#HappeningNow
በሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚልና በስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በአቶ አሊ ከድር መሪነት በዞኑ የባህል አዳራሽ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። እየተደረገ በሚገኘው የውይይት መድረክ ላይ የመንገድ፣ የመብራት፣ የውሃና ሌሎች የመሰረተ ልማቶችን በማስመልከት ተሳታፊዎች ጥያቄዎችን በማንሳት ላይ ናቸው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚልና በስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በአቶ አሊ ከድር መሪነት በዞኑ የባህል አዳራሽ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። እየተደረገ በሚገኘው የውይይት መድረክ ላይ የመንገድ፣ የመብራት፣ የውሃና ሌሎች የመሰረተ ልማቶችን በማስመልከት ተሳታፊዎች ጥያቄዎችን በማንሳት ላይ ናቸው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
በደሴ ከተማ አስተዳደር ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የእምነቱ ተከታዮች በሞጣ ከተማ በእምነት ተቋማት ላይ ደረሰው ጥቃት አሳፋሪ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የእምነቱ ተከታዮች በደሴ ከተማ በሚገኘው ዐረብ ገንዳ መስጂድ ባደረጉት ውይይት አጥፊዎቹ በሕግ ሊጠየቁ እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡ ጥቃቱ ከመድረሱ በፊትም ሆነ ከደረሰ በኋላ መንግሥት እያሳዬ ያለው ለዘብተኛ አቋም መታረም እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡
የክልሉ መንግሥት በመስጂዶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንደሚደርስ መረጃዎች እንደነበሩት በማንሳትም ቅድመ መከላከል አልሠራም በሚል ወቅሰዋል፡፡ ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላም በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው ተጠርጣሪዎች ቁጥር አነስተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
መንግሥት የተቃጠሉ ቤተ እምነቶችን እንዲሠራና የተዘረፉ ንብረቶችን እንዲመለሱ ማድረግ እንደለበትም ተናግረዋል፡፡ችግሩ እንዲባባስም ሆነ የቤተ እምነቶች እንዲቃጠሉ የሚዲያ አካላት ድርሻ ከፍተኛ እንደሆነም ነው ተወያዮቹ ያነሱት፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሚዲያ አውታሮች በተለይ በመስጂዶች ላይ ጥቃት ሲደርስ የሚሰጡት ሽፋን ሚዛናዊ እንዳልሆና መታረም እንደሚገባውም መክረዋል፡፡ መንግሥት የተቃጠሉ ቤተ እምነቶችን እንዲሠራና የተዘረፉ ንብረቶችን እንዲያስመልስም አሳስበዋል።
#AMMA
#TIKVAH_ETH
በሞጣ ከተማ በእምነት ተቋማት ላይ የተፈፀመው ድርጊት የሚያወግዙ ሰልፎች በተለያዩ ከተሞች እና አካባቢዎች እንደተደረጉ መረጃዎች ደርሰውናል። በባሌ ደሎ መና በተካሄደ ሰልፍ የሙስሊሙ እና ክርስትያኑ ማህበረሰብ አባላት ድርጊቱን አደባባይ በመውጣት በጋራ አውግዘዋል። በተለያዩ ከተሞች እና አካባቢዎች የተደረጉ የተቃውሞ ሰልፎችን ማስፈንጠሪያውን በመጫን መመልከት ትችላላችሁ https://telegra.ph/TIKVAH-12-22
@tikvahethiopiaBot
በደሴ ከተማ አስተዳደር ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የእምነቱ ተከታዮች በሞጣ ከተማ በእምነት ተቋማት ላይ ደረሰው ጥቃት አሳፋሪ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የእምነቱ ተከታዮች በደሴ ከተማ በሚገኘው ዐረብ ገንዳ መስጂድ ባደረጉት ውይይት አጥፊዎቹ በሕግ ሊጠየቁ እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡ ጥቃቱ ከመድረሱ በፊትም ሆነ ከደረሰ በኋላ መንግሥት እያሳዬ ያለው ለዘብተኛ አቋም መታረም እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡
የክልሉ መንግሥት በመስጂዶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንደሚደርስ መረጃዎች እንደነበሩት በማንሳትም ቅድመ መከላከል አልሠራም በሚል ወቅሰዋል፡፡ ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላም በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው ተጠርጣሪዎች ቁጥር አነስተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
መንግሥት የተቃጠሉ ቤተ እምነቶችን እንዲሠራና የተዘረፉ ንብረቶችን እንዲመለሱ ማድረግ እንደለበትም ተናግረዋል፡፡ችግሩ እንዲባባስም ሆነ የቤተ እምነቶች እንዲቃጠሉ የሚዲያ አካላት ድርሻ ከፍተኛ እንደሆነም ነው ተወያዮቹ ያነሱት፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሚዲያ አውታሮች በተለይ በመስጂዶች ላይ ጥቃት ሲደርስ የሚሰጡት ሽፋን ሚዛናዊ እንዳልሆና መታረም እንደሚገባውም መክረዋል፡፡ መንግሥት የተቃጠሉ ቤተ እምነቶችን እንዲሠራና የተዘረፉ ንብረቶችን እንዲያስመልስም አሳስበዋል።
#AMMA
#TIKVAH_ETH
በሞጣ ከተማ በእምነት ተቋማት ላይ የተፈፀመው ድርጊት የሚያወግዙ ሰልፎች በተለያዩ ከተሞች እና አካባቢዎች እንደተደረጉ መረጃዎች ደርሰውናል። በባሌ ደሎ መና በተካሄደ ሰልፍ የሙስሊሙ እና ክርስትያኑ ማህበረሰብ አባላት ድርጊቱን አደባባይ በመውጣት በጋራ አውግዘዋል። በተለያዩ ከተሞች እና አካባቢዎች የተደረጉ የተቃውሞ ሰልፎችን ማስፈንጠሪያውን በመጫን መመልከት ትችላላችሁ https://telegra.ph/TIKVAH-12-22
@tikvahethiopiaBot
በሀገሪቱ የተከሰቱ ግጭቶች የፍርድ ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ ላይ እንቅፋት ፈጥረዋል ተባለ!
የክልል ፍርድ ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ ቢሆንም በሀገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች ተከስተው የነበሩ ግጭቶች ለአገልግሎት አሰጣጡ ተግዳሮት እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
ይህ የተገለፀው እየተካሄደ ባለው 4ኛው የፌዴራል ፍ/ቤት ጉባኤ ላይ ነው፡፡ በጉባኤው በክልል ፍ/ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ውይይት እየተደረገ ይገኛል፡፡ አሁን በአገሪቱ ያለው የፖለቲካ ትኩሳት በዳኝነት ነፃነት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ እንደመጣም ተገልጿል፡፡
(ኢቲቪ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የክልል ፍርድ ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ ቢሆንም በሀገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች ተከስተው የነበሩ ግጭቶች ለአገልግሎት አሰጣጡ ተግዳሮት እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
ይህ የተገለፀው እየተካሄደ ባለው 4ኛው የፌዴራል ፍ/ቤት ጉባኤ ላይ ነው፡፡ በጉባኤው በክልል ፍ/ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ውይይት እየተደረገ ይገኛል፡፡ አሁን በአገሪቱ ያለው የፖለቲካ ትኩሳት በዳኝነት ነፃነት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ እንደመጣም ተገልጿል፡፡
(ኢቲቪ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#PMOEthiopia
ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ከአዲስ አበባ የታክሲ ባለቤቶች፣ አሽከርካሪዎችና ረዳቶች ጋር የታክሲ ጣቢያውን አጸዱ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በካዛንቺስ የሚገኘውንና የ8 መሥመሮች መነሻ የሆነውን ጣቢያ ያጸዱት ለታክሲ አሽከርካሪዎችና ረዳቶች አገልግሎት ያላቸውን ክብር ለማሳየት መሆኑን ገልጠዋል።
ምንጭ፡- የጠ/ሚር ፅ/ቤት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ከአዲስ አበባ የታክሲ ባለቤቶች፣ አሽከርካሪዎችና ረዳቶች ጋር የታክሲ ጣቢያውን አጸዱ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በካዛንቺስ የሚገኘውንና የ8 መሥመሮች መነሻ የሆነውን ጣቢያ ያጸዱት ለታክሲ አሽከርካሪዎችና ረዳቶች አገልግሎት ያላቸውን ክብር ለማሳየት መሆኑን ገልጠዋል።
ምንጭ፡- የጠ/ሚር ፅ/ቤት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#EthiopianAirlines
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ18 ዓመታት በፊት ተቋርጦ የነበረውን የግሪክ አቴንስ በረራ አገልግሎት መጀመሩን አስታወቀ። አየር መንገዱ እንዳስታወቀው፤ የግሪኳ አቴንስ ዳግመኛ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ መረብ ውስጥ ተቀላቅላለች። አየር መንገዱ ታህሳስ 8 ቀን 2012 ዓ.ም የጀመረው የአቴንስ በረራ በአለም ላይ በሁሉም አህጉራት ያሉትን መዳረሻዎች ወደ 127 ከፍ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
(ኢዜአ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ18 ዓመታት በፊት ተቋርጦ የነበረውን የግሪክ አቴንስ በረራ አገልግሎት መጀመሩን አስታወቀ። አየር መንገዱ እንዳስታወቀው፤ የግሪኳ አቴንስ ዳግመኛ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ መረብ ውስጥ ተቀላቅላለች። አየር መንገዱ ታህሳስ 8 ቀን 2012 ዓ.ም የጀመረው የአቴንስ በረራ በአለም ላይ በሁሉም አህጉራት ያሉትን መዳረሻዎች ወደ 127 ከፍ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
(ኢዜአ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አልፈልግም ማለት አልፈልግም ነው!
• "አቁም" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መሸሽ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "እምቢ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መግፋት/መገፍተር" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ዝግጁ አይደለሁም" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ተወኝ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ዞር በል" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መጮህ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "እረፍ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ማልቀስ" ማለት አልፈልግም ነው!
የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ያንቺ ንቅናቄ ( Yanchi movement ) ለሶስት ቀን በሚቆየው የሴት ልጅ ጥቃትን በመቃወም የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅተዋል፡፡ ዝግጅቱ ትላንት የተጀመረ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የ16 ቀን ንቅናቄ አንድ አካል እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸውልናል፡፡ በዚህ ንቅናቄ በዩኒቨርሲቲው የሚገኙ ሌሎች ክበባትም ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
በሌላ በኩል በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚገኘው "መራሂት ክበብ" አትኩሮቱን ሴት ተማሪዎችን በማብቃት ላይ አድርጎ እየሰራ ሲሆን ለሴት ተማሪዎች የፅዳት መጠበቂያ የሚሆን 88 ካርቶን ሞዴስ በመግዛት ለሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሴቶች ህፃናት ወጣቶች እና ኤችአይቪ ኤድስ ዳይሬክትቶሬት አስረክበዋል። የመጀመሪያውን ድጋፋቸውንም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቅርንጫፍ በሆነው በአዋዳ ካምፓስ አድርገዋል።
- በቲክቫህ ኢትዮጵያ ስም እየሰራችሁት ላለው መልካም ስራና ለሌሎች ወጣቶች ትምህርት የሚሰጥ ተግባር ላይ በመሳተፋችሁ ያለንን አክብሮት እና ምስጋና እናቀርባለን!
#HawassaUniversity
በርቱልን!
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
• "አቁም" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መሸሽ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "እምቢ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መግፋት/መገፍተር" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ዝግጁ አይደለሁም" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ተወኝ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ዞር በል" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መጮህ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "እረፍ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ማልቀስ" ማለት አልፈልግም ነው!
የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ያንቺ ንቅናቄ ( Yanchi movement ) ለሶስት ቀን በሚቆየው የሴት ልጅ ጥቃትን በመቃወም የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅተዋል፡፡ ዝግጅቱ ትላንት የተጀመረ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የ16 ቀን ንቅናቄ አንድ አካል እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸውልናል፡፡ በዚህ ንቅናቄ በዩኒቨርሲቲው የሚገኙ ሌሎች ክበባትም ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
በሌላ በኩል በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚገኘው "መራሂት ክበብ" አትኩሮቱን ሴት ተማሪዎችን በማብቃት ላይ አድርጎ እየሰራ ሲሆን ለሴት ተማሪዎች የፅዳት መጠበቂያ የሚሆን 88 ካርቶን ሞዴስ በመግዛት ለሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሴቶች ህፃናት ወጣቶች እና ኤችአይቪ ኤድስ ዳይሬክትቶሬት አስረክበዋል። የመጀመሪያውን ድጋፋቸውንም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቅርንጫፍ በሆነው በአዋዳ ካምፓስ አድርገዋል።
- በቲክቫህ ኢትዮጵያ ስም እየሰራችሁት ላለው መልካም ስራና ለሌሎች ወጣቶች ትምህርት የሚሰጥ ተግባር ላይ በመሳተፋችሁ ያለንን አክብሮት እና ምስጋና እናቀርባለን!
#HawassaUniversity
በርቱልን!
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
#AddisAbeba
የጥምቀት ክብረ በዓል በዩኔስኮ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ መድረክ በሚሌኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) የጥምቀት በዓል አከባበርን ከመስቀል በዓል፣ የገዳ ስርዓት እና የፍቼ ጨምበላላ ክብረ በዓላትን ተከትሎ አራተኛው የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ መመዝገቡ የሚታወስ ነው፡፡
(Mayor Office of AA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጥምቀት ክብረ በዓል በዩኔስኮ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ መድረክ በሚሌኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) የጥምቀት በዓል አከባበርን ከመስቀል በዓል፣ የገዳ ስርዓት እና የፍቼ ጨምበላላ ክብረ በዓላትን ተከትሎ አራተኛው የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ መመዝገቡ የሚታወስ ነው፡፡
(Mayor Office of AA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#SomaliRegionalState
የሶማሌ ክልል በተወካዮች ምክር ቤት ያለው የውክል ቁጥር እንዲስተካከል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ሙስጠፋ መሐመድ ዑመር ብሔራዊ ምርጫ ቦርድንና የፌዴሬሽን ምክር ቤትን በደብዳቤ ጠይቀዋል። ክልሉ 23 መቀመጫዎች በተወካዮች ምክር ቤት አሉት። ክልሉ በሕገ መንግሥቱ መሠረት 32 መቀመጫዎች ሊኖሩት ቢገባም ዘጠኝ ተቀንሶበት ለረጅም አመታት በ23 የውክልና መቀመጫ መቆየቱን አቶ ሙስጠፋ በደብዳቤያቸው ገልጸዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሶማሌ ክልል በተወካዮች ምክር ቤት ያለው የውክል ቁጥር እንዲስተካከል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ሙስጠፋ መሐመድ ዑመር ብሔራዊ ምርጫ ቦርድንና የፌዴሬሽን ምክር ቤትን በደብዳቤ ጠይቀዋል። ክልሉ 23 መቀመጫዎች በተወካዮች ምክር ቤት አሉት። ክልሉ በሕገ መንግሥቱ መሠረት 32 መቀመጫዎች ሊኖሩት ቢገባም ዘጠኝ ተቀንሶበት ለረጅም አመታት በ23 የውክልና መቀመጫ መቆየቱን አቶ ሙስጠፋ በደብዳቤያቸው ገልጸዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Congratulations - አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲው ለ 6ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 140 የሕክምና ዶክተሮች ትላንት ታኅሣሥ 11/2012 ዓ/ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል፡፡ ከእነዚህም መካከል 37ቱ ሴቶች መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"አንዳንድ አካላት ብሄርን ከብሄርና ሃይማኖትን ከሃይማኖት በማጋጨት ሰላምን ለማወክ የሚያደርጉት ጥረት አይሳካም። እነዚህ ኣካላት የማንንም ብሄርና ሃይማኖት አይወክሉም። የሃይማኖት ብዝሃነት የግጭትና የስጋት ምንጭ ሳይሆን የሰላም ፣ የመቻቻልና የአንድነት መሰረት ነው። በአሁኑ ወቅት የሃይማኖትና የብሄር እኩልነት ወደ ኋላ በማይቀለበስበት ደረጃ ደርሷል፤ ይሄን በመጣስ የሚከናወን አፀያፊ ተግባርን ሁሉም ሊያወግዘው ይገባል።" - ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም (የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AbiyAhemed #LemmaMegersa
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድና የመከላከያ ሚኒስትሩ ለማ መገርሳ መካከል የነበረ አለመግባባት "በበሳል የድርጅታችን ስራ አስፈጻሚ አመራሮችና በቀድሞ የትግል ጓዶች" ተፈቷል ሲል የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ አስታውቋል። ዶ/ር አብይ እና አቶ ለማ በጋራ ለመታገል ተስማምተዋል።
(እሸት በቀለ - ከጀርመን ድምፅ ሬድዮ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድና የመከላከያ ሚኒስትሩ ለማ መገርሳ መካከል የነበረ አለመግባባት "በበሳል የድርጅታችን ስራ አስፈጻሚ አመራሮችና በቀድሞ የትግል ጓዶች" ተፈቷል ሲል የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ አስታውቋል። ዶ/ር አብይ እና አቶ ለማ በጋራ ለመታገል ተስማምተዋል።
(እሸት በቀለ - ከጀርመን ድምፅ ሬድዮ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AbiyAhemed #LemmaMegersa
አቶ አዲሱ አረጋ ዛሬ በፌስቡክ ገጻቸው እንደገለጹት በአስተዳራዊ ስርዓት በተለይም እንደ ሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታና አዳዲስ ሀሳቦችና የፓርቲ ሪፎርሞች በሚካሄዱበት ወቅት የሀሳብ ልዩነቶች ሊኖሩ ቢችሉም የሀሳብ ልዩነት በራሱ ችግር እንዳልሆነ ገልጸው ትልቁ ጉዳይ ይህን የሀሳብ ልዩነት እንዴት ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንፈታዋለን የሚለው ነው ሲሉ አክለዋል፡፡
አቶ አዲሱ በቅርቡ የፓርቲው አመራር የሆኑት አቶ ለማ መገርሳ ለመገናኛ ብዙሃን በመደመር ፍልስፍና እንዲሁም በፓርቲው ውህደት እንደማይስማሙ የገለጹትን ጠቅሰው ይህንን ጉዳይ በኦሮሞ ባህልና ስርዓት መሰረት የቀድሞ የኦዲፒ የስራ አመራሮች ሌሎችም ኃላፊዎች በተገኙበት የበሰለ ውይይት በማድረግና የነበሩ ልዩነቶችን በማጥበብ ከዚህ በኃላም አንድነትን አጠናክሮ አብሮ ለመስራት ተስማምተናል ብለዋል፡፡
አቶ አዲሱ አክለውም ፓርቲያቸው በዲሞክራሲ ባህል እና በኦሮሞ ባህልና ስርዓት የውስጥ ችግሩን ለመፍታትና ህብረተሰቡ ያለውን ጥያቄ ሁሉ ለመፍታት የሚሰራውን ስራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አቶ አዲሱ አረጋ ዛሬ በፌስቡክ ገጻቸው እንደገለጹት በአስተዳራዊ ስርዓት በተለይም እንደ ሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታና አዳዲስ ሀሳቦችና የፓርቲ ሪፎርሞች በሚካሄዱበት ወቅት የሀሳብ ልዩነቶች ሊኖሩ ቢችሉም የሀሳብ ልዩነት በራሱ ችግር እንዳልሆነ ገልጸው ትልቁ ጉዳይ ይህን የሀሳብ ልዩነት እንዴት ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንፈታዋለን የሚለው ነው ሲሉ አክለዋል፡፡
አቶ አዲሱ በቅርቡ የፓርቲው አመራር የሆኑት አቶ ለማ መገርሳ ለመገናኛ ብዙሃን በመደመር ፍልስፍና እንዲሁም በፓርቲው ውህደት እንደማይስማሙ የገለጹትን ጠቅሰው ይህንን ጉዳይ በኦሮሞ ባህልና ስርዓት መሰረት የቀድሞ የኦዲፒ የስራ አመራሮች ሌሎችም ኃላፊዎች በተገኙበት የበሰለ ውይይት በማድረግና የነበሩ ልዩነቶችን በማጥበብ ከዚህ በኃላም አንድነትን አጠናክሮ አብሮ ለመስራት ተስማምተናል ብለዋል፡፡
አቶ አዲሱ አክለውም ፓርቲያቸው በዲሞክራሲ ባህል እና በኦሮሞ ባህልና ስርዓት የውስጥ ችግሩን ለመፍታትና ህብረተሰቡ ያለውን ጥያቄ ሁሉ ለመፍታት የሚሰራውን ስራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አቶ ለማ መገርሳ ብልፅግናን ደገፉ - ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ተፈጥሮ የነበረው አለመግባባትም ተፈታ!
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና የመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ መካከል ተከስቶ የነበረው አለመግባባት በተከታታይ በአባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች ጋር በተደረገ ውይይት ከመግባባት ላይ መደረሱ ተነግሯል። አቶ ለማ መገርሳ ያለውን ችግር በሂደት ለመፍታትና ከብልፅግና ፓርቲ ጋርም ለመስራት መስማማታቸውን OBN የቴሌቭዥን ጣብያ ማምሻውን ዘግቧል።
(SBS ሬድዮ አማርኛው አገልግሎት)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና የመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ መካከል ተከስቶ የነበረው አለመግባባት በተከታታይ በአባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች ጋር በተደረገ ውይይት ከመግባባት ላይ መደረሱ ተነግሯል። አቶ ለማ መገርሳ ያለውን ችግር በሂደት ለመፍታትና ከብልፅግና ፓርቲ ጋርም ለመስራት መስማማታቸውን OBN የቴሌቭዥን ጣብያ ማምሻውን ዘግቧል።
(SBS ሬድዮ አማርኛው አገልግሎት)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የወጪ እና የገቢ ንግድ ተነጣጥለው ኦዲት ሊደረጉ ነው!
የወጪ ንግድና የገቢ ንግድ ተቀላቅለው በመሰራታቸው አስመጪና ላኪዎች ኪሳራቸውን በተለያየ መልክ እያስመዘገቡ ያቀርቡ የነበረውን የውሸት ሪፖርት ለመከላከል ሁለቱም ለየብቻ ኦዲት ሊደረጉ መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ በመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ በሰጡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ ቀድሞ አስመጪ ብቻ የነበሩ በሙሉ ወደ ላኪነት ገብተዋል። እነዚህ የውጪ ነጋዴዎች የውሸት የኪሳራ ሪፖርት እያቀረቡ በመሆኑ፤ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከአሁን በኋላ የወጪ ንግድ ራሱን ችሎ ኦዲት መደረግ ያለበት መሆኑን ለገቢዎች አመልክተዋል።
(EPA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የወጪ ንግድና የገቢ ንግድ ተቀላቅለው በመሰራታቸው አስመጪና ላኪዎች ኪሳራቸውን በተለያየ መልክ እያስመዘገቡ ያቀርቡ የነበረውን የውሸት ሪፖርት ለመከላከል ሁለቱም ለየብቻ ኦዲት ሊደረጉ መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ በመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ በሰጡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ ቀድሞ አስመጪ ብቻ የነበሩ በሙሉ ወደ ላኪነት ገብተዋል። እነዚህ የውጪ ነጋዴዎች የውሸት የኪሳራ ሪፖርት እያቀረቡ በመሆኑ፤ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከአሁን በኋላ የወጪ ንግድ ራሱን ችሎ ኦዲት መደረግ ያለበት መሆኑን ለገቢዎች አመልክተዋል።
(EPA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETHIOPIA #SUDAN
የኢትዮጵያ የውሃ ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከሱዳን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌተናል ጄኔራል አብደል ፋታህ አል ቡርሃን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሊቀመንበሩ በሱዳን እና በኢትዮጵያ ግንኙነት መካከል የታየውን የለውጥ ደረጃ አድንቀዋል፡፡
የሱዳን የመስኖ እና የውሃ ሀብት ሚኒስትር ኢንጂነር ያሲር አባስ በተገኙበት ሊቀመንበሩ ትናንት ምሽት በጽህፈት ቤታቸው ከኢትዮጵያ የውሃ ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በዚህ ወቅት ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር በሁሉም መስክ ያላትን ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ መግለፃቸውን የሉዓላዊ ሽግግር ምክር ቤት ሚዲያ አስታውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የውሃ ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከሱዳን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌተናል ጄኔራል አብደል ፋታህ አል ቡርሃን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሊቀመንበሩ በሱዳን እና በኢትዮጵያ ግንኙነት መካከል የታየውን የለውጥ ደረጃ አድንቀዋል፡፡
የሱዳን የመስኖ እና የውሃ ሀብት ሚኒስትር ኢንጂነር ያሲር አባስ በተገኙበት ሊቀመንበሩ ትናንት ምሽት በጽህፈት ቤታቸው ከኢትዮጵያ የውሃ ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በዚህ ወቅት ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር በሁሉም መስክ ያላትን ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ መግለፃቸውን የሉዓላዊ ሽግግር ምክር ቤት ሚዲያ አስታውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የትግራይ ልማት ማህበር...
የትግራይ ልማት ማህበር ድህነትን ለመቀነስ እያደረገ ላለው ጥረት የማህበሩ አባላትና ደጋፊዎች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አሳሰቡ። የልማት ማህበሩ ከትናንት በስቲያ ባካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን 130 ሚሊዮን ብር አገኘ።
በገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶኑ ላይ የተገኙት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እንዳሉት፣ የልማት ማህበሩ በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና ተደራሽነትን ለማስፋት በርካታ ውጤታማ ተግባራትን አከናውኗል።
በተያዘው ዓመትም ከ3 ሺህ በላይ የዳስ ትምህርት ቤቶችን ወደ ሕንጻ ክፍሎች ለመቀየር በማሰብ የገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። ዶክተር ደብረጽዮን እንዳሉት በአሁኑ ወቅት በክልሉ ካሉ በርካታ ችግሮች መካከል የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅ አንዱና መሰረታዊ ጉዳይ ነው። የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ብቁና አገሩን የሚወድ ትውልድ ለማፍራት ማህበሩ የጀመረውን እንቅስቃሴ እንዲያጠናክርም ጠይቀዋል።
ሥራ ፈጣሪና ችግር ፈቺ ትውልድን ለማፍራት በሚደረገው ጥረት የትግራይ ልማት ማህበርን በገንዘብ፣ በእውቀትና በጉልበት ማጠናከር እንደሚገባም ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ደብረፅዮን ተናግረዋል። በተለይ የማህበሩ አባላትና ደጋፊዎች አቅማቸውን በማሰባሰብና አንድነታቸውን በማጠናከር ለማህበሩ ሲያደርጉት የነበረውን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል።
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የትግራይ ልማት ማህበር ድህነትን ለመቀነስ እያደረገ ላለው ጥረት የማህበሩ አባላትና ደጋፊዎች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አሳሰቡ። የልማት ማህበሩ ከትናንት በስቲያ ባካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን 130 ሚሊዮን ብር አገኘ።
በገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶኑ ላይ የተገኙት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እንዳሉት፣ የልማት ማህበሩ በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና ተደራሽነትን ለማስፋት በርካታ ውጤታማ ተግባራትን አከናውኗል።
በተያዘው ዓመትም ከ3 ሺህ በላይ የዳስ ትምህርት ቤቶችን ወደ ሕንጻ ክፍሎች ለመቀየር በማሰብ የገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። ዶክተር ደብረጽዮን እንዳሉት በአሁኑ ወቅት በክልሉ ካሉ በርካታ ችግሮች መካከል የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅ አንዱና መሰረታዊ ጉዳይ ነው። የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ብቁና አገሩን የሚወድ ትውልድ ለማፍራት ማህበሩ የጀመረውን እንቅስቃሴ እንዲያጠናክርም ጠይቀዋል።
ሥራ ፈጣሪና ችግር ፈቺ ትውልድን ለማፍራት በሚደረገው ጥረት የትግራይ ልማት ማህበርን በገንዘብ፣ በእውቀትና በጉልበት ማጠናከር እንደሚገባም ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ደብረፅዮን ተናግረዋል። በተለይ የማህበሩ አባላትና ደጋፊዎች አቅማቸውን በማሰባሰብና አንድነታቸውን በማጠናከር ለማህበሩ ሲያደርጉት የነበረውን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል።
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia