#update ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎች እንዲማሩበት ታስቦ በግንባታ ላይ የሚገኘው የኢኖቬሽን ማዕከል ከ50 በመቶ በላይ መጠናቀቁን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ዋና ኦዲተር ለመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ መምህራን በነጻ የታደሉ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየመረመረ መሆኑን ካፒታል አስነብቧል፡፡ ለመምህራኑ የተሰጡት በቦሌ ቡልቡላ የሚገኙ 30 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ናቸው፡፡ መምህኑ በወር 5 ሺህ ብር የቤት አበል እያላቸው ነው በ500 ብር ኪራይ እንዲኖሩባቸው የታደላቸው፡፡ አካዳሚው በጠቅላይ ሚንስትር ጽፈት ቤት ስር ያለ የፌደራል ተቋም ነው፡፡ የአካዳሚክ ፕሬዝዳንቱ ጸሃፊ ዳዊት ለገሠ ግን ብቃት ያላቸውን አስተማሪዎች በተቋማችን ለማቆየት ስንል የሰጠናቸው ጥቅማጥቅም ነው ብለዋል፡፡
Via ካፒታል(በዋዜማ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via ካፒታል(በዋዜማ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መልዕክት ለአዲስ አበባ ልጆች፦
(ከዶክተር ኤልያስ ገብሩ)
...ኢትዮጵያን እወዳታለሁኝ። አዲስ አበባም ያደግኩባት አድባሬ ነች። እናም ኢትዮጵያንም አዲስ አበባንም ስለምወዳቸው የውስጤን የስሜት ግፊያ(Urge) ትቼ እውነትን እናገራለሁኝ። >>>ጀዋርም እስክንድርም ቁጥራቸው ይለያይ እንጂ የሚሊዮኖች ድጋፍ ያላቸው። በእነርሱ የማይደራደር ተከታዮች ያላቸው አክቲቪስቶች ናቸው።
እናም የዚህን ወቅታዊ ትኩሳት መዳረሻ የሚሆኑትን ሁለት መራር እውነታዎች ተቀበል...
1ኛ>> አንዱን ደግፈህ አንዱን ስለጠላህ የኢትዮጵያን ሰላምና አንድነት የምታስጠብቅ ከመሰለህ ተሳስተሃል።
2ኛ>> በዚህ አላስፈላጊ ፍትጊያ አንዱ ወገን አሸናፊ ይሆናል ብለህ የምታስብ ካለህ ተሳስተሃል። አንዱ ወገን አሸናፊ ቢሆን እንኳን ኢትዮጵያን እንደ ሐገር ሊያስቀጥል የማይችል የእርስ በርስ ደም መፋሰስ አይቀሬ ነው።
***ስለዚህ ወገኔ ሆይ ኢትዮጵያን እወዳታለሁኝ የምትል፣ ከሆነ ጎራ ለይተህ መገፋፋቱን ተውና ቆም ብለህ አስብ። እውነት ነው የምልህ አርቀህ ተመልከት። አዲስ አበባንም እወዳታለሁኝ የምትል የሸገር ልጅ ንቃ። እንደ ሰበታ፣ ሱሉልታ፣ ቡራዩ፣ ለገጣፎ፣ ወለቴ፣ ካራቆሬ... ያሉ ቦታዎች ላይ ሊከሰት የሚችለውን ነገር አሻግሮ ማየት ያስፈልጋል። መቻቻል...የኦሮሞ ወንድምህን አክብረህ መወያየትና አብረህ መኖር እንጂ እልህና የቃላት ልውውጥ ለማንም አይጠቅምም። ዋናው ነገር ፍቅሩ ነው የሚሉ የአራዳ ልጆች አሁን ብዙ ስራ ይጠበቅባችኋል።
#ወደ_ልቦናችን_እንመለስ
#ኢትዮጵያ_የሁላችንም_መሰብሰቢያ_ዋርካ_ናት።
(ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አዕምሮ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
(ከዶክተር ኤልያስ ገብሩ)
...ኢትዮጵያን እወዳታለሁኝ። አዲስ አበባም ያደግኩባት አድባሬ ነች። እናም ኢትዮጵያንም አዲስ አበባንም ስለምወዳቸው የውስጤን የስሜት ግፊያ(Urge) ትቼ እውነትን እናገራለሁኝ። >>>ጀዋርም እስክንድርም ቁጥራቸው ይለያይ እንጂ የሚሊዮኖች ድጋፍ ያላቸው። በእነርሱ የማይደራደር ተከታዮች ያላቸው አክቲቪስቶች ናቸው።
እናም የዚህን ወቅታዊ ትኩሳት መዳረሻ የሚሆኑትን ሁለት መራር እውነታዎች ተቀበል...
1ኛ>> አንዱን ደግፈህ አንዱን ስለጠላህ የኢትዮጵያን ሰላምና አንድነት የምታስጠብቅ ከመሰለህ ተሳስተሃል።
2ኛ>> በዚህ አላስፈላጊ ፍትጊያ አንዱ ወገን አሸናፊ ይሆናል ብለህ የምታስብ ካለህ ተሳስተሃል። አንዱ ወገን አሸናፊ ቢሆን እንኳን ኢትዮጵያን እንደ ሐገር ሊያስቀጥል የማይችል የእርስ በርስ ደም መፋሰስ አይቀሬ ነው።
***ስለዚህ ወገኔ ሆይ ኢትዮጵያን እወዳታለሁኝ የምትል፣ ከሆነ ጎራ ለይተህ መገፋፋቱን ተውና ቆም ብለህ አስብ። እውነት ነው የምልህ አርቀህ ተመልከት። አዲስ አበባንም እወዳታለሁኝ የምትል የሸገር ልጅ ንቃ። እንደ ሰበታ፣ ሱሉልታ፣ ቡራዩ፣ ለገጣፎ፣ ወለቴ፣ ካራቆሬ... ያሉ ቦታዎች ላይ ሊከሰት የሚችለውን ነገር አሻግሮ ማየት ያስፈልጋል። መቻቻል...የኦሮሞ ወንድምህን አክብረህ መወያየትና አብረህ መኖር እንጂ እልህና የቃላት ልውውጥ ለማንም አይጠቅምም። ዋናው ነገር ፍቅሩ ነው የሚሉ የአራዳ ልጆች አሁን ብዙ ስራ ይጠበቅባችኋል።
#ወደ_ልቦናችን_እንመለስ
#ኢትዮጵያ_የሁላችንም_መሰብሰቢያ_ዋርካ_ናት።
(ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አዕምሮ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ትግራይ ክልል ሀገር ዐቀፉ ሕዝብና ቤቶች ቆጠራ መራዘሙን ተቃውሟል፡፡ ለቆጠራው ዝግጅቶች ተደርገው ሳለ በአስቸኳይ ስብሰባ መራዘሙ ሕገ መንግሥቱን ይሸረሽራል፤ ሀገሪቱንም ለኪሳራ ይዳርጋል ብለዋል የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር አብርሃም ተከስተ ለኢቢሲ፡፡ ውሳኔው የመንግሥትን የአመራር ግልጽነት አለመኖሩን ያሳያል፤ ሀገሪቱ በዐለም ላይ ያላትን አመኔታ ያሳጣል፡፡
Via #ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአማራ ክልል መንግስት ለ4 ሺህ 280 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታውቋል። እነዚህ የህግ ታራሚዎች #ከነገ ጀምሮ በይቅርታ እደሚለቀቁ የተገለፀ ሲሆን ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች ውስጥ 67 ሴቶች ናቸው ተብሏል፡፡
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በየካ ክፍለ ከተማ #በቅርስነት የተመዘገበውን የደጃዝማች አምኃ አበራ መኖሪያ ቤት በከፊል #እንዳፈረሰው ሸገር ዘግቧል፡፡ የከተማዋ ባሕል፣ ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ግን ቅርሱን እንዳያፈርስ ኮርፔሬሽኑ ጋር ደብዳቤ ተለዋውጠን ተስማምተን ነበር ብሏል፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ የቢሮው ሃላፊ ታርጋ የሌለው እስካቫተር ነው ያፈረሰው፤ አፍራሾቹን ከድርጊታቸው አስቁመን በፖሊስ አስይዘናቸዋል ብለዋል፡፡ ካሁን በፊትም ኮርፖሬሽኑ የቅርሱን እልፍኞች አፍርሶ ጉዳዩ ክስ ላይ ነበር፡፡ ቅርሱ የ90 ዐመታት ዕድሜ አለው፡፡ ደጃዝማች አምኃ የእውቁ አርበኛ ልዑል ራስ ካሳ ኃይሉ የልጅ ልጅ ናቸው፡፡ አባታቸው አበራ ካሳ ከወንድማቸው ወንድወሰን ካሳ ጋር ከፋሽስት ጣሊያን ጋር ሲዋጉ ተይዘው በስቅላት የተገደሉ አርበኛ ናቸው።
Via ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፈረሰውን በቅርስነት የተመዘገበ መኖሪያ ቤት ጉዳይ በህግ አግባብ ለመፍታት ጥረት ይደረጋል-የአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም
.
.
በአዲስ አበባ ትላንት የፈረሰው የደጃዝማች ዐምዴ አበራ ካሳ መኖሪያ ቤት ጉዳይ በህግ አግባብ ለመፍታት እንሚንቀሳቀስ የአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ የሚገኘውና በቅርስነት የተመዘገበው መኖሪያ ቤቱ በትላንትናው ዕለት መፍረሱ ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጉዳዩን በተመለከተ በዛሬው ዕለት ወደ ስፍራው በመሄድ #እንደረጋገጠው ከሆነ ከ90 ዓመታት በላይ ያስቆጠረዉ መኖሪያ ቤቱ የፈረሰው በፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አማካኝነት ነው፡፡
በአዲስ አበበ ከተማ በቅርስነት ከተያዙ ታሪካዊ ግንባታዎች አንዱ እንደሆነ የሚነገርለት የደጃዝማች ዐምዴ አበራ ቤት ለምን እንዳፈረሰ የተጠየቀው የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በበኩሉ ቤቱ በቅርስነት ስለመመዝገቡ ምንም ዓይነት መረጃ እንደሌለው በተለይ ለኢቲቪ ገልጿል፡፡
ኢቲቪ የፈረሰው ታሪካዊ መኖሪያ ቤት በከተማዋ በቅርስነት ከተመዘገቡ ከ400 በላይ ቅርሶች መካከል አንዱ መሆኑን ከአዲስ አበበ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በዛሬው ዕለት ማረጋገጥ ችሏል፡፡
በቅርስነት ተመዝግቧል የተባለዉን መኖሪያ ቤት ጉዳይ ወደ ፊት በህግ አግባብ ለመፍታት እንሚንቀሳቀስ ነው የአዲስ አበበ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የገለፀው፡፡
Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
በአዲስ አበባ ትላንት የፈረሰው የደጃዝማች ዐምዴ አበራ ካሳ መኖሪያ ቤት ጉዳይ በህግ አግባብ ለመፍታት እንሚንቀሳቀስ የአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ የሚገኘውና በቅርስነት የተመዘገበው መኖሪያ ቤቱ በትላንትናው ዕለት መፍረሱ ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጉዳዩን በተመለከተ በዛሬው ዕለት ወደ ስፍራው በመሄድ #እንደረጋገጠው ከሆነ ከ90 ዓመታት በላይ ያስቆጠረዉ መኖሪያ ቤቱ የፈረሰው በፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አማካኝነት ነው፡፡
በአዲስ አበበ ከተማ በቅርስነት ከተያዙ ታሪካዊ ግንባታዎች አንዱ እንደሆነ የሚነገርለት የደጃዝማች ዐምዴ አበራ ቤት ለምን እንዳፈረሰ የተጠየቀው የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በበኩሉ ቤቱ በቅርስነት ስለመመዝገቡ ምንም ዓይነት መረጃ እንደሌለው በተለይ ለኢቲቪ ገልጿል፡፡
ኢቲቪ የፈረሰው ታሪካዊ መኖሪያ ቤት በከተማዋ በቅርስነት ከተመዘገቡ ከ400 በላይ ቅርሶች መካከል አንዱ መሆኑን ከአዲስ አበበ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በዛሬው ዕለት ማረጋገጥ ችሏል፡፡
በቅርስነት ተመዝግቧል የተባለዉን መኖሪያ ቤት ጉዳይ ወደ ፊት በህግ አግባብ ለመፍታት እንሚንቀሳቀስ ነው የአዲስ አበበ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የገለፀው፡፡
Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በባህርዳር ከተማ የሚገኘውን የአባይ ድልድይ ለማስገንባት በዛሬው ዕለት ስምምነት ተፈርሟል። ለበርካታ አመታት በባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ጥያቄ ሲነሳበት የቆየው ይህ ድልድይ በ 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ነው የሚገነባው፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: #ለጌዴኦ_ወገኖቻችን የህክምናና የተለያዩ ድጋፎች ለመስጠት ተፈናቃዮች ወዳለባቸው አካባቢዎች የተጓዙ የይ/ዓለም ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ #ዶክተሮች_ልዑካን!
@tsegabwolde
@tsegabwolde
“አማራ፣ ኦሮሞ... እንዲህ በሚል የሚደራጁ ፓርቲዎች የርዕዮተ ዓለም ስብሰብ ሳይሆኑ ብሶት፤ ቂም በቀልና ምሬት የወለዳቸው ፓርቲዎች ናቸው።” ፕሮፌሰር #በየነ_ጴጥሮስ
.
.
- “የኢትዮጵያ ፖለቲካ መቼም ተቃንቶ አያውቅም። ምክንያቱም መተማመን የለም። አንዱ ሌላኛውን በበላይነት መግዛት ነው የሚፈልገው”
- “አሁንም የጎበዝ አለቆች በአገሪቱ ዴሞክራሲ እናመጣለን ብለው ከዲሞክራሲ ጋር የማይገናኝ ፍጹማዊ አምባገነን አስተዳደር ጫኑብን።”
- “በኢትዮጵያ ያለው ፖለቲከኛ፤ ጠባብና የተደበቀ አጀንዳ ያለው ነው”
- “ዶ/ር ዐቢይ ከዚህ በፊት ታፍኖ የነበረው ህዝብ ትንሽ ይተንፍስ ነው የሚሉት፤ መተንፈሱ ግን ወደ ጋጠ-ወጥነት ተሻገረ።”
- “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይዘው የመጡት ጉዳይ፤ ትንታኔ ለየት ያለ አቀራረብ ነው። ህብረተሰቡ ተስፋ እንዲያድርበት አድርጓል።”
- “ኢህአዴግ ቀደም ብሎ ቢዋሀድ ኖሮ ህውሓት አኩርፎ ጠርዝ ላይ አይሆንም ነበር።”
- “ኢህአዴጎች ፍቱን መድሃኒት ብለው ያዘዙት መርዝ አሁን ላይ ለመሰብሰብ አስቸጋሪ ሆኗል።”
- “በአዲስ የፖለቲካ ፍላጎት አዲስ አበባ ፊንፊኔ ነው፤ በረራ ነው እያሉ ወዲያና ወዲህ የሚላገው ነገር ቅንነት የሌለው ክርክር ነው።”
Via አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
- “የኢትዮጵያ ፖለቲካ መቼም ተቃንቶ አያውቅም። ምክንያቱም መተማመን የለም። አንዱ ሌላኛውን በበላይነት መግዛት ነው የሚፈልገው”
- “አሁንም የጎበዝ አለቆች በአገሪቱ ዴሞክራሲ እናመጣለን ብለው ከዲሞክራሲ ጋር የማይገናኝ ፍጹማዊ አምባገነን አስተዳደር ጫኑብን።”
- “በኢትዮጵያ ያለው ፖለቲከኛ፤ ጠባብና የተደበቀ አጀንዳ ያለው ነው”
- “ዶ/ር ዐቢይ ከዚህ በፊት ታፍኖ የነበረው ህዝብ ትንሽ ይተንፍስ ነው የሚሉት፤ መተንፈሱ ግን ወደ ጋጠ-ወጥነት ተሻገረ።”
- “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይዘው የመጡት ጉዳይ፤ ትንታኔ ለየት ያለ አቀራረብ ነው። ህብረተሰቡ ተስፋ እንዲያድርበት አድርጓል።”
- “ኢህአዴግ ቀደም ብሎ ቢዋሀድ ኖሮ ህውሓት አኩርፎ ጠርዝ ላይ አይሆንም ነበር።”
- “ኢህአዴጎች ፍቱን መድሃኒት ብለው ያዘዙት መርዝ አሁን ላይ ለመሰብሰብ አስቸጋሪ ሆኗል።”
- “በአዲስ የፖለቲካ ፍላጎት አዲስ አበባ ፊንፊኔ ነው፤ በረራ ነው እያሉ ወዲያና ወዲህ የሚላገው ነገር ቅንነት የሌለው ክርክር ነው።”
Via አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia