#INVEA : በህገ-ወጥ መንገድ ፓስፖርት ሲያዘጋጁ የተገኙ 10 የኢሚግሬሽን ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
በፌዴራል ፖሊስ የሙስና ወንጀሎች ዳይሬክተር ኮማንደር ታደሰ አያሌው ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፥ ተጠርጣሪዎቹ ህጋዊውን የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደት ወደ ጎን በመተው፣ የፓስፖርት ባለቤቶችን ሙሉ መረጃ በመቀየር እና በአንድ ማእከል መጠናቀቅ የነበረበትን አገልግሎት ወደ ተለያዩ ቅርንጫፎች በማዘዋወር ወንጀሉን በኔትወርክ መፈፀማቸውን ገልፀዋል።
ተጠርጣሪዎቹ ከደላሎች ጋር በፈጠሩት የጥቅም ትስስር በወንጀል የሚፈለጉ ግለሰቦች እና የውጭ ሀገር ዜጎችም ጭምር ፓስፖርት እንዲያገኙ ማመቻቸታቸውን አሳውቀዋል።
በተጨማሪም መንግስት ሊያገኝ ይችል የነበረውን ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዳሳጡ ነው ኮማንደር ታደሰ አያሌው ለቴሌቪዥን ጣቢያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
በፌዴራል ፖሊስ የሙስና ወንጀሎች ዳይሬክተር ኮማንደር ታደሰ አያሌው ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፥ ተጠርጣሪዎቹ ህጋዊውን የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደት ወደ ጎን በመተው፣ የፓስፖርት ባለቤቶችን ሙሉ መረጃ በመቀየር እና በአንድ ማእከል መጠናቀቅ የነበረበትን አገልግሎት ወደ ተለያዩ ቅርንጫፎች በማዘዋወር ወንጀሉን በኔትወርክ መፈፀማቸውን ገልፀዋል።
ተጠርጣሪዎቹ ከደላሎች ጋር በፈጠሩት የጥቅም ትስስር በወንጀል የሚፈለጉ ግለሰቦች እና የውጭ ሀገር ዜጎችም ጭምር ፓስፖርት እንዲያገኙ ማመቻቸታቸውን አሳውቀዋል።
በተጨማሪም መንግስት ሊያገኝ ይችል የነበረውን ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዳሳጡ ነው ኮማንደር ታደሰ አያሌው ለቴሌቪዥን ጣቢያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia