አሳዛኝ ዜና!
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ በቤት ዉስጥ የተቀመጠ ቦምብ ፈንድቶ አንድ የሶሰት ዓመት ህጻን ሲገድል በአራት ህጻናት ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ማድረሱ ተገለጸ።
የምስራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት አስተባባሪ ዋና ኢንስፔክተር ጎበዜ ይርሳዉ እንዳሉት በደብረ ኤልያስ ወረዳ ጥጃ ጎጠር የጠንጠር ቀበሌ ዛሬ ከቀኑ 8.00 ሰዓት በአቶ ጌታሁን የኋላዉ ቤት ዉስጥ ተቀምጦ የነበረን የጣሊያን ቦንብ ልጆች ሲነካኩ በመፈንዳቱ ምክንያት በልጆች ላይ ጉዳት አድርሷል።
በጉዳቱ የሶስት አመት ህጻን ህይወቷ ወዲያዉኑ ሲያልፋ እድሚያቸዉ ከሶስት ወር እስከ ሃያ አመት የሆኑ አራት የአንድ ቤተሰብ ልጆች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ በደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል እየተረዱ ነዉ።
ህዝቡ በቤት ዉስጥ ያስቀመጠዉ ቦሞብ ካለ በሰዉ ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ከማድረሱ በፊት ለመንግስት ገቢ እንዲያደርጉም ዋና ኢንስፔክተር ጎበዜ ይርሳዉ ማሳሰባቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
Via Machakel Woreda Government Communication/ETHIO-FM/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ በቤት ዉስጥ የተቀመጠ ቦምብ ፈንድቶ አንድ የሶሰት ዓመት ህጻን ሲገድል በአራት ህጻናት ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ማድረሱ ተገለጸ።
የምስራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት አስተባባሪ ዋና ኢንስፔክተር ጎበዜ ይርሳዉ እንዳሉት በደብረ ኤልያስ ወረዳ ጥጃ ጎጠር የጠንጠር ቀበሌ ዛሬ ከቀኑ 8.00 ሰዓት በአቶ ጌታሁን የኋላዉ ቤት ዉስጥ ተቀምጦ የነበረን የጣሊያን ቦንብ ልጆች ሲነካኩ በመፈንዳቱ ምክንያት በልጆች ላይ ጉዳት አድርሷል።
በጉዳቱ የሶስት አመት ህጻን ህይወቷ ወዲያዉኑ ሲያልፋ እድሚያቸዉ ከሶስት ወር እስከ ሃያ አመት የሆኑ አራት የአንድ ቤተሰብ ልጆች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ በደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል እየተረዱ ነዉ።
ህዝቡ በቤት ዉስጥ ያስቀመጠዉ ቦሞብ ካለ በሰዉ ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ከማድረሱ በፊት ለመንግስት ገቢ እንዲያደርጉም ዋና ኢንስፔክተር ጎበዜ ይርሳዉ ማሳሰባቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
Via Machakel Woreda Government Communication/ETHIO-FM/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የህዳሴ ግድብን እየጎበኙ ይገኛሉ!
የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ዛሬ (መስከረም 14 ቀን 2012 ዓ.ም) ታላቁ የኢትየጵያ ህዳሴ ግድብን በመጎብኘት ላይ ናቸው።
የአባይን ወንዝ በተመለከተ እ ኤ አ የ1959 ስምምነት ተቀባይነት እንደሌለው ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂነር የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከጎበኙ ብኋላ ገልጸዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ግድቡ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ተጽዕኖዎችን ለማሳደር የሚደረጉ መሯሯጦች መኖራቸውን አስታውሰው ይሁንና መንግስት ከተፋሰሱ አገራት ጋር በመነጋገር ችግሮችን እየፈታ ነው ብለዋል።
ከግብጽ በኩል ሰሞኑን እየተራገበ ያለው ነገር በምን ምክንያት እንደተነሳ እንደማያውቁ የገለጹት ሚኒስትሩ አዲስ የሰራነው ነገር የለም የውኃ ሙሌቱንም በተመለከተ በምን አኳኋን መካሄድ እንዳለበት ከታችኛው ተፋሰስ አገሮች ጋር ተነጋግረን ተስማምተናል ብለዋል።
ውኃ በብዛት በሚኖርበትና ውኃ በሚቀንስበት ወቅት አሞላሉ ምን መምሰል እንዳለበት ከታችኛው የተፋሰስ አገራቱ ጋር ንግግር መደረጉን የገለጹት ሚኒስትሩ ሙሌቱ በእነርሱ ላይ ተጽዕኖ በማይኖረው መልኩ እንደሚከናወን ግብጽም ሆነች ሱዳን ጠንቅቀው ያውቃሉ ብለዋል።
ሰሞኑን በግብጽ ሚዲያዎች የሚራገቡ ነገሮች መነሻቸው ምን አልባት ከሌሎች ነገሮች ጋር የተያያዙ ሊሆኑ ይችላሉ ሲሉ ሚኒስትሩ ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
Via #EPA
Photo: EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ዛሬ (መስከረም 14 ቀን 2012 ዓ.ም) ታላቁ የኢትየጵያ ህዳሴ ግድብን በመጎብኘት ላይ ናቸው።
የአባይን ወንዝ በተመለከተ እ ኤ አ የ1959 ስምምነት ተቀባይነት እንደሌለው ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂነር የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከጎበኙ ብኋላ ገልጸዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ግድቡ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ተጽዕኖዎችን ለማሳደር የሚደረጉ መሯሯጦች መኖራቸውን አስታውሰው ይሁንና መንግስት ከተፋሰሱ አገራት ጋር በመነጋገር ችግሮችን እየፈታ ነው ብለዋል።
ከግብጽ በኩል ሰሞኑን እየተራገበ ያለው ነገር በምን ምክንያት እንደተነሳ እንደማያውቁ የገለጹት ሚኒስትሩ አዲስ የሰራነው ነገር የለም የውኃ ሙሌቱንም በተመለከተ በምን አኳኋን መካሄድ እንዳለበት ከታችኛው ተፋሰስ አገሮች ጋር ተነጋግረን ተስማምተናል ብለዋል።
ውኃ በብዛት በሚኖርበትና ውኃ በሚቀንስበት ወቅት አሞላሉ ምን መምሰል እንዳለበት ከታችኛው የተፋሰስ አገራቱ ጋር ንግግር መደረጉን የገለጹት ሚኒስትሩ ሙሌቱ በእነርሱ ላይ ተጽዕኖ በማይኖረው መልኩ እንደሚከናወን ግብጽም ሆነች ሱዳን ጠንቅቀው ያውቃሉ ብለዋል።
ሰሞኑን በግብጽ ሚዲያዎች የሚራገቡ ነገሮች መነሻቸው ምን አልባት ከሌሎች ነገሮች ጋር የተያያዙ ሊሆኑ ይችላሉ ሲሉ ሚኒስትሩ ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
Via #EPA
Photo: EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA | ኢንጂነር ስለሺ_በቀለ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ ዛሬ በጎበኙበት ወቅት የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) #አጓትቶት የነበረው የኤሌክትሮ ሜካኒካል እና የብረታ ብረት ሥራ ለአምስት ዓለም አቀፍ ኮንትራክተሮች ከተሰጠ ወዲህ ስራው በጥሩ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ገልፀዋል። በዚህም ምክንያት ሳሊኒ ከዚህ በፊት አቁሞት የነበረው የሲቪል ሥራ(በተለይ በግድቡ የመሃል ክፍል ላይ አርማታ የመሙላት ሥራ)አሁን መጀመሩን ተናግረዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ አሁን ያለበት ሁኔታ፦
• ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በመጪው ዓመት አጋማሽ በኃላ ወደ ኃይል ማመንጨት ይሸጋገራል፣
• በቅድሚያ ኃይል የሚያመነጩት ዩኒት 9 እና 10 ሲሆኑ አሁን ላይ የሁለቱ ዩኒት አፈጻጸም 50 በመቶ ደርሷል፣
• የዋናው ግድብ የኮንክሪት ግድብ ይወስዳል ተብሎ ከተገመተው 10 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውስጥ ከ8 ሚሊዮን በላይ የኮንክሪት ሙሊት ተከናውኗል፤ አፈጻጸሙም ከ80.4 በመቶ ነው፣
• የኮርቻ ቅርፅ ግድቡ ግንባታ አፈጻጸም 96 በመቶ ተጠናቋል፣
• ለቅድመ ማመንጨት ሥራው የሚያስፈልጉ ተርባይኖች የሚገጠሙበት የስፓይራል ኬዝ ተከላ እና የብየዳ ስራ በጥራት በመከናወን ላይ ነው፣
• በግድቡ የግራ ክፍል ግድቡን ከባህር ጠለል በላይ 560 ሜትር ከፍታ ላይ ለማድረስ 26 ሺህ ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት ተሞልቷል፣ በቀሪው የግድቡ ክፍል ላይ ደግሞ 50 ሺህ ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት የመሙላት ሥራ እየተከናወነ ነው፤
• ለታችኛው የውሃ ማስተንፈሻ (ቦተም አውትሌት) ሥራ የሚያስፈልገውን ማቴሪያል ከውጭ ሃገር በማስገባት በሳይት ላይ የምርት ሥራ ተጀምሯል፣
• በአሁኑ ሰዓት የጎርፍ ማስተንፈሻ 96 በመቶ፣ የኃይል ማመንጫ ክፍል 70 በመቶ እንዲሁም የዋናው ግድብ የኮንክሪት ሙሌት 80 በመቶ ተጠናቋል፣
• ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ሥራው በ2003 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን ዓመታዊ አማካይ የኃይል ምርት አቅሙም 15,670 ጊጋ ዋት ሰዓት ነው፣
• ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም አሁን ላይ 68 ነጥብ 3 በመቶ ደረሷል።
ምንጭ፦ ኢፕድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
• ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በመጪው ዓመት አጋማሽ በኃላ ወደ ኃይል ማመንጨት ይሸጋገራል፣
• በቅድሚያ ኃይል የሚያመነጩት ዩኒት 9 እና 10 ሲሆኑ አሁን ላይ የሁለቱ ዩኒት አፈጻጸም 50 በመቶ ደርሷል፣
• የዋናው ግድብ የኮንክሪት ግድብ ይወስዳል ተብሎ ከተገመተው 10 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውስጥ ከ8 ሚሊዮን በላይ የኮንክሪት ሙሊት ተከናውኗል፤ አፈጻጸሙም ከ80.4 በመቶ ነው፣
• የኮርቻ ቅርፅ ግድቡ ግንባታ አፈጻጸም 96 በመቶ ተጠናቋል፣
• ለቅድመ ማመንጨት ሥራው የሚያስፈልጉ ተርባይኖች የሚገጠሙበት የስፓይራል ኬዝ ተከላ እና የብየዳ ስራ በጥራት በመከናወን ላይ ነው፣
• በግድቡ የግራ ክፍል ግድቡን ከባህር ጠለል በላይ 560 ሜትር ከፍታ ላይ ለማድረስ 26 ሺህ ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት ተሞልቷል፣ በቀሪው የግድቡ ክፍል ላይ ደግሞ 50 ሺህ ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት የመሙላት ሥራ እየተከናወነ ነው፤
• ለታችኛው የውሃ ማስተንፈሻ (ቦተም አውትሌት) ሥራ የሚያስፈልገውን ማቴሪያል ከውጭ ሃገር በማስገባት በሳይት ላይ የምርት ሥራ ተጀምሯል፣
• በአሁኑ ሰዓት የጎርፍ ማስተንፈሻ 96 በመቶ፣ የኃይል ማመንጫ ክፍል 70 በመቶ እንዲሁም የዋናው ግድብ የኮንክሪት ሙሌት 80 በመቶ ተጠናቋል፣
• ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ሥራው በ2003 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን ዓመታዊ አማካይ የኃይል ምርት አቅሙም 15,670 ጊጋ ዋት ሰዓት ነው፣
• ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም አሁን ላይ 68 ነጥብ 3 በመቶ ደረሷል።
ምንጭ፦ ኢፕድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ #ተጽዕኖ ለማሳረፍ የሚደረጉ መሯሯጦች ተቀባይነት የላቸውም"- ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት የመሬት የባለቤትነት የይዞታ ማረጋገጫ ሰነዶችን አስረከቡ። ምክትል ከንቲባው ሰነዶቹን ያስረከቡት በፓትርያርክ ፅህፈት ቤት በመገኘት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ነው። ጥያቄ ከቀረበባቸው 137 አብያተ ክርስቲያናት መካከል 15ቱ ዛሬ የባለቤትነት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተሰጥቷቸዋል።
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኬንያና ሶማሊያ ግንኙነታቸውን ወደ ወደ ሰላማዊ ሁኔታው ለመመለስ ተስማሙ፡፡ ኬንያና ሶማልያ በህንድ ውቅያኖስ ጠረፍ ስፍራ ይገባኛል ውጥረት ውስጥ ገብተው ለወራት ዘልቀዋል፤ ጉዳዩንም ዘ ሄግ ለሚገኘው ዓለማቀፍ ፍርድ ቤት አቅርበዋል፡፡ አሁን ላይ ግን ግንኙነታቸውን ለማሻሻል #መግባባት ላይ መድረሳቸው ተሰምቷል፡፡ በግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ አሸማጋይነት በተደረገ ምክክር የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል፡፡
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EGYPT vs #ETHIOPIA | ግብጽ በይፋ ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ጀምራለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ #ሳሜሕ_ሽኩሪ በካይሮ የአረብ ሊግ ስብሰባ ላይ በድርድሮቹ ኢትዮጵያ «ግትር» ሆናለች ሲሉ መውቀሳቸውን አል ሞኒተር የተባለው የግብጽ ጋዜጣ ዘግቧል። የግብጽ ውጭ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ሐምዲ ሎዛ በበኩላቸው መቀመጫቸውን በካይሮ ካደረጉ የአውሮፓ አገራት አምባሳደሮች ጋር በጉዳዩ ላይ ባደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ የሌሎች አገሮችን ጥቅም ችላ በማለት የራሷን አተያይ ብቻ ለመጫን ጥረት እያደረገች ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የከምባታ ጠምባሮ ዞን ምክር ቤት 17ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከመስከረም 21- 23 ቀን 2012 ዓ/ም ያደርጋል። #ዱራሜ
Via Z/TIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via Z/TIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
☺️ባለፉት 10 ቀናት 12,480 አዳዲስ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ተቀላቅለውናል! TIKVAH/HOPE/ተስፋ
🤔የቤተሰቡ ቁጥር በየደቂቃው ተለዋዋጭ ስለሆነ Edit ይደረግ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
🤔የቤተሰቡ ቁጥር በየደቂቃው ተለዋዋጭ ስለሆነ Edit ይደረግ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Alert
የሚመለከታችሁ የፀጥታ አካላት በአርሲ ሮቤ ከተማ ስለተፈጠረው ጉዳይ አስቸኳይ የሆነ መፍትሄ እንድትፈልጉ እንዲሁም ለተፈጠረው ችግር ትኩረት እንድትሰጡ በከተማዋ የሚኖሩ የTIKVAH-ETHIOPIA ቤተሰብ አባላት ተደጋጋሚ ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ። ችግሮች አሁን ካሉባት እንዳይሰፉም የሚመለከተው አካል ሁሉ በሰከነ መንፈስ እንዲወያይም ጥሪ አቅርበዋል።
ስለጉዳዩ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎች ይኖሩናል!
Via Frew/ TIKVAH-ETH/
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
የሚመለከታችሁ የፀጥታ አካላት በአርሲ ሮቤ ከተማ ስለተፈጠረው ጉዳይ አስቸኳይ የሆነ መፍትሄ እንድትፈልጉ እንዲሁም ለተፈጠረው ችግር ትኩረት እንድትሰጡ በከተማዋ የሚኖሩ የTIKVAH-ETHIOPIA ቤተሰብ አባላት ተደጋጋሚ ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ። ችግሮች አሁን ካሉባት እንዳይሰፉም የሚመለከተው አካል ሁሉ በሰከነ መንፈስ እንዲወያይም ጥሪ አቅርበዋል።
ስለጉዳዩ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎች ይኖሩናል!
Via Frew/ TIKVAH-ETH/
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ #የመምህራን ፍልሰት #አሳሳቢ ሆኗል፤ ባለፉት 2 ወራት ብቻ እስከ 10 የሚደርሱ ሲኒየር መምህራን ዩኒቨርሲቲውን ለቀዋል ሲሉ አንድ ስማቸውን እንዲገለፅ ያልፈለጉ የTIKVAH-ETHIOPIA ቤተሰብ አባል ተናግረዋል። ለመምህራኑ ዩኒቨርሲቲውን መልቀቅ እንደ ምክንያትነት የሚነሳውም የአካባቢው ፀጥታ ሁኔታ/TEPI/፣ የመምህራን አያያዝ እና የአስተዳደር ችግር ነው። ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ከሌሎች ተመሳሳይ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲነፃፀር ወደኃላ ቀርቷል ጉዳዩ ትኩረት ይፈልጋል ሲሉ መልዕክቱን ያደረሱት የቤተሰባችን አባል ገልፀዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዘንድሮው የትምህርት መርሃ ግብር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የነበሩ ውስጣዊ ችግሮች በአብዛኛው የተፈቱ በመሆናቸውና ውጫዊ ተብለው ሊያጋጥሙ ይችላሉ የተባሉትም ቢሆኑ በመንግስት በኩል ከፍተኛ ዝግጅት በመደረጉ ወላጆች ስጋት አይግባችሁ ሰላም ላይ ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ሲሉ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍል ጥሪ አቅርበዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዘንድሮ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር መንግስት በቂ ዝግጅት አድርጓል!
"የወላጆች ስጋት ይገባኛል፤ በግልም በዙሪያችንም ብዙ ወላጆች ስላሉ ብዙ ቤተሰብም ስለምናውቅ ትክክልም ነው። በባለፉት ዓመታት ካጋጠሙን አንፃር ስጋታቸው ተገቢ ነው። ግን በዚህኛው ዓመት የተደረገው ዝግጅት ከባለፉት ዓመታት እጅግ በጣም ጥልቅም ነው ጠንካራም ነው። በዚህ ረገድ ፀጥታን በተመለከተ መንግስት በቂ ዝግጅት አድርጓል። ከፌደራል መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እስካሉበት ከተሞችና ዞኖች ድረስ ያለው የመንግስት መዋቅር በቂ ዝግጅት አድርጓል። ክልሎች የራሳቸው በክልላቸው ያለ ዩኒቨርሲቲ ሁሉም ሰላም እንዲሆን በቂ ዝግጅት አድርገዋል። ሁሉም በዚህ ደረጃ ከተንቀሳቀሰ ዩኒቨርሲቲዎች የውስጥ ተጋላጭነታቸውን ከቀነሱ ዓመቱ ሰላማዊ ይሆናል ብለን እንወስዳለን። ወላጆችም በዚህ ጉዳይ ላይ በመንግስት በመተማመን ልጆቻቸውን መክረው ከማንኛውም አደጋ ራሳቸውን ጠብቀው እንዲማሩ በማንኛውም ሁከት ውስጥ እንዳይሳተፉ፤ ሰላምን የነሱንም ህይወት አደጋ ላይ የሚጥል ነገር ላይ ሳይሳተፉ፡ ትምህርታቸውን አተኩረው እንዲማሩ መክረው ከላኩ ዓመቱ ሰላማዊ ሆኖ ይጠናቀቃል።" ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ - /ከኤፍ ቢ ሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ/
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የወላጆች ስጋት ይገባኛል፤ በግልም በዙሪያችንም ብዙ ወላጆች ስላሉ ብዙ ቤተሰብም ስለምናውቅ ትክክልም ነው። በባለፉት ዓመታት ካጋጠሙን አንፃር ስጋታቸው ተገቢ ነው። ግን በዚህኛው ዓመት የተደረገው ዝግጅት ከባለፉት ዓመታት እጅግ በጣም ጥልቅም ነው ጠንካራም ነው። በዚህ ረገድ ፀጥታን በተመለከተ መንግስት በቂ ዝግጅት አድርጓል። ከፌደራል መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እስካሉበት ከተሞችና ዞኖች ድረስ ያለው የመንግስት መዋቅር በቂ ዝግጅት አድርጓል። ክልሎች የራሳቸው በክልላቸው ያለ ዩኒቨርሲቲ ሁሉም ሰላም እንዲሆን በቂ ዝግጅት አድርገዋል። ሁሉም በዚህ ደረጃ ከተንቀሳቀሰ ዩኒቨርሲቲዎች የውስጥ ተጋላጭነታቸውን ከቀነሱ ዓመቱ ሰላማዊ ይሆናል ብለን እንወስዳለን። ወላጆችም በዚህ ጉዳይ ላይ በመንግስት በመተማመን ልጆቻቸውን መክረው ከማንኛውም አደጋ ራሳቸውን ጠብቀው እንዲማሩ በማንኛውም ሁከት ውስጥ እንዳይሳተፉ፤ ሰላምን የነሱንም ህይወት አደጋ ላይ የሚጥል ነገር ላይ ሳይሳተፉ፡ ትምህርታቸውን አተኩረው እንዲማሩ መክረው ከላኩ ዓመቱ ሰላማዊ ሆኖ ይጠናቀቃል።" ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ - /ከኤፍ ቢ ሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ/
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሎስ አንጀለስ የኦሮሞ ማኅበረስብ ማዕከል አዘጋጅነት ለ6ኛ ጊዜ የእሬቻ በዓልን ባሳለፍነው ቅዳሜ በሎስ አንጀለስ ከተማ የማኅበረስቡ ተወላጆች በተገኙበት አክብረዋል፡፡
Photo: VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Photo: VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኔቶ የአፍሪካ ቀንድ ሰላምን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ እንደሚሰራ አስታወቀ። የኢፌዲሪ ሰላም ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዲኤታ ወ/ሮ አልማዝ መኮንን የሰሜን አትላንቲክ የቃል ኪዳን ሀገሮች ድርጅት (ኔቶ) ንዑስ-ኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑትን ሚሮ ኮቫችን እና ከልዩ ልዩ ሀገራት የተውጣጡ የድርጅቱን የፓርላማ አባላት በሚኒስትር ጽህፈት ቤት ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ዞን የክልልነት ጥያቄን በማስመልከት ለማካሄድ ላቀደው ህዝበ ውሳኔ የምርጫ ምልክቶችን ይፋ አደረገ። ቦርዱ በመጪው ህዳር 3 ቀን 2012 ዓ.ም የሲዳማ ዞን የክልልነት ጥያቄን በማስመልከት ለማካሄድ ላቀደው ህዝበ ውሳኔ አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እያከናወነ ይገኛል።
Via #ETHIO_FM
@tsrgabwolde @tikvahethiopia
Via #ETHIO_FM
@tsrgabwolde @tikvahethiopia
1. “ሲዳማ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ውስጥ እንዲቆይ እፈልጋለሁ” ለሚለው አማራጭ የጎጆ ቤት ምልክት፣
2. “ሲዳማ ራሱን ችሎ በክልልነት እንዲደራጅ እፈልጋለሁ” ለሚለው አማራጭ የሻፌታ ምልክት ሆኖ ለህዝበ ውሳኔው ድምጽ መስጫነት እንዲያገለግል የተወሰነ መሆኑን ቦርዱ አስታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
2. “ሲዳማ ራሱን ችሎ በክልልነት እንዲደራጅ እፈልጋለሁ” ለሚለው አማራጭ የሻፌታ ምልክት ሆኖ ለህዝበ ውሳኔው ድምጽ መስጫነት እንዲያገለግል የተወሰነ መሆኑን ቦርዱ አስታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia