TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#INVEA : በህገ-ወጥ መንገድ ፓስፖርት ሲያዘጋጁ የተገኙ 10 የኢሚግሬሽን ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በፌዴራል ፖሊስ የሙስና ወንጀሎች ዳይሬክተር ኮማንደር ታደሰ አያሌው ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፥ ተጠርጣሪዎቹ ህጋዊውን የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደት ወደ ጎን በመተው፣ የፓስፖርት ባለቤቶችን ሙሉ መረጃ በመቀየር እና በአንድ ማእከል መጠናቀቅ የነበረበትን አገልግሎት ወደ ተለያዩ ቅርንጫፎች በማዘዋወር ወንጀሉን በኔትወርክ መፈፀማቸውን ገልፀዋል።

ተጠርጣሪዎቹ ከደላሎች ጋር በፈጠሩት የጥቅም ትስስር በወንጀል የሚፈለጉ ግለሰቦች እና የውጭ ሀገር ዜጎችም ጭምር ፓስፖርት እንዲያገኙ ማመቻቸታቸውን አሳውቀዋል።

በተጨማሪም መንግስት ሊያገኝ ይችል የነበረውን ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዳሳጡ ነው ኮማንደር ታደሰ አያሌው ለቴሌቪዥን ጣቢያው ተናግረዋል።

@tikvahethiopia