎችን ሳይጨምር 1 ሺህ 457 ተሸከርካሪዎች ተዘጋጅተዋል ተብሏል።
#AddisAbaba #Bishoftu
@tikvahethiopia
የኢሬቻ ' ሆራ ፊንፊኔ ' እና ' ሆራ አርሰዲ ' በዓልን ለሚያከብሩ ታዳሚዎች ትራንስፖርት መዘጋጀቱን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ገልጿል።
በአዲስ አበባ በ5ቱም መግቢያ በሮች ወደ በዓሉ ማክበሪያ ቦታ የሚያደርሱ ከአዲስ አበባ ሲቲ ባስ 907 የከተማ አውቶብሶች፣ 400 የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አውቶብሶች መዘጋጀታቸውን ተገልጿል።
ቢሾፍቱ ለሚከበረው የኢሬቻ በዓል 150 የሚሆኑ ሀገር አቋራጭና መለስተኛ አውቶቢሶች ዝግጁ እንዲሆኑ መደረጉን ተመላክቷል።
በአጠቃላይ ታክሲዎችን ሳይጨምር 1 ሺህ 457 ተሸከርካሪዎች ተዘጋጅተዋል ተብሏል።
#AddisAbaba #Bishoftu
@tikvahethiopia
(ኢትዮ ቴሌኮም)
#5ጂ በቢሾፍቱ ተጀመረ!!
ኩባንያችን የዘመናችን የመጨረሻው እና እጅግ ፈጣን የሆነው የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) የሞባይል አገልግሎት በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ ማስጀመሩን ስናበስር ታላቅ ደስታ ይሰማናል!
በዛሬው እለት ይፋ ያደረግነው የ5ጂ ሞባይል ኔትወርክ ኩሪፍቱ ወተር ፓርክ፣ በምስራቅ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ሰንሻይን፣ ግራር ሜዳ እና የረር የገበሬዎች ኅብረት ሥራ ማህበር የሚገኙ አካባቢዎች የሚሸፍን ነው፡፡
የአገልግሎቱ ተግባራዊ መሆን እያደገ የመጣውን የደንበኞች ዳታ ፍላጎት ለማስተናገድ ከማስቻሉ ባሻገር ተሞክሮን የሚጨምሩ የዲጂታል ሶሉሽኖችን በማቅረብ የዜጎችን ህይወት ለማዘመን እና ቢዝነስን ለማቀላጠፍ እንዲሁም አዳዲስ የዲጂታል ሥራ እድሎችን በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ያረጋግጣል፡፡
የ5ጂ አገልግሎት ከፍተኛ ፍጥነት ያለው፣ ዳታ የማስተላለፍ መዘግየትን በእጅጉ በመቀነስ ፋብሪካዎችና ኢንዱስትሪዎችን ከማዘመን በተጨማሪ ለሀገራችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ እንደ ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት፣ ማዕድን፣ ትራንስፖርት ያሉ ዘርፎችን አሰራር በማቀላጠፍ ተወዳዳሪነትን ይጨምራል፡፡
ክቡራን ደንበኞቻችን የ5ጂ አገልግሎትን ለማግኘት የሚያስችሉ ቀፎዎች በመጠቀም በእጅግ ፈጣኑ ኔትወርክ አስደሳች ተሞክሮ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንገልጻለን፡፡
ቀደም ሲል የ5ጂ ሞባይል ኔትወርክ አገልግሎትን በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ጂግጂጋ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ባህር ዳር፣ ሐዋሳ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ሆሳዕና እና አርባ ምንጭ ከተሞች ማስጀመራችን ይታወሳል፡፡
አዲስ ፍጥነት፣ አዲስ ምቾት፣ አዲስ አኗኗር!
#ዲጂታል_ኢትዮጵያን ዕውን በማድረግ ላይ
ለተጨማሪ: https://bit.ly/48PskNK
#Bishoftu #5G
#5ጂ በቢሾፍቱ ተጀመረ!!
ኩባንያችን የዘመናችን የመጨረሻው እና እጅግ ፈጣን የሆነው የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) የሞባይል አገልግሎት በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ ማስጀመሩን ስናበስር ታላቅ ደስታ ይሰማናል!
በዛሬው እለት ይፋ ያደረግነው የ5ጂ ሞባይል ኔትወርክ ኩሪፍቱ ወተር ፓርክ፣ በምስራቅ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ሰንሻይን፣ ግራር ሜዳ እና የረር የገበሬዎች ኅብረት ሥራ ማህበር የሚገኙ አካባቢዎች የሚሸፍን ነው፡፡
የአገልግሎቱ ተግባራዊ መሆን እያደገ የመጣውን የደንበኞች ዳታ ፍላጎት ለማስተናገድ ከማስቻሉ ባሻገር ተሞክሮን የሚጨምሩ የዲጂታል ሶሉሽኖችን በማቅረብ የዜጎችን ህይወት ለማዘመን እና ቢዝነስን ለማቀላጠፍ እንዲሁም አዳዲስ የዲጂታል ሥራ እድሎችን በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ያረጋግጣል፡፡
የ5ጂ አገልግሎት ከፍተኛ ፍጥነት ያለው፣ ዳታ የማስተላለፍ መዘግየትን በእጅጉ በመቀነስ ፋብሪካዎችና ኢንዱስትሪዎችን ከማዘመን በተጨማሪ ለሀገራችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ እንደ ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት፣ ማዕድን፣ ትራንስፖርት ያሉ ዘርፎችን አሰራር በማቀላጠፍ ተወዳዳሪነትን ይጨምራል፡፡
ክቡራን ደንበኞቻችን የ5ጂ አገልግሎትን ለማግኘት የሚያስችሉ ቀፎዎች በመጠቀም በእጅግ ፈጣኑ ኔትወርክ አስደሳች ተሞክሮ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንገልጻለን፡፡
ቀደም ሲል የ5ጂ ሞባይል ኔትወርክ አገልግሎትን በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ጂግጂጋ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ባህር ዳር፣ ሐዋሳ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ሆሳዕና እና አርባ ምንጭ ከተሞች ማስጀመራችን ይታወሳል፡፡
አዲስ ፍጥነት፣ አዲስ ምቾት፣ አዲስ አኗኗር!
#ዲጂታል_ኢትዮጵያን ዕውን በማድረግ ላይ
ለተጨማሪ: https://bit.ly/48PskNK
#Bishoftu #5G