TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Mali 🇲🇱

በአፍሪካዊቷ #ማሊ የታጠቁ አማፂያን በፈጸሙት ጥቃት ከ100 በላይ ንፁሀን ዜጎች መገደላቸውን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል።

ጥቃቱ ማዕከላዊ ማሊ ውስጥ መፈፀሙ ነው የተነገረው።

ጥቃቱን ' Katiba Macina ' የተባለው የታጠቀ ቡድን አባላት ቅዳሜ ለሊት ለእሁድ አጥቢያ የፈፀሙ ሲሆን ፤ ሞፕቲ ክልል ውስጥ በሚገኘው ባንካስ የገጠር ማህበረሰብ ውስጥ ቢያንስ በሶስት መንደሮች ላይ ባደረሱት ጥቃት በትንሹ 132 ንፁሃን ሰዎች በግፍ መደገላቸውን የሀገሪቱ መንግስት ገልጿል።

ጥቃቱን ተከትሎ የማሊ መንግስት ዛሬ የሶስት ቀን ብሄራዊ ሀዘን አውጇል።

@tikvahethiopia