This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማት ተቀበሉ!
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማታቸውን ተቀበሉ። የኖቤል የሰላም ሽልማት ስነ ስርዓት በዛሬው እለት በኖርዌይ ኦስሎ በመካሄድ ላይ ይግኛል። በስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማታቸውን ተቀበሉ። የኖቤል የሰላም ሽልማት ስነ ስርዓት በዛሬው እለት በኖርዌይ ኦስሎ በመካሄድ ላይ ይግኛል። በስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#NobelPeacePrize #AbiyAhemed
የኖቤል ኮሚቴ ሊቀ መንበር ቤሪት ራይስ አንደርሰን ለጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ ሽልማት ከመስጠታቸው በፊት ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚንሥትሩ ለሰላም ላበረከቱት አስተዋጽዖ ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ ሰላምና ዲሞክራሲን ለማስፈን በርካታ ርምጃዎችን መውሰዳቸው እንዲሁም በካቢኔያቸው አምሳ በመቶ ሴቶችን መሾማቸዉ ተመስግኗል። በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የሰላም ሚንስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ሣኅለ-ወርቅ ዘውዴ እንዲሁም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ማአዛ አሸናፊ ሴቶች መኾናቸውን ሊቀመንበሯ አመስግነዋል።
ሽልማቱም የተሰጠው፦ ሰላም እና ብልጽግና በኢትዮጵያ ለማስፈን ዓልመው መነሳታቸው ሊቀመንበሯ ገልጠዉ የኖቤል ኮሚቴዉ ዕውቅና ሰጥቶታል። በምሥራቅ አፍሪቃ ሃገራት ሰላም እንዲሰፍን ጠቅላይ ሚንስትሩ ላበረከቱት አስተዋጽዖም በኮሚቴው ተመስግነዋል።
ኤርትራ እና ጅቡቲ ሰላም እንዲፈጥሩ ጥረት መደረጉ፤ በደቡብ ሱዳን እና ሱዳን ሰላማዊ መፍትኄዎችን እንደ አማራጭ መወሰዳቸው ተወድሷል። «ኢትዮጵያ የሰው ልጆች መገኛ ናት» ያሉት የኖቤል ኮሚቴ ሊቀ መንበር ቤሪት ራይስ አንደርሰን፤ «የመጀመሪያው ሆሞ ሴፒያን የፈለሰው ከእርስዎ [ጠ/ሚ ዐቢይ]ሀገር ነው፣ በዚህም እኛ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ነን» ብለዋል። ኢትዮጵያ በአዉሮጳዉያን ቅኝ አለመገዛትዋ፤ የአፍሪቃ ኅብረት መቀመጫ መኾኗ ከመድረኩ ሲገለጥም ሞቅ ያለ ጭብጨባ ከታዳሚያን ተሰምቷል።
(DW)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኖቤል ኮሚቴ ሊቀ መንበር ቤሪት ራይስ አንደርሰን ለጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ ሽልማት ከመስጠታቸው በፊት ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚንሥትሩ ለሰላም ላበረከቱት አስተዋጽዖ ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ ሰላምና ዲሞክራሲን ለማስፈን በርካታ ርምጃዎችን መውሰዳቸው እንዲሁም በካቢኔያቸው አምሳ በመቶ ሴቶችን መሾማቸዉ ተመስግኗል። በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የሰላም ሚንስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ሣኅለ-ወርቅ ዘውዴ እንዲሁም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ማአዛ አሸናፊ ሴቶች መኾናቸውን ሊቀመንበሯ አመስግነዋል።
ሽልማቱም የተሰጠው፦ ሰላም እና ብልጽግና በኢትዮጵያ ለማስፈን ዓልመው መነሳታቸው ሊቀመንበሯ ገልጠዉ የኖቤል ኮሚቴዉ ዕውቅና ሰጥቶታል። በምሥራቅ አፍሪቃ ሃገራት ሰላም እንዲሰፍን ጠቅላይ ሚንስትሩ ላበረከቱት አስተዋጽዖም በኮሚቴው ተመስግነዋል።
ኤርትራ እና ጅቡቲ ሰላም እንዲፈጥሩ ጥረት መደረጉ፤ በደቡብ ሱዳን እና ሱዳን ሰላማዊ መፍትኄዎችን እንደ አማራጭ መወሰዳቸው ተወድሷል። «ኢትዮጵያ የሰው ልጆች መገኛ ናት» ያሉት የኖቤል ኮሚቴ ሊቀ መንበር ቤሪት ራይስ አንደርሰን፤ «የመጀመሪያው ሆሞ ሴፒያን የፈለሰው ከእርስዎ [ጠ/ሚ ዐቢይ]ሀገር ነው፣ በዚህም እኛ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ነን» ብለዋል። ኢትዮጵያ በአዉሮጳዉያን ቅኝ አለመገዛትዋ፤ የአፍሪቃ ኅብረት መቀመጫ መኾኗ ከመድረኩ ሲገለጥም ሞቅ ያለ ጭብጨባ ከታዳሚያን ተሰምቷል።
(DW)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
«ኢትዮጵያ የሰው ልጆች መገኛ ናት። የመጀመሪያው ሆሞ ሴፒያን የፈለሰው ከእርስዎ [ጠ/ሚ ዐቢይ] ግዛት ነው። በዚህም እኛ ሁላችንም ኢትዮጵያውያኖች ነን።» - የኖቤል ኮሚቴ ሊቀ መንበር ቤሪት ራይስ አንደርሰን
#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኖርዌይ፣ ኦስሎ የኖቤል የሰላም ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፡-
• የኖርዌይ የኖቤል ኮሚቴ ለሰጠኝ እውቅና አመሰግናለሁ፡፡
• ለኢትዮ-ኤርትራ የሰላም ስምምነት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሰላም ቁርጠኝነት ወሳኝ ነበር፡፡
• ይህንን ሽልማት የአፍሪካ ህዝቦችና የዓለም ህዝቦችን ወክዬ ነው የምቀበለው፡፡
• ከ20 ዓመታት በፊት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የሬድዮ ኦፕሬተር ነበርኩ፡፡
• ጦርነቱ በርካታ ቀውሶችን አስከትሎ ነበር፡፡
• በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ለሁለት አስርት ዓመታት ሰላም አልነበረም፤ ሰዎች ተለያይተዋል፤ በርካታ ሰራዊት በሁለቱ አገራት ድንበር ላይ መሽጎ ነበር፡፡
• ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆንኩ በኋላ የሁለቱ አገራት ህዝቦች ልዩነት መቆም እንዳለበት ወሰንኩ፡፡
• ሁለቱ አገራት ጠላቶች እንዳልሆኑ ይልቁንስ ድህነት የጋራ ጠላታችን እንደሆነ አውቀን ለአገራቱ እና ለቀጠናው ብልፅግና መስራት ጀመርን፡፡
• መደመር አገር በቀል ሀሳብና የጋራ ብልጽግና ላይ ያተኮረ ፍልስፍና ነው፡፡
• የመደመር ጽንሰ ሀሳብ እንደ ዘር ውስጤ የበቀለው በኦሮሚያ ክልል በምትገኝ የትውልድ መንደሬ በሻሻ ውስጥ ነው፡፡
• በመደመር ጽንሰ ሀሳብ ውስጥ እኛና እነሱ የሚባል ነገር የለም፡፡
• ኢትዮጵያውያን በአንድነት በመቆማችን ለዓመታት ነፃ አገር ሆነን ቆይተናል፡፡
• የአፍሪካ ቀንድ የአሸባሪዎች ቀጠና እንዲሆን አንፈልግም፣ የሰላም ቀጠና እንጂ፡፡
• ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሰላም ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
• ለዴሞክራሲ ግንባታ መንገድ ዘርግተናል፤ በቅርቡ ነፃና ፍትሓዊ ምርጫ እናካሂደለን፡፡
• ለሁሉም ዜጎቿ እኩልነት መረጋገጥ አብረውኝ እንዲሰሩ ለኢትዮጵያውያን ጥሪ አቀርባለሁ፡፡
(ኢቢሲ)
• የኖርዌይ የኖቤል ኮሚቴ ለሰጠኝ እውቅና አመሰግናለሁ፡፡
• ለኢትዮ-ኤርትራ የሰላም ስምምነት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሰላም ቁርጠኝነት ወሳኝ ነበር፡፡
• ይህንን ሽልማት የአፍሪካ ህዝቦችና የዓለም ህዝቦችን ወክዬ ነው የምቀበለው፡፡
• ከ20 ዓመታት በፊት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የሬድዮ ኦፕሬተር ነበርኩ፡፡
• ጦርነቱ በርካታ ቀውሶችን አስከትሎ ነበር፡፡
• በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ለሁለት አስርት ዓመታት ሰላም አልነበረም፤ ሰዎች ተለያይተዋል፤ በርካታ ሰራዊት በሁለቱ አገራት ድንበር ላይ መሽጎ ነበር፡፡
• ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆንኩ በኋላ የሁለቱ አገራት ህዝቦች ልዩነት መቆም እንዳለበት ወሰንኩ፡፡
• ሁለቱ አገራት ጠላቶች እንዳልሆኑ ይልቁንስ ድህነት የጋራ ጠላታችን እንደሆነ አውቀን ለአገራቱ እና ለቀጠናው ብልፅግና መስራት ጀመርን፡፡
• መደመር አገር በቀል ሀሳብና የጋራ ብልጽግና ላይ ያተኮረ ፍልስፍና ነው፡፡
• የመደመር ጽንሰ ሀሳብ እንደ ዘር ውስጤ የበቀለው በኦሮሚያ ክልል በምትገኝ የትውልድ መንደሬ በሻሻ ውስጥ ነው፡፡
• በመደመር ጽንሰ ሀሳብ ውስጥ እኛና እነሱ የሚባል ነገር የለም፡፡
• ኢትዮጵያውያን በአንድነት በመቆማችን ለዓመታት ነፃ አገር ሆነን ቆይተናል፡፡
• የአፍሪካ ቀንድ የአሸባሪዎች ቀጠና እንዲሆን አንፈልግም፣ የሰላም ቀጠና እንጂ፡፡
• ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሰላም ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
• ለዴሞክራሲ ግንባታ መንገድ ዘርግተናል፤ በቅርቡ ነፃና ፍትሓዊ ምርጫ እናካሂደለን፡፡
• ለሁሉም ዜጎቿ እኩልነት መረጋገጥ አብረውኝ እንዲሰሩ ለኢትዮጵያውያን ጥሪ አቀርባለሁ፡፡
(ኢቢሲ)
ዶ/ር ዐብይ ፕሬዚደንት ኢሣያስ አፈወርቂ አወደሱ!
ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ የዓለም የሰላም ኖቤል ሽልማታቸውን ሲቀበሉ ባደረጉት ንግግር ፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ አወደሱ። «ይኽን ሽልማት የምቀበለው በኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ስም ነው።
በተለይ ደግሞ ለሰላም ሲሉ ከፍተኛውን መስዋእትነት በከፈሉት ስም። በተመሳሳይ ሽልማቱን የምቀበለው በአጋሬና የሰላም ጓድ በኾኑት ፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ ስም ነው» ብለዋል። ይኽ ንግግራቸውም ከታዳሚያን ሞቅ ያለጭብጨባ ታጅቧል። የፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ «መልካም ፈቃድ፣ እምነት እና ቁርጠኝነት ለኹለት ዐስርተ-ዓመታት በሃገሮቻችን መካከል የዘለቀው መቆራረጥ እንዲያበቃ ወሳኝ ነበር።»
በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ጦርነቱ ሲከፈት ወጣት እንደነበሩ የተናገሩት ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ፦ በጦርነት አውድማ «ወንድም ወንድሙን ሲገድል» መመልከታቸውን ገልጠዋል። የጦርነት መራራ ገጽታን፤ የሰላምን ወሳኝነት አጉልተው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጦርነት የተነሳ ለኹለት ዐሥርተ-ዓመታት ተለያይተው የነበሩ ቤተሰቦች መገናኘታቸውን፤ «ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሙሉ በሙሉ እንደ አዲስ መጀመሩንም» ጠቅሰዋል። የአየር እና የቴሌኮሙኒኬሽን ግንኙነት በኹለቱ ሃገራት መጀመሩንም በንግግራቸው አሰምተዋል።
More👇
https://telegra.ph/ETH-12-10-3
(DW)
@tikvahethiopiaBot tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ የዓለም የሰላም ኖቤል ሽልማታቸውን ሲቀበሉ ባደረጉት ንግግር ፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ አወደሱ። «ይኽን ሽልማት የምቀበለው በኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ስም ነው።
በተለይ ደግሞ ለሰላም ሲሉ ከፍተኛውን መስዋእትነት በከፈሉት ስም። በተመሳሳይ ሽልማቱን የምቀበለው በአጋሬና የሰላም ጓድ በኾኑት ፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ ስም ነው» ብለዋል። ይኽ ንግግራቸውም ከታዳሚያን ሞቅ ያለጭብጨባ ታጅቧል። የፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ «መልካም ፈቃድ፣ እምነት እና ቁርጠኝነት ለኹለት ዐስርተ-ዓመታት በሃገሮቻችን መካከል የዘለቀው መቆራረጥ እንዲያበቃ ወሳኝ ነበር።»
በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ጦርነቱ ሲከፈት ወጣት እንደነበሩ የተናገሩት ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ፦ በጦርነት አውድማ «ወንድም ወንድሙን ሲገድል» መመልከታቸውን ገልጠዋል። የጦርነት መራራ ገጽታን፤ የሰላምን ወሳኝነት አጉልተው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጦርነት የተነሳ ለኹለት ዐሥርተ-ዓመታት ተለያይተው የነበሩ ቤተሰቦች መገናኘታቸውን፤ «ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሙሉ በሙሉ እንደ አዲስ መጀመሩንም» ጠቅሰዋል። የአየር እና የቴሌኮሙኒኬሽን ግንኙነት በኹለቱ ሃገራት መጀመሩንም በንግግራቸው አሰምተዋል።
More👇
https://telegra.ph/ETH-12-10-3
(DW)
@tikvahethiopiaBot tikvahethiopia
የእንኳን ደስ አሎት እና የስጋት መልዕክት...
(ቲክቫህ ቤተሰቦች)
በቅድሚያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተ አብይ አህመድ የኖቤል የሰላም ተሸላሚ በመሆናቸው ከፍተኛ ክብር፣ ኩራት እና ደስታ ተሰምቶናል። ይህ ሽልማት ለሰላም እና ለዓለም አቀፍ ትብብር ላደረጉት ጥረት በተለይም ደግሞ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለዓመታት የዘለቀው የድንበር የይገባኛል ውዝግብ በሰላም እንዲፈታ ተነሳሽነትን በመውሰዶ የተበረከተ እንደሆነ እናምናለን።
በቀጠናው ላይ ያመጡትን ለውጥ እያደነቀን በአሁን ሰዓት እኛ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በእጅጉ ሀገራችን ያለችበት ሁኔታ እንደሚያሳስበን፣ በሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታም በከፍተኛ ሁኔታ እየተጨነቅን እንደሆነ ለመግለፅ እንወዳለን።
ሽልማቱ በሀገር ውስጥ የሚታየውን ምኑም ያልተጨበጠ ምስቅልቅል ያለውን የፖለቲካ ሁኔታ እንዲያጠሩ ተነሳሽነትን ይፈጥርሎታል ብለን እናምናለን። ሁሉም ዜጎች በእኩል ተስተናግደው እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎችም ትኩረት እየተሰጣቸው ሀገሪቱ እየሄደች ካለችበት አደገኛ አካሄድ ጊዜው ሳይረፍድ ለመመለስ ትልቅ ተነሳሽነት ይፈጥርሎታል ብለን እናምናለን።
ይህ ሽልማት በሀገራችን ላይ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣ የህግ የበላይነት እንዲከበር፣ የዜጎች በተለይም በአሁን ወቅት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ደህንነት እንዲጠበቅ፣ ህዝቡ ሰላም ወጥቶ ሰላም እንዲገባ፣ ወጣቱ እየሄደበት ካለው አደገኛ አካሄድ ቆም ብሎ እንዲያስብ፣ ጥፋተኞች ለህግ እንዲቀርቡ፣ በመንግስት ተገፍተናል የሚሉ አካላት ድምፃቸው ተሰምቶ እኩል ስለሀገራቸው እንዲጮሁ የማድረግ ስራ እንዲሰሩ መነሳሳት ይሆኖታል ብለን እናምናለን።
ሀገራችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ትሻለች!
በድጋሚ እንኳን ደስ አሎት!
(የቲክቫህ ቤተሰቦች የላኩት መልዕክት)
@tikvahethiopiaBot
(ቲክቫህ ቤተሰቦች)
በቅድሚያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተ አብይ አህመድ የኖቤል የሰላም ተሸላሚ በመሆናቸው ከፍተኛ ክብር፣ ኩራት እና ደስታ ተሰምቶናል። ይህ ሽልማት ለሰላም እና ለዓለም አቀፍ ትብብር ላደረጉት ጥረት በተለይም ደግሞ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለዓመታት የዘለቀው የድንበር የይገባኛል ውዝግብ በሰላም እንዲፈታ ተነሳሽነትን በመውሰዶ የተበረከተ እንደሆነ እናምናለን።
በቀጠናው ላይ ያመጡትን ለውጥ እያደነቀን በአሁን ሰዓት እኛ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በእጅጉ ሀገራችን ያለችበት ሁኔታ እንደሚያሳስበን፣ በሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታም በከፍተኛ ሁኔታ እየተጨነቅን እንደሆነ ለመግለፅ እንወዳለን።
ሽልማቱ በሀገር ውስጥ የሚታየውን ምኑም ያልተጨበጠ ምስቅልቅል ያለውን የፖለቲካ ሁኔታ እንዲያጠሩ ተነሳሽነትን ይፈጥርሎታል ብለን እናምናለን። ሁሉም ዜጎች በእኩል ተስተናግደው እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎችም ትኩረት እየተሰጣቸው ሀገሪቱ እየሄደች ካለችበት አደገኛ አካሄድ ጊዜው ሳይረፍድ ለመመለስ ትልቅ ተነሳሽነት ይፈጥርሎታል ብለን እናምናለን።
ይህ ሽልማት በሀገራችን ላይ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣ የህግ የበላይነት እንዲከበር፣ የዜጎች በተለይም በአሁን ወቅት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ደህንነት እንዲጠበቅ፣ ህዝቡ ሰላም ወጥቶ ሰላም እንዲገባ፣ ወጣቱ እየሄደበት ካለው አደገኛ አካሄድ ቆም ብሎ እንዲያስብ፣ ጥፋተኞች ለህግ እንዲቀርቡ፣ በመንግስት ተገፍተናል የሚሉ አካላት ድምፃቸው ተሰምቶ እኩል ስለሀገራቸው እንዲጮሁ የማድረግ ስራ እንዲሰሩ መነሳሳት ይሆኖታል ብለን እናምናለን።
ሀገራችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ትሻለች!
በድጋሚ እንኳን ደስ አሎት!
(የቲክቫህ ቤተሰቦች የላኩት መልዕክት)
@tikvahethiopiaBot
የሰብዓዊ መብት አያያዝ ቢሻሻልም የመንጋ ፍትህ ሌላ ፈተና ሆኗል!
በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ መስተካከል የሚገባቸው ጉዳዮች ቢኖሩም መሻሻል እየታየበት መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተቋማት ገለጹ። ከለውጡ በኋላ የተለያዩ ህጎች እየተሻሻሉ መምጣታቸው እንደመልካም አጋጣሚ ቢቆጠርም የመንጋ ፍትህ አሁንም ስጋት ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ71ኛ ጊዜ የሚከበረው የሰብዓዊ መብቶች ቀን ዛሬ በአዲስ አበባ ከሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ የሲቪክ ማህበራት ጋር ተከብሯል።
የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ህብረት ዋና ዳይሬክተር አቶ መስዑድ ገበየሁ እንዳሉት፤ ከለውጡ በኋላ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ተስፋ ሰጭ ጉዳዮች ይታያሉ።
መንግስት ለሰብዓዊ መብት አያያዝ እንቅፋት የሆኑ የህግ ማዕቀፎችን በማሻሻልና ተቋማትን በማደራጀት ብዙ ርቀት ሂዷል ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት በሰብዓዊ መብት ጉዳይ የተሰማሩ የሲቪክ ማህበራት እንደጠላት ይቆጠሩ እንደነበር ገልጸው፤ አሁን መንግስት ለውይይት በሩን ክፍት ማድረጉን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ አሁን ያለው አካሄድ በዜጎች ሰብዓዊ መብት ላይ አሉታዊም ሆነ አዎንታዊም አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። መንግስት ለሰብዓዊ መብት ትኩረት ሰጥቶ ተቋማትን ማደራጀቱና ህጎችን ማሻሻሉ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ የውስጥ መፈናቀል፤ የመንጋ ፍርድ፣ መንግስት ህግ ለማስከበር የሚያሳየው ዳተኝነት ለዜጎች ስጋት መሆኑን አስረድተዋል።
https://telegra.ph/ETH-12-10-4
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ መስተካከል የሚገባቸው ጉዳዮች ቢኖሩም መሻሻል እየታየበት መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተቋማት ገለጹ። ከለውጡ በኋላ የተለያዩ ህጎች እየተሻሻሉ መምጣታቸው እንደመልካም አጋጣሚ ቢቆጠርም የመንጋ ፍትህ አሁንም ስጋት ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ71ኛ ጊዜ የሚከበረው የሰብዓዊ መብቶች ቀን ዛሬ በአዲስ አበባ ከሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ የሲቪክ ማህበራት ጋር ተከብሯል።
የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ህብረት ዋና ዳይሬክተር አቶ መስዑድ ገበየሁ እንዳሉት፤ ከለውጡ በኋላ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ተስፋ ሰጭ ጉዳዮች ይታያሉ።
መንግስት ለሰብዓዊ መብት አያያዝ እንቅፋት የሆኑ የህግ ማዕቀፎችን በማሻሻልና ተቋማትን በማደራጀት ብዙ ርቀት ሂዷል ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት በሰብዓዊ መብት ጉዳይ የተሰማሩ የሲቪክ ማህበራት እንደጠላት ይቆጠሩ እንደነበር ገልጸው፤ አሁን መንግስት ለውይይት በሩን ክፍት ማድረጉን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ አሁን ያለው አካሄድ በዜጎች ሰብዓዊ መብት ላይ አሉታዊም ሆነ አዎንታዊም አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። መንግስት ለሰብዓዊ መብት ትኩረት ሰጥቶ ተቋማትን ማደራጀቱና ህጎችን ማሻሻሉ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ የውስጥ መፈናቀል፤ የመንጋ ፍርድ፣ መንግስት ህግ ለማስከበር የሚያሳየው ዳተኝነት ለዜጎች ስጋት መሆኑን አስረድተዋል።
https://telegra.ph/ETH-12-10-4
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ማሻሻያ በሚል ሰበብ ዜጎች መጎዳት የለባቸውም!
"መንግስት ችግሮች ሲፈጠሩ በመዋቅራዊ ለውጥ ላይ ስለሆንኩ ነው በሚል የሚያቀርበው ሰበብ ጊዜ ሊቀመጥለት ይገባል፤ ሁልጊዜ ማሻሻያ በሚል ሰበብ ዜጎች መጎዳት የለባቸውም፤ በመሆኑም መንግስት የመንጋ ፍርድ እንዲቆምና ዜጎች ሰብዓዊ መብታቸው ተከብሮ በነፃነት መንቀሳቀስ እንዲችሉ እኛም የበኩላችንን ሚና እንወጣለን።" - ሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ የሲቪክ ማህበራት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"መንግስት ችግሮች ሲፈጠሩ በመዋቅራዊ ለውጥ ላይ ስለሆንኩ ነው በሚል የሚያቀርበው ሰበብ ጊዜ ሊቀመጥለት ይገባል፤ ሁልጊዜ ማሻሻያ በሚል ሰበብ ዜጎች መጎዳት የለባቸውም፤ በመሆኑም መንግስት የመንጋ ፍርድ እንዲቆምና ዜጎች ሰብዓዊ መብታቸው ተከብሮ በነፃነት መንቀሳቀስ እንዲችሉ እኛም የበኩላችንን ሚና እንወጣለን።" - ሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ የሲቪክ ማህበራት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#EthiopianAirlines
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ አውሮፕላን ከመንደርደርያ ውጭ ተንሸራቶ መውጣቱ ተገለፀ። የበረራ ቁጥሩ ET357 የሆነው ይህ Q-400 አውሮፕላን ከደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ወደ አዲስ አበባ ለመነሳት ሲሞክር ዛሬ ከሰአት 11:15 ገደማ መንሸራተቱን አየር መንገዱ ገልፆ ማንም ተሳፋሪ ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ አረጋግጧል። የአየር ፀባዩ ነፋሻማ እና ዝናባማ እንደነበርም ተጠቁሟል።
(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikavhethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ አውሮፕላን ከመንደርደርያ ውጭ ተንሸራቶ መውጣቱ ተገለፀ። የበረራ ቁጥሩ ET357 የሆነው ይህ Q-400 አውሮፕላን ከደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ወደ አዲስ አበባ ለመነሳት ሲሞክር ዛሬ ከሰአት 11:15 ገደማ መንሸራተቱን አየር መንገዱ ገልፆ ማንም ተሳፋሪ ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ አረጋግጧል። የአየር ፀባዩ ነፋሻማ እና ዝናባማ እንደነበርም ተጠቁሟል።
(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikavhethiopiaBot @tikvahethiopia
*6880#
የአለርት ማዕከል በስልክ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት ታካሚዎች ወረፋ መያዝ እንደሚችሉ አስታወቀ። ታካሚዎች በእጅ ሥልኮቻቸው ወደ *6880# የጥሪ ማእከል በመደውል ባሉበት ቦታ ሆነው ወረፋ መያዝ እንደሚችሉ ማዕከሉ አስታውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአለርት ማዕከል በስልክ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት ታካሚዎች ወረፋ መያዝ እንደሚችሉ አስታወቀ። ታካሚዎች በእጅ ሥልኮቻቸው ወደ *6880# የጥሪ ማእከል በመደውል ባሉበት ቦታ ሆነው ወረፋ መያዝ እንደሚችሉ ማዕከሉ አስታውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize #AbiyAhemedAli
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከኦስሎ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ አቀባበል ሊደረግላቸው ነው። የዘንድሮው የሰላም ኖቤል አሸናፊ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ነገ ወደ አገራቸው ይመለሳሉ።
የአዲስ አበባ ከንቲባ ከደቂቃዎች በፊት በትዊተር ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ወደ አዲስ አበባ ሲመለሱ አቀባበል ይደረግላቸዋል።
ኢንጅነር ታከለ እንዳሉትም የአዲስ አበባ ህዝብ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ተገኝቶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቀባል እንዲያደርግላቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
(ETHIO FM 107.8)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከኦስሎ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ አቀባበል ሊደረግላቸው ነው። የዘንድሮው የሰላም ኖቤል አሸናፊ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ነገ ወደ አገራቸው ይመለሳሉ።
የአዲስ አበባ ከንቲባ ከደቂቃዎች በፊት በትዊተር ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ወደ አዲስ አበባ ሲመለሱ አቀባበል ይደረግላቸዋል።
ኢንጅነር ታከለ እንዳሉትም የአዲስ አበባ ህዝብ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ተገኝቶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቀባል እንዲያደርግላቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
(ETHIO FM 107.8)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Election2012
"ምርጫው በእርግጠኝነት ይካሄዳል!" - ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ (የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ)
ከኢቲቪ ጋር ቆይታ ያደረጉት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ቀጣዮ ሀገር አቀፍ ምርጫ በተቀመጠለት ጊዜ "በእርግጠኝነት ይካሄዳል" ብለዋል። ምርጫውን ለማከናወን ያለውን አጭር ጊዜ ታሳቢ በማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በፍጥነት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ተአማኒነትን የሚያጎድሉ ስህተቶች እንዳይኖሩም ጥንቃቄ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። ለምርጫው የሚያስፈልጉ አለም አቀፍ ግዢዎች እየተደረገ መሆኑንም ሰብሳቢዋ ገልፀዋል።
የሲዳማን ክልልነትን ለመወሰን የተደረገው ህዝበ ውሳኔ ለሀገር አቀፍ ምርጫው በርካታ ልምድ የተገኘበት እንደሆነም ጠቁመዋል። ምርጫ 2012 ነፃ፣ ተአማኒና ገለልተኛ እንዲሆን ቦርዱ ከቃል በላይ በተግባር ይሰራል ያሉት ወ/ሪት ብርቱካን ለዚህም ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል።
(ኢቲቪ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
"ምርጫው በእርግጠኝነት ይካሄዳል!" - ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ (የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ)
ከኢቲቪ ጋር ቆይታ ያደረጉት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ቀጣዮ ሀገር አቀፍ ምርጫ በተቀመጠለት ጊዜ "በእርግጠኝነት ይካሄዳል" ብለዋል። ምርጫውን ለማከናወን ያለውን አጭር ጊዜ ታሳቢ በማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በፍጥነት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ተአማኒነትን የሚያጎድሉ ስህተቶች እንዳይኖሩም ጥንቃቄ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። ለምርጫው የሚያስፈልጉ አለም አቀፍ ግዢዎች እየተደረገ መሆኑንም ሰብሳቢዋ ገልፀዋል።
የሲዳማን ክልልነትን ለመወሰን የተደረገው ህዝበ ውሳኔ ለሀገር አቀፍ ምርጫው በርካታ ልምድ የተገኘበት እንደሆነም ጠቁመዋል። ምርጫ 2012 ነፃ፣ ተአማኒና ገለልተኛ እንዲሆን ቦርዱ ከቃል በላይ በተግባር ይሰራል ያሉት ወ/ሪት ብርቱካን ለዚህም ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል።
(ኢቲቪ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ኢትዮጵያዊው የህግ ባለሙያ አቶ አምሃ መኮንን የዘንድሮውን የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ሽልማትን አሸነፉ!
ኢትዮጵያዊው የህግ ባለሙያና ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን የዘንድሮውን የፈረንሳይ ጀርመን የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ሽልማት አሸንፈዋል። ጠበቃ አምሃ መኮንን በኢትዮጵያ በነበረው አስቸጋሪ ወቅት እና ጊዜያት ሁሉ ለዜጎች ሰብዓዊ መብት እና ነጻነት መከበር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ነው ሽልማቱ የተበረከተላቸው።
ሽልማቱን የጀርመንና የፈረንሳይ አምባሳደሮች ያበረከቱት ሲሆን፥ በስነ ስርዓቱ ላይ ቤተሰቦቻቸው፣ ጓደኞቻቸው እና የሙያ ባልደረቦቻቸው ተገኝተዋል። የፈረንሣይ ጀርመን የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ሽልማት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታህሳስ 10 የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በዓለም ዙሪያ ለ15 የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የሚሰጥ ነው።
(ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኢትዮጵያዊው የህግ ባለሙያና ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን የዘንድሮውን የፈረንሳይ ጀርመን የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ሽልማት አሸንፈዋል። ጠበቃ አምሃ መኮንን በኢትዮጵያ በነበረው አስቸጋሪ ወቅት እና ጊዜያት ሁሉ ለዜጎች ሰብዓዊ መብት እና ነጻነት መከበር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ነው ሽልማቱ የተበረከተላቸው።
ሽልማቱን የጀርመንና የፈረንሳይ አምባሳደሮች ያበረከቱት ሲሆን፥ በስነ ስርዓቱ ላይ ቤተሰቦቻቸው፣ ጓደኞቻቸው እና የሙያ ባልደረቦቻቸው ተገኝተዋል። የፈረንሣይ ጀርመን የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ሽልማት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታህሳስ 10 የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በዓለም ዙሪያ ለ15 የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የሚሰጥ ነው።
(ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጎንደር ከተማ የደረሰ እሳት ቃጠሎ በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ!
- በጎንደር ከተማ አዘዞ ቀበሌ 19 ትናንት ምሽት በደረሰ የእሳት ቃጠሎ በ3 የእህል ወፍጮ ቤቶችና በአራት ጊዚያዊ የእህል መጋዘኖች ላይ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ተመልክቷል።
የከተማው ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት አስተባባሪ ምክትል ኮማንደር አበበ አለባቸው እንዳሉት ቃጠሎው የደረሰው በከተማው የአውቶብስ መናኸሪያ አጠገብ በሚገኙ ጊዚያዊ የገበያ ስፍራ አጠገብ ነው፡፡
ምሽት አራት ሰዓት ተኩል አካባቢ በተነሳው የእሳት ቃጠሎ ሶስት የእህል ወፍጮ ቤቶችና አራት ጊዚያዊ የእህል መጋዘኖች ለጊዜው ግምታቸው ካልታወቁ ንብረቶች ጋር ወድመዋል፡፡ ለአንድ ሰዓት የዘለቀውን የእሳት ቃጠሎ ለመቆጣጠር የአከባቢው ወጣቶችን ሌላም የህብረተሰብ ክፍል ከከተማው እሳት አደጋ መከላከያ ጋር በመሆን ርብብር ማድረጋቸውን ምክትል ኮማንደሩ ገልጸዋል፡፡
በዚህም ቃጠሎውን መቆጣጠር መቻሉን ጠቁመው እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ ላይ ተሳታፊ የነበሩ ሁለት ሰዎች በጭሽ የመታፈን ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ መደረጉን አመልክተዋል። ምክትል ኮማንደሩ እንደተናገሩት ቃጠሎው በሰው ሕይወት ላይ ያደረሰው ጉዳት የለም፡፡ ፖሊስ ቃጠሎው ያደረሰውን የንብረት ውድመትና የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት የምርመራ ስራ መጀመሩንም አብራርተዋል፡፡
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
- በጎንደር ከተማ አዘዞ ቀበሌ 19 ትናንት ምሽት በደረሰ የእሳት ቃጠሎ በ3 የእህል ወፍጮ ቤቶችና በአራት ጊዚያዊ የእህል መጋዘኖች ላይ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ተመልክቷል።
የከተማው ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት አስተባባሪ ምክትል ኮማንደር አበበ አለባቸው እንዳሉት ቃጠሎው የደረሰው በከተማው የአውቶብስ መናኸሪያ አጠገብ በሚገኙ ጊዚያዊ የገበያ ስፍራ አጠገብ ነው፡፡
ምሽት አራት ሰዓት ተኩል አካባቢ በተነሳው የእሳት ቃጠሎ ሶስት የእህል ወፍጮ ቤቶችና አራት ጊዚያዊ የእህል መጋዘኖች ለጊዜው ግምታቸው ካልታወቁ ንብረቶች ጋር ወድመዋል፡፡ ለአንድ ሰዓት የዘለቀውን የእሳት ቃጠሎ ለመቆጣጠር የአከባቢው ወጣቶችን ሌላም የህብረተሰብ ክፍል ከከተማው እሳት አደጋ መከላከያ ጋር በመሆን ርብብር ማድረጋቸውን ምክትል ኮማንደሩ ገልጸዋል፡፡
በዚህም ቃጠሎውን መቆጣጠር መቻሉን ጠቁመው እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ ላይ ተሳታፊ የነበሩ ሁለት ሰዎች በጭሽ የመታፈን ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ መደረጉን አመልክተዋል። ምክትል ኮማንደሩ እንደተናገሩት ቃጠሎው በሰው ሕይወት ላይ ያደረሰው ጉዳት የለም፡፡ ፖሊስ ቃጠሎው ያደረሰውን የንብረት ውድመትና የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት የምርመራ ስራ መጀመሩንም አብራርተዋል፡፡
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#BetaSamati
በቅድመ ሮም የነበረች ጥንታዊት ከተማ ኢትዮጵያ ውስጥ ተገኘች!
የቅሪተ አካል ተመራማሪዎች ከ1400 ዓመታት በፊት የነበረች ከተማ ኢትዮጵያ ውስጥ በቁፋሮ ማግኘታቸው ታወቀ። ከተማዋ በምሥራቅ አፍሪካ ገናና የነበረው እና እንደ ሮማ ግዛተ አጼ ከመሳሰሉ ኃያላን ጋር የንግድ ግንኙነት የነበረው የጥንታዊ አክሱም ግዛት አካል የነበረች መሆኗም ተጠቅሷል።
በአሜሪካን አገር ሜሪላንድ ግዛት ባልቲሞር በሚገኘው የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ የሆኑት ሚካኤል ሃሮወር “ይህ ስፍራ ከቀደምት ሥልጣኔዎች አንዱ ነው፤ ነገር ግን ሰዎች ስለ ስፍራው የሚያውቁት ነገር የለም። ከግብጽ እና ሱዳን ውጭ ይህ ስፍራ ቀደምት የአፍሪካ ታላቅ ሥልጣኔ የነበረበት ኅብረተሰብ መገኛ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
https://www.newscientist.com/article/2226803-lost-ethiopian-town-comes-from-a-forgotten-empire-that-rivalled-rome/
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በቅድመ ሮም የነበረች ጥንታዊት ከተማ ኢትዮጵያ ውስጥ ተገኘች!
የቅሪተ አካል ተመራማሪዎች ከ1400 ዓመታት በፊት የነበረች ከተማ ኢትዮጵያ ውስጥ በቁፋሮ ማግኘታቸው ታወቀ። ከተማዋ በምሥራቅ አፍሪካ ገናና የነበረው እና እንደ ሮማ ግዛተ አጼ ከመሳሰሉ ኃያላን ጋር የንግድ ግንኙነት የነበረው የጥንታዊ አክሱም ግዛት አካል የነበረች መሆኗም ተጠቅሷል።
በአሜሪካን አገር ሜሪላንድ ግዛት ባልቲሞር በሚገኘው የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ የሆኑት ሚካኤል ሃሮወር “ይህ ስፍራ ከቀደምት ሥልጣኔዎች አንዱ ነው፤ ነገር ግን ሰዎች ስለ ስፍራው የሚያውቁት ነገር የለም። ከግብጽ እና ሱዳን ውጭ ይህ ስፍራ ቀደምት የአፍሪካ ታላቅ ሥልጣኔ የነበረበት ኅብረተሰብ መገኛ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
https://www.newscientist.com/article/2226803-lost-ethiopian-town-comes-from-a-forgotten-empire-that-rivalled-rome/
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በትራፊክ አደጋ 2 ሰዎች ሲሞቱ በ17 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት ደረሰ!
በትግራይ ደቡባዊ ዞን ከማይጨው ከተማ ወደ ነቅሰገ ሲጓዝ የነበረው መኪና ተገልብጦ ሁለት ሰዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ በ17 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ ገለፀ።
በዞኑ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ደህንነት ቁጥጥርና አጣሪ ምክትል ዳይሬክተር ኮማንደር አብረሃ ወረደ እንደገለፁት 19 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ የተገለበጠው ነቅሰገ ከተማ መግቢያ አካባቢ ነው።
ትናንት ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ በደረሰው አደጋ 2 ሰዎች ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ ሾፌሩን ጨምሮ በ17 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ኮማንደሩ ተናግረዋል። ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 17 ሰዎች በማይጨው ሆስፒታልና በማይጨው ጤና ጣቢያ በህክምና ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 ትግ 06605 የሆነው ሚኒባስ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ 11 ሰዎች መጫን ሲገባው ትርፍ ጭኖ በመጓዝ ላይ እንዳለ መገልበጡን ገልፀዋል። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ነው ያሉት ኮማንደሩ የትራፊክ አደጋ በየጊዜው እየጨመረ የበርካታ ወገኖች ህይወት እየቀጠፈና የአገርና የህዝብ ንብረት እያወደመ በመሆኑ አሽርካሪዎች በጥንቃቄ እንዲጓዙ አሳስበዋል።
(ኢዜአ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በትግራይ ደቡባዊ ዞን ከማይጨው ከተማ ወደ ነቅሰገ ሲጓዝ የነበረው መኪና ተገልብጦ ሁለት ሰዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ በ17 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ ገለፀ።
በዞኑ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ደህንነት ቁጥጥርና አጣሪ ምክትል ዳይሬክተር ኮማንደር አብረሃ ወረደ እንደገለፁት 19 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ የተገለበጠው ነቅሰገ ከተማ መግቢያ አካባቢ ነው።
ትናንት ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ በደረሰው አደጋ 2 ሰዎች ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ ሾፌሩን ጨምሮ በ17 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ኮማንደሩ ተናግረዋል። ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 17 ሰዎች በማይጨው ሆስፒታልና በማይጨው ጤና ጣቢያ በህክምና ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 ትግ 06605 የሆነው ሚኒባስ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ 11 ሰዎች መጫን ሲገባው ትርፍ ጭኖ በመጓዝ ላይ እንዳለ መገልበጡን ገልፀዋል። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ነው ያሉት ኮማንደሩ የትራፊክ አደጋ በየጊዜው እየጨመረ የበርካታ ወገኖች ህይወት እየቀጠፈና የአገርና የህዝብ ንብረት እያወደመ በመሆኑ አሽርካሪዎች በጥንቃቄ እንዲጓዙ አሳስበዋል።
(ኢዜአ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ነገሮችን ማድበስበስ ሊቆም ይገባል...
በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እየታዩ ያሉት እንቅስቃሴዎች እጅግ አደገኛ ለሀገር ህልውናም አስጊ እንደሆኑ ደጋግመን ሳንሰለች እየገለፅን ነው። ሁሉን አሳታፊ ውይይት ተደርጎ፣ ከምንም ነገር የነፃ እውነተኛ እርቅ ወርዶ፣ ተማሪው ይቅርታ ተጠያይቆ፣ ከኃላፊዎች ጀምሮ ጥፋተኞች ካሉ በአግባቡ ተጠይቀው፣ የተጎዱ ተማሪዎች ተክሰው፣ ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱትም በክብር ተመልሰው፣ ወንድም ወንድሙን አቅፎ ተቀብሎ የትምህርት ስርዓቱ በአስተማማኝ ሁኔታ ውስጥ ማስቀጠል ካልተቻል፤
ተማሪዎች እያነሷቸው ላሉት ጥያቄዎች በክብር አዳምጦ ምላሽ መስጠት የማይቻል ከሆነ፣ ለተማሪ ሞት፣ ለአካል ጉዳት፣ ግቢ ጥሎ መውጣት ፣ መሰቃየት፣ ምክንያት የሆኑ፣ አካላት በግልፅ በህዝብ ፊት እስካልተጠየቁ ድረስ መሰል ችግሮች ዳግም ላለመከሰታቸው አሁንም እየተከሰቱ ያሉ አሳዛኝ ክስተቶች ላለመቀጠላቸው ምንም ዋስትና የለም። የሀገሪቱ መንግስት የሚታዩትን ምልክቶች እንደቀላል ነገር ከመቁጠር፣ እንዲሁም እያድበሰበሰ ከማለፍ ይልቅ ችግሩ ነገ ሀገር ሊያሳጣን የሚችል እንደሆነ ታምኖ ሳይውል ሳያድር መፍትሄ ቢፈልግ መልካም ነው።
አጥፊዎች፣ የግጭት አቀናባሪዎች በግልፅ ታውቀው እስካልተጠየቁ፣ የተማሪዎች ጥያቄ ምንድነው ብሎ በመጠየቅ ለመፍታት ካልተሰራ፣ እውነተኛ እርቅ እና ሰላም እንዲወርድ ከፖለቲካ የነፃ ተግባራዊ ስራ ካልተሰራ፣ ዜጎች በሀገሪቱ መንግስት ላይ ያላቸው እምነት እየተሸረሸረ እየሄደ እንደሆነ እየታዘብን ነው። በ ሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች፣ ልጆቻቸውን በግፍ ያጡ ምስኪን ወላጆች ዛሬም ፍትህ የታለች እያሉ ነው። ግጭት ሸሽተው በየቤታቸው የተቀመጡ ሀገር ተረካቢ ወጣቶች መፍትሄ፣ ሰላም እንደሚገልጉ እየገለፁ ነው።
የሚሰማን መንግስት ካለ አሁንም ጥሪ እናቀርባለን!
@tikvahethiopiaBot
በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እየታዩ ያሉት እንቅስቃሴዎች እጅግ አደገኛ ለሀገር ህልውናም አስጊ እንደሆኑ ደጋግመን ሳንሰለች እየገለፅን ነው። ሁሉን አሳታፊ ውይይት ተደርጎ፣ ከምንም ነገር የነፃ እውነተኛ እርቅ ወርዶ፣ ተማሪው ይቅርታ ተጠያይቆ፣ ከኃላፊዎች ጀምሮ ጥፋተኞች ካሉ በአግባቡ ተጠይቀው፣ የተጎዱ ተማሪዎች ተክሰው፣ ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱትም በክብር ተመልሰው፣ ወንድም ወንድሙን አቅፎ ተቀብሎ የትምህርት ስርዓቱ በአስተማማኝ ሁኔታ ውስጥ ማስቀጠል ካልተቻል፤
ተማሪዎች እያነሷቸው ላሉት ጥያቄዎች በክብር አዳምጦ ምላሽ መስጠት የማይቻል ከሆነ፣ ለተማሪ ሞት፣ ለአካል ጉዳት፣ ግቢ ጥሎ መውጣት ፣ መሰቃየት፣ ምክንያት የሆኑ፣ አካላት በግልፅ በህዝብ ፊት እስካልተጠየቁ ድረስ መሰል ችግሮች ዳግም ላለመከሰታቸው አሁንም እየተከሰቱ ያሉ አሳዛኝ ክስተቶች ላለመቀጠላቸው ምንም ዋስትና የለም። የሀገሪቱ መንግስት የሚታዩትን ምልክቶች እንደቀላል ነገር ከመቁጠር፣ እንዲሁም እያድበሰበሰ ከማለፍ ይልቅ ችግሩ ነገ ሀገር ሊያሳጣን የሚችል እንደሆነ ታምኖ ሳይውል ሳያድር መፍትሄ ቢፈልግ መልካም ነው።
አጥፊዎች፣ የግጭት አቀናባሪዎች በግልፅ ታውቀው እስካልተጠየቁ፣ የተማሪዎች ጥያቄ ምንድነው ብሎ በመጠየቅ ለመፍታት ካልተሰራ፣ እውነተኛ እርቅ እና ሰላም እንዲወርድ ከፖለቲካ የነፃ ተግባራዊ ስራ ካልተሰራ፣ ዜጎች በሀገሪቱ መንግስት ላይ ያላቸው እምነት እየተሸረሸረ እየሄደ እንደሆነ እየታዘብን ነው። በ ሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች፣ ልጆቻቸውን በግፍ ያጡ ምስኪን ወላጆች ዛሬም ፍትህ የታለች እያሉ ነው። ግጭት ሸሽተው በየቤታቸው የተቀመጡ ሀገር ተረካቢ ወጣቶች መፍትሄ፣ ሰላም እንደሚገልጉ እየገለፁ ነው።
የሚሰማን መንግስት ካለ አሁንም ጥሪ እናቀርባለን!
@tikvahethiopiaBot
“መፍትሄ የሚገኘው ወንጀለኛን በመቅጣት ብቻ ሳይሆን፣ ህግና ደንብን በማስተማር ጭምር ነው” - ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ (የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት)
.
.
የጠቅላይ ፍርድቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ መአዛ አሸናፊ በትላንትናው ዕለት ዓለማቀፍ የሰብአዊ መብት ቀንን ምክንያት በማድረግ ከዳግማዊ ምኒሊክ መሰናዶ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጋር በተደረገው የውይይት መድረክ ላይ እንዳሉት በፍትህ ዘርፉ ስኬት የሚገኘው ወንጀለኛን በመቅጣት ብቻ ሳይሆን ህግና ደንብን በማስተማር በተለይ ደግሞ በታዳጊዎች ላይ መብትና ግዴታቸውን አውቀው እንዲያድጉ በማደረግ ነው።
በመሆኑም ይላሉ ወይዘሮ መዓዛ ጠቅላይ ፍርድቤት የፍትህ ዘርፉ የሚስተዋልበትን ችግሮች መቅረፍ እንዲችል ታዳጊዎች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት ላይ ነው። መብት እና ግዴታውን ያወቀ ህብረተሰብ ለመገንባት ጠንክሮ መሰራት ያለበት መሰረቱ ላይ እንደሆነ ፕሬዚዳንቷ አጽዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል።
መብቱን ብቻ ሳይሆን ግዴታውን ያወቀ ህብረተሰብ መገንባት ካልተቻለ የዳኝነት ስራውን ከባድ ያደርገዋል ያሉት ፕሬዝዳንቷ ትውልድን ለመገንባትም መስርያ ቤታቸው በወጣቶች ላይ በተለይም ተማሪዎች ላይ ትኩረት በመስጠት ይሰራል፡፡ በመድረኩ 500 የዳግማዊ ምኒሊክ መሰናዶ ትምህርትቤት ተማሪዎች ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን ጠቅላይ ፍርድቤት የሰብአዊ መብት ቀንን ምክንያት በማድረግ በተመሳሳይ በሌሎች ሶስት ትምህርት ቤቶች ላይ ቀጣይ መድረክ ይኖረዋል።
(EPA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
.
.
የጠቅላይ ፍርድቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ መአዛ አሸናፊ በትላንትናው ዕለት ዓለማቀፍ የሰብአዊ መብት ቀንን ምክንያት በማድረግ ከዳግማዊ ምኒሊክ መሰናዶ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጋር በተደረገው የውይይት መድረክ ላይ እንዳሉት በፍትህ ዘርፉ ስኬት የሚገኘው ወንጀለኛን በመቅጣት ብቻ ሳይሆን ህግና ደንብን በማስተማር በተለይ ደግሞ በታዳጊዎች ላይ መብትና ግዴታቸውን አውቀው እንዲያድጉ በማደረግ ነው።
በመሆኑም ይላሉ ወይዘሮ መዓዛ ጠቅላይ ፍርድቤት የፍትህ ዘርፉ የሚስተዋልበትን ችግሮች መቅረፍ እንዲችል ታዳጊዎች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት ላይ ነው። መብት እና ግዴታውን ያወቀ ህብረተሰብ ለመገንባት ጠንክሮ መሰራት ያለበት መሰረቱ ላይ እንደሆነ ፕሬዚዳንቷ አጽዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል።
መብቱን ብቻ ሳይሆን ግዴታውን ያወቀ ህብረተሰብ መገንባት ካልተቻለ የዳኝነት ስራውን ከባድ ያደርገዋል ያሉት ፕሬዝዳንቷ ትውልድን ለመገንባትም መስርያ ቤታቸው በወጣቶች ላይ በተለይም ተማሪዎች ላይ ትኩረት በመስጠት ይሰራል፡፡ በመድረኩ 500 የዳግማዊ ምኒሊክ መሰናዶ ትምህርትቤት ተማሪዎች ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን ጠቅላይ ፍርድቤት የሰብአዊ መብት ቀንን ምክንያት በማድረግ በተመሳሳይ በሌሎች ሶስት ትምህርት ቤቶች ላይ ቀጣይ መድረክ ይኖረዋል።
(EPA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰኔ 15ቱ የባለሥልጣናት ግድያ ተከሳሾች መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ለታኅሣሥ 21 ቀጠሮ ሰጠ፡፡
ለታኅሣሥ 1 ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ 4ኛ ወንጀል ችሎት በእነ አስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ መዝገብ የተከሰሱትን ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች የክስ መቃወሚያ ተቀብሏል፡፡
የአብን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ክርስቲያን ታደለ የሚገኙበት የዚሁ መዝገብ ተከሳሾች በዐቃቤ ሕግ የቀረበባቸውን ክስ መሰረት በማድረግ የክስ መቃወሚያቸውን ለፍርድ ቤቱ አቅርበዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም የክስ መቃወሚያቸውን ተቀብሎ ዐቃቤ ሕግ ለቀረበው የክስ መቃወሚያ መልስ እንዲያዘጋጅ ያዘዘ ሲሆን፤ የክስ መዝገቡን እና መቃወሚያውን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለታኅሣሥ 21/2012 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
(AHADUTV)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰኔ 15ቱ የባለሥልጣናት ግድያ ተከሳሾች መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ለታኅሣሥ 21 ቀጠሮ ሰጠ፡፡
ለታኅሣሥ 1 ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ 4ኛ ወንጀል ችሎት በእነ አስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ መዝገብ የተከሰሱትን ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች የክስ መቃወሚያ ተቀብሏል፡፡
የአብን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ክርስቲያን ታደለ የሚገኙበት የዚሁ መዝገብ ተከሳሾች በዐቃቤ ሕግ የቀረበባቸውን ክስ መሰረት በማድረግ የክስ መቃወሚያቸውን ለፍርድ ቤቱ አቅርበዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም የክስ መቃወሚያቸውን ተቀብሎ ዐቃቤ ሕግ ለቀረበው የክስ መቃወሚያ መልስ እንዲያዘጋጅ ያዘዘ ሲሆን፤ የክስ መዝገቡን እና መቃወሚያውን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለታኅሣሥ 21/2012 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
(AHADUTV)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert
(Elias Meseret)
ይህ "ዛሬ ጠዋት ፕሬዝደንት ኢሳያስ ጠ/ሚር አብይ ልዩ ሰው ነው አሉ፣ እሱን በቃላት ለመግለፅ ይከብዳል ብለው ለጋዜጠኞች ተናገሩ" እየተባለ በብዛት ሼር እየተደረገ ያለ ነገር የሀሰት ነው። ብዙ ተከታይ ያላቸው ግለሰቦች፣ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲህም የሚድያ ሰዎች የሀሰት መረጃ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ላለማሰራጨት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(Elias Meseret)
ይህ "ዛሬ ጠዋት ፕሬዝደንት ኢሳያስ ጠ/ሚር አብይ ልዩ ሰው ነው አሉ፣ እሱን በቃላት ለመግለፅ ይከብዳል ብለው ለጋዜጠኞች ተናገሩ" እየተባለ በብዛት ሼር እየተደረገ ያለ ነገር የሀሰት ነው። ብዙ ተከታይ ያላቸው ግለሰቦች፣ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲህም የሚድያ ሰዎች የሀሰት መረጃ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ላለማሰራጨት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia