አቶ ኢሳያስ በዋስ እንዲወጡ ተወሰነ‼️
ፍርድ ቤቱ መርማሪ ፖሊስ አቶ #ኢሳያስ_ዳኘው በዋስ ሊለቀቁ አይገባም በሚል ያቀረበውን ይግባኝ ውድቅ አደረገ። በከባድ የሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት አቶ ኢሳያስ ዳኘው በተጠረጠሩበት ወንጀል በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 10ኛ የወንጀል ችሎት ቀርበው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ #ተፈቅዶላቸዋል።
መርማሪ ፖሊስም ግለሰቡ በዋስ መውጣት የለባቸውም በሚል ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ያቀረበው ይግባኝ ውድቅ ተደርጎበታል።
በመሆኑም ከዚህ ቀደም በተወሰነው መሰረት በ50 ሺህ ከሃገር እንዳይወጡ በተጣለ እገዳ #በዋስ እንዲለቀቁ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔውን አፅንቷል።
አቶ ኢሳያስ ዳኘው በኢትዮ ቴሌኮም የኤን ጂ ፒ ኦ ዳይሬክተር ሆነው በሚሰሩበት ወቅት ለሜቴክ የተሰጠን ውል በማሻሻልና ክፍያ እንዲፈጸም በማድረግ በመንግስት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል በሚል በከባድ የሙስና ወንጀል ነበር የተጠረጠሩት።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፍርድ ቤቱ መርማሪ ፖሊስ አቶ #ኢሳያስ_ዳኘው በዋስ ሊለቀቁ አይገባም በሚል ያቀረበውን ይግባኝ ውድቅ አደረገ። በከባድ የሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት አቶ ኢሳያስ ዳኘው በተጠረጠሩበት ወንጀል በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 10ኛ የወንጀል ችሎት ቀርበው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ #ተፈቅዶላቸዋል።
መርማሪ ፖሊስም ግለሰቡ በዋስ መውጣት የለባቸውም በሚል ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ያቀረበው ይግባኝ ውድቅ ተደርጎበታል።
በመሆኑም ከዚህ ቀደም በተወሰነው መሰረት በ50 ሺህ ከሃገር እንዳይወጡ በተጣለ እገዳ #በዋስ እንዲለቀቁ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔውን አፅንቷል።
አቶ ኢሳያስ ዳኘው በኢትዮ ቴሌኮም የኤን ጂ ፒ ኦ ዳይሬክተር ሆነው በሚሰሩበት ወቅት ለሜቴክ የተሰጠን ውል በማሻሻልና ክፍያ እንዲፈጸም በማድረግ በመንግስት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል በሚል በከባድ የሙስና ወንጀል ነበር የተጠረጠሩት።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ-የሲዳማ ሪፈረንደም ሰልፍ‼️
#የሲዳማ_ክልል_ጥያቄ የሕዝቤ ውሳኔ ቀን መዘግየት አስመልክቶ በቀን 14/6/2011 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ የሚካሄደው ሰልፍ በሰላማዊ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት #ማጠናቀቁን የሲዳማ ዞንና የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎች በጋራ በሰጡት መግለጫቸው አስታውቀዋል።
የሰልፉ ዓላማ የሲዳማ ሕዝብ በክልልነት የመደራጀት መብት አስፈላጊውን ሕጋዊ ቅድመ ሁኔታዎችን በማጠናቀቅ በቀን 12/3/2011 ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቢቀርብም እስከ አሁን ድረስ ሕዝቤ ውሳኔ የሚካሄድበት ቀን ተወስኖ ምላሽ ባለመሰጠቱና በመዘግየቱ የሚካሄድ ሰልፍ መሆኑን ለማወቅም ተችሏል።
"ሕገ መንግስታዊ መብታችን ይከበር" በሚል መሪ ቃልና ሌሎች መፈክሮችን በመያዝ በዕለቱ ከጧቱ 1:00-6:00 ሰዓት ድረስ መነሻውን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ያደረገ በሲዳማ ዞን አስተዳደር- በአሮጌው መናኸሪያ -በተስፋዬ ግዛው ሕንጻ-በመሳይ ሆቴል አቋርጦ በሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲዬም ማሳረጊያ የሚደረግ ይሆናል።
በሰልፉ ላይ ከሲዳማ ዞን ሁሉም ወረዳዎች የተወጣጡ ሰልፈኞች የሚሳተፉ መሆኑን በመግለጽ ሰልፉም በሰላማዊ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ፖሊስ ከተለያዩ ፀጥታ አካላትና ከሰልፉ አስተባባሪዎች ጋር በመሆን አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን በመግለጫው አክሏል።
ኀብረተሰቡም ይህን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ የራሱንና የአካባቢውን ሰላምና ፀጥታ በመጠበቅና በማስጠበቅ ረገድ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣና ማንኛውንም ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲያጋጥም ለፀጥታ አካላት ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበርም ጥሪ ቀርቧል።
ከዚህም በተጨማሪ: በሰላማዊ ሰልፉ መነሻ-መድረሻ እንዲሆኑ በተፈቀዱ መንገዶች ላይ ማንኛውም ዓይነት የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ የማይፈቀድ መሆኑንና የሰላማዊ ሰልፍ ትዕይንት እስኪጠናቀቅ ድረስ ለትራፍክ እንቅስቃሴ ዝግ እንደሚሆን ተገልጿል።
ከዚህ ውጭ በቡድንም ሆነ በተናጠል የከተማውን ኀብረተሰብ ሰላማዊ እንቅስቃሴና የሰላማዊ ሰልፉ ሠላማዊ ህደቱን ማወክ የተለያዩ #የጦር_መሳሪያዎችን ይዞ መገኘት፣በሰልፉ ወቅት በሕግ #የተከለከሉ ድርጊቶች መፈፀም በጥብቅ የተከለከሉ ሲሆን ተፈጽሞም ሲገኙ የፀጥታ አካሉ አስፈላጊውን ሕጋዊ #እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን ኃላፊዎቹ በመግለጫቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
በማጠቃለያም ሕዝባዊ ትዕይንቱ በሰላም እንዲጠናቀቅ ኀብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በትብብር እንዲሰራ በድጋሚ ጥሪ በማቅረብ ኃላፊዎቹ መግለጫቸውን አጠቃለዋል።
ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የሲዳማ_ክልል_ጥያቄ የሕዝቤ ውሳኔ ቀን መዘግየት አስመልክቶ በቀን 14/6/2011 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ የሚካሄደው ሰልፍ በሰላማዊ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት #ማጠናቀቁን የሲዳማ ዞንና የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎች በጋራ በሰጡት መግለጫቸው አስታውቀዋል።
የሰልፉ ዓላማ የሲዳማ ሕዝብ በክልልነት የመደራጀት መብት አስፈላጊውን ሕጋዊ ቅድመ ሁኔታዎችን በማጠናቀቅ በቀን 12/3/2011 ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቢቀርብም እስከ አሁን ድረስ ሕዝቤ ውሳኔ የሚካሄድበት ቀን ተወስኖ ምላሽ ባለመሰጠቱና በመዘግየቱ የሚካሄድ ሰልፍ መሆኑን ለማወቅም ተችሏል።
"ሕገ መንግስታዊ መብታችን ይከበር" በሚል መሪ ቃልና ሌሎች መፈክሮችን በመያዝ በዕለቱ ከጧቱ 1:00-6:00 ሰዓት ድረስ መነሻውን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ያደረገ በሲዳማ ዞን አስተዳደር- በአሮጌው መናኸሪያ -በተስፋዬ ግዛው ሕንጻ-በመሳይ ሆቴል አቋርጦ በሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲዬም ማሳረጊያ የሚደረግ ይሆናል።
በሰልፉ ላይ ከሲዳማ ዞን ሁሉም ወረዳዎች የተወጣጡ ሰልፈኞች የሚሳተፉ መሆኑን በመግለጽ ሰልፉም በሰላማዊ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ፖሊስ ከተለያዩ ፀጥታ አካላትና ከሰልፉ አስተባባሪዎች ጋር በመሆን አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን በመግለጫው አክሏል።
ኀብረተሰቡም ይህን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ የራሱንና የአካባቢውን ሰላምና ፀጥታ በመጠበቅና በማስጠበቅ ረገድ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣና ማንኛውንም ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲያጋጥም ለፀጥታ አካላት ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበርም ጥሪ ቀርቧል።
ከዚህም በተጨማሪ: በሰላማዊ ሰልፉ መነሻ-መድረሻ እንዲሆኑ በተፈቀዱ መንገዶች ላይ ማንኛውም ዓይነት የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ የማይፈቀድ መሆኑንና የሰላማዊ ሰልፍ ትዕይንት እስኪጠናቀቅ ድረስ ለትራፍክ እንቅስቃሴ ዝግ እንደሚሆን ተገልጿል።
ከዚህ ውጭ በቡድንም ሆነ በተናጠል የከተማውን ኀብረተሰብ ሰላማዊ እንቅስቃሴና የሰላማዊ ሰልፉ ሠላማዊ ህደቱን ማወክ የተለያዩ #የጦር_መሳሪያዎችን ይዞ መገኘት፣በሰልፉ ወቅት በሕግ #የተከለከሉ ድርጊቶች መፈፀም በጥብቅ የተከለከሉ ሲሆን ተፈጽሞም ሲገኙ የፀጥታ አካሉ አስፈላጊውን ሕጋዊ #እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን ኃላፊዎቹ በመግለጫቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
በማጠቃለያም ሕዝባዊ ትዕይንቱ በሰላም እንዲጠናቀቅ ኀብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በትብብር እንዲሰራ በድጋሚ ጥሪ በማቅረብ ኃላፊዎቹ መግለጫቸውን አጠቃለዋል።
ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ~ጥብቅ ማስጠንቀቂያ‼️
#በቡድንም ሆነ #በተናጠል የሀዋሳ ከተማ ኀብረተሰብን #ሰላማዊ እንቅስቃሴና የሰላማዊ ሰልፉ ሠላማዊ ሂደቱን ማወክ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ይዞ መገኘት፣ በሰልፉ ወቅት በሕግ #የተከለከሉ ድርጊቶች መፈፀም በጥብቅ #የተከለከለ ሲሆን ተፈጽሞም ሲገኝ የፀጥታ አካሉ አስፈላጊውን ሕጋዊ #እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን ገልጿል።
#ሲዳማሪፈረንደም2011 #ሀዋሳ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#በቡድንም ሆነ #በተናጠል የሀዋሳ ከተማ ኀብረተሰብን #ሰላማዊ እንቅስቃሴና የሰላማዊ ሰልፉ ሠላማዊ ሂደቱን ማወክ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ይዞ መገኘት፣ በሰልፉ ወቅት በሕግ #የተከለከሉ ድርጊቶች መፈፀም በጥብቅ #የተከለከለ ሲሆን ተፈጽሞም ሲገኝ የፀጥታ አካሉ አስፈላጊውን ሕጋዊ #እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን ገልጿል።
#ሲዳማሪፈረንደም2011 #ሀዋሳ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Alert ~ ሸዋሮቢት‼️
"ሰላም ፀግሽ እንዴት ነህ #ሽዋሮቢት ላይ ችግር አለ መንገድ ተዘግቷል፤ ወጣቶች አስፓልት ላይ ጎማ እያነደዱ ነው። ምክንያቱ ደግሞ እናትና ህፃን ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገለው መገኘታቸው ነው። ተዟዙሬ እንዳጣራሁት #የብሄርም #የሃይማኖትም ግጭት #የለበትም ገዳዩ ተይዟል ወጣቶቹ ደግሞ #ይሰጠን ይገደል ነው ጥያቄያቸው ነገሩ ወደባሰ ደረጃ ሳይደርስ በቂ የፖሊስ ሃይል መድረስ ይኖርበታል። እየተቀጣጠሉ ያሉት ጎማዎች ብዙ እና ረጅም መንገድ ላይ ነው ዋናው ግን የሃይማኖትም የብሄርም ግጭት አይደለም!!!" ሠአሌው ምህረት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ሰላም ፀግሽ እንዴት ነህ #ሽዋሮቢት ላይ ችግር አለ መንገድ ተዘግቷል፤ ወጣቶች አስፓልት ላይ ጎማ እያነደዱ ነው። ምክንያቱ ደግሞ እናትና ህፃን ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገለው መገኘታቸው ነው። ተዟዙሬ እንዳጣራሁት #የብሄርም #የሃይማኖትም ግጭት #የለበትም ገዳዩ ተይዟል ወጣቶቹ ደግሞ #ይሰጠን ይገደል ነው ጥያቄያቸው ነገሩ ወደባሰ ደረጃ ሳይደርስ በቂ የፖሊስ ሃይል መድረስ ይኖርበታል። እየተቀጣጠሉ ያሉት ጎማዎች ብዙ እና ረጅም መንገድ ላይ ነው ዋናው ግን የሃይማኖትም የብሄርም ግጭት አይደለም!!!" ሠአሌው ምህረት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Mbirr❓
በትላንትናው ዕለት በማዕበራዊ ድረገፅ በተለይም "Think Tank" በተባለው ድረገፅ Mbirrን የተመለከተ መረጃ ተሰራጭቶ በርካቶች ሲቀባበሉት አምሽተዋል። በሀገራችን ውስጥ የሚነገሩ ሀሰተኛ ወሬዎችን ከምንጩ እያጣራ በማቅረብ የሚታወቀው አለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ይህንን መረጃም አጣርቶ የደረሰበትን በፌስቡክ ገፁ ይፋ አድርጓል።
ጋዜጠኛው የMBirr ሀላፊ የሆኑትን እና በኢሜይሉ ላይ የተጠቀሱትን አቶ #እንደሻውን በስልክ አነጋግሮ ያገኘው ምላሽ ይኸ ነው፦
"ይህ fabricated (የፈጠራ) የሆነ መረጃ ነው። አንተም እንዳየኸው ሰዉ ዝም ብሎ ነው ሼር እያረገው ያለው። እንደዚህ አይነት ኢሜይል አልተላከምም፣ አልተላከም።"
በተጨማሪ...
ጋዜጠኛ ኤልያስ የMbirr ኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ሀላፊ የሆነችውን እየሩሳሌም ሀድጉን ስለጉዳዩ ጠይቋት ይህን መልስ ሰጥታለች፦
"Hello Elias, The #fake_news article posted on Ethio Think Tank was categorically untrue, and resulted from the impersonation of one of our employee's email accounts. We have demanded that they retract the article immediately. We request that all news media refrain from publishing this fake news article."
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት (https://www.facebook.com/Elias-Meseret-517243322140049/)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በትላንትናው ዕለት በማዕበራዊ ድረገፅ በተለይም "Think Tank" በተባለው ድረገፅ Mbirrን የተመለከተ መረጃ ተሰራጭቶ በርካቶች ሲቀባበሉት አምሽተዋል። በሀገራችን ውስጥ የሚነገሩ ሀሰተኛ ወሬዎችን ከምንጩ እያጣራ በማቅረብ የሚታወቀው አለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ይህንን መረጃም አጣርቶ የደረሰበትን በፌስቡክ ገፁ ይፋ አድርጓል።
ጋዜጠኛው የMBirr ሀላፊ የሆኑትን እና በኢሜይሉ ላይ የተጠቀሱትን አቶ #እንደሻውን በስልክ አነጋግሮ ያገኘው ምላሽ ይኸ ነው፦
"ይህ fabricated (የፈጠራ) የሆነ መረጃ ነው። አንተም እንዳየኸው ሰዉ ዝም ብሎ ነው ሼር እያረገው ያለው። እንደዚህ አይነት ኢሜይል አልተላከምም፣ አልተላከም።"
በተጨማሪ...
ጋዜጠኛ ኤልያስ የMbirr ኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ሀላፊ የሆነችውን እየሩሳሌም ሀድጉን ስለጉዳዩ ጠይቋት ይህን መልስ ሰጥታለች፦
"Hello Elias, The #fake_news article posted on Ethio Think Tank was categorically untrue, and resulted from the impersonation of one of our employee's email accounts. We have demanded that they retract the article immediately. We request that all news media refrain from publishing this fake news article."
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት (https://www.facebook.com/Elias-Meseret-517243322140049/)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️
አክሱም ሽረ እንደስላሴ መስመር ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡
የትራፊክ አደጋው ከሽረ እንደስላሴ ወደ አክሱምና ከአክሱም ወደ ሽረ እንደስላሴ ሲጓዙ የነበሩ ተሽከርካሪዎች #በመጋጨታቸው ያጋጠመ ነው ተብሏል፡፡
በትራፊክ አደጋው በ15 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ያጋጠመ ሲሆን በአምስት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላይ አካል ጉዳት አጋጥሟል፡፡
የትራፊክ አደጋው ልዩ ስሙ አዲግዳድ በተባለ ቦታ ላይ በትናትናው ዕለት እንዳጋጠመ ነው ተገለፀው፡፡
ምንጭ፡-Dimtsi Weyane
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አክሱም ሽረ እንደስላሴ መስመር ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡
የትራፊክ አደጋው ከሽረ እንደስላሴ ወደ አክሱምና ከአክሱም ወደ ሽረ እንደስላሴ ሲጓዙ የነበሩ ተሽከርካሪዎች #በመጋጨታቸው ያጋጠመ ነው ተብሏል፡፡
በትራፊክ አደጋው በ15 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ያጋጠመ ሲሆን በአምስት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላይ አካል ጉዳት አጋጥሟል፡፡
የትራፊክ አደጋው ልዩ ስሙ አዲግዳድ በተባለ ቦታ ላይ በትናትናው ዕለት እንዳጋጠመ ነው ተገለፀው፡፡
ምንጭ፡-Dimtsi Weyane
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢንጂነር አይሻ መሃመድ‼️
#የመከላከያ_ሰራዊት_ቀን የሰራዊቱን አቅም በማሳየት እና የሰራዊቱ ሞራል በመገንባትም ጭምር ከፍተኛ ሚና እንደተጫወተ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጅነር #አይሻ_መሃመድ አስታወቁ።
ሚንስትሯ በሰጡት የማጠቃለያ መግለጫ 7ተኛው የኢፊዲሪ የመከላከያ ሰራዊት ቀን በስኬት ተጀምሮ በስኬት እንደተጠናቀቀ ተናግረዋል።
ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ አባላት ያሉት ኮሚቴ ተዋቅሮ በአሉን እንዴት እናስኪድ በሚለው ጉዳይ ላይ መግባባት ላይ ተደርሶ ወደ ስራ እንደተገባ ሚንስትሯ አስታውሰዋል።
በተለያዩ ቦታዎች የተደረጉት የፓናል ውይይቶች እና የተለያዩ ዝግጅቶች ህብረተሰቡንና የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የበለጠ እንዲቀራረቡ እንዳደረገም ተገልጿል፡፡
በአሁኑ ሰአት የመከላከያ ሰራዊተ በአንዳንድ የሃገሪቱ ክፍሎች ህገ መንግቱን የማስከበር ስራ በመስራት ላይ እንደሚገኝ እና የሕብረተሰቡን ሰላም ለመጠበቅ የሃገሪቱን ሉአላዊነት ከውስጥም ከውጭም ለማስጠበቅ ከመቼውም ጊዜ በላይ እይተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ነው መከላከያ ሚኒስትሯ የገለፁት።
ምንጭ፦ EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የመከላከያ_ሰራዊት_ቀን የሰራዊቱን አቅም በማሳየት እና የሰራዊቱ ሞራል በመገንባትም ጭምር ከፍተኛ ሚና እንደተጫወተ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጅነር #አይሻ_መሃመድ አስታወቁ።
ሚንስትሯ በሰጡት የማጠቃለያ መግለጫ 7ተኛው የኢፊዲሪ የመከላከያ ሰራዊት ቀን በስኬት ተጀምሮ በስኬት እንደተጠናቀቀ ተናግረዋል።
ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ አባላት ያሉት ኮሚቴ ተዋቅሮ በአሉን እንዴት እናስኪድ በሚለው ጉዳይ ላይ መግባባት ላይ ተደርሶ ወደ ስራ እንደተገባ ሚንስትሯ አስታውሰዋል።
በተለያዩ ቦታዎች የተደረጉት የፓናል ውይይቶች እና የተለያዩ ዝግጅቶች ህብረተሰቡንና የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የበለጠ እንዲቀራረቡ እንዳደረገም ተገልጿል፡፡
በአሁኑ ሰአት የመከላከያ ሰራዊተ በአንዳንድ የሃገሪቱ ክፍሎች ህገ መንግቱን የማስከበር ስራ በመስራት ላይ እንደሚገኝ እና የሕብረተሰቡን ሰላም ለመጠበቅ የሃገሪቱን ሉአላዊነት ከውስጥም ከውጭም ለማስጠበቅ ከመቼውም ጊዜ በላይ እይተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ነው መከላከያ ሚኒስትሯ የገለፁት።
ምንጭ፦ EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አንዳንድ #ተራ የሚመስሉ #ንግግሮች በሰዎች ላይ ከባድ ተፅእኖን ይፈጥራሉና ዘወትር መልካም ንግግር እንናገር።
#የጥላቻ_በር_ይዘጋ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የጥላቻ_በር_ይዘጋ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake Pages Alert‼️
ከላይ በምስሉ ላይ የ'ራይት' ምልክት የተደረገበት(ከ28ሺ በላይ ተከታይ ያለድ ገፅ) ትክክለኛው የጉለሌ ፖስት ገፅ ሲሆን ሌሎቹ ፌክ ገፆች ናቸው።
Via Gulale Post
https://www.facebook.com/Elias-Meseret-517243322140049/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከላይ በምስሉ ላይ የ'ራይት' ምልክት የተደረገበት(ከ28ሺ በላይ ተከታይ ያለድ ገፅ) ትክክለኛው የጉለሌ ፖስት ገፅ ሲሆን ሌሎቹ ፌክ ገፆች ናቸው።
Via Gulale Post
https://www.facebook.com/Elias-Meseret-517243322140049/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በለገጣፎ ለገዳዲ ቤት ማፍረሱ ዛሬም ቀጥሏል‼️
የለገጣፎ -ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር አረንጓዴ ቦታዎችን፥ የወንዝ ዳርቻዎችን፥ ከፈቃድ ውጭ የተያዙ እና ካሳ ተከፍሎባቸው ግንባታ የተካሄደባቸው ናቸው ያላቸውን ቤቶች እያፈረሰ ነው።
ቤት ማፍረሱ በትናንት ማክሰኞ ዕለት የተጀመረ ሲሆን የከተማው ከንቲባ የሆኑት በ10 ሺህዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ፈርሰው የሕዝብ መናፈሻ ይሆናሉ ማለታቸው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
በዛ ያለ ቁጥር ያላቸው ተጨማሪ ቤቶች እንደሚፈርሱ የሚጠበቅ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎች እርምጃው ዱብ ዕዳ ሆኖብናል ይላሉ።
በ1990ዎቹ መጀመሪያ ከአርሶ አደር መሬት ገዝቶ፤ ጎጆ ቀልሶ በስፍራው መኖር ሲጀምር አካባቢው ከሞላ ጎደል በማሣዎች የተከበበ፣ መሠረት ልማት የናፍቀው እንደነበር የሚገልፀው አንዋር አህመድ ቤቶቻቸው በትናንትናው ዕለት ከፈረሱባቸው አባወራዎች አንዱ ነው።
እኛ ስንገባ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ራሱ አልተዋቀረም ነበር የሚለው አንዋር፤ ለቤቱ ካርታ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ ባይሳካም "ውሃና መብራት አስገብተናል፣ የቤት ቁጥር ተሰጥቶናል፣ የመሬት ግብር እንከፍላለን" ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል።
መንደሩን የሚያቋርጡ መንገዶች በሚቀየሱበት ወቅት ኗሪዎች ሁለት፣ ሦስት ጊዜ ቤቶቻቸውን እና አጥሮቻቸውን አፍረሰው መሥራታቸውን የሚያስታውሰው አንዋር፤ የአሁኑ እርምጃ ፈጣን እንዲሁም የነዋሪዎቹን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ እንደሆነ ይናገራል።
"ይህ የመኖሪያ መንደር እንደሆነ ይታወቃል፤ አረንጓዴ መናፈሻ ይሁን የሚለው አዲስ ማስተር ፕላን እዚያው ቢሮ ቁጭ ብለው የወሰኑት ነገር ነው። ምንም ሳያወያዩን ነው ድንገት ውሳኔ ይዘው የመጡት።"
በወርሃ የካቲት መባቻ የ'ውጡ' ትዕዛዝ እንደደረሰው ለቢቢሲ የገለፀው አንዋር፤ አስር አባላት ያሉትን ቤተሰቡን ይዞ የትም ለመሄድ እንዳልቻለ ይገልፃል።
እንደአንዋር ገለፃ ቤቶቻቸውን ያጡ አንዳንድ ነዋሪዎች በእምነት ተቋማት ተጠልለዋል።
"ያለምንም ቅደም ሁኔታ ነው ያፈረርሱብን። ዕቃችን እስክንሸክፍ እንኳ ጊዜ አልሰጡንም" ሲል ጨምሮ ለቢቢሲ ተናግሯል።
በአካባቢው መሬት ገዝታ መኖር ከጀመረች ስምንት ዓመት እንደሞላት ለቢቢሲ የገለፀች ሌላ ነዋሪ፤ የመኖሪያ ቤቷ ባይፈርስም በስጋት መወጠሯ እንዳልቀረ ታስረዳለች።
"ትናንትና ብዙ ሕፃናት ሜዳ ላይ ሲወድቁ አይቻለሁ" የምትለው ነዋሪ ይህም ያለፈቃድ የሚሠሩ ቤቶችን አስመልክቶ "ሰማይ ላይ ነው እንጅ ምድር ላይ ጨረቃ የለም" በሚል ከመንግሥት ተሰጥቷል የምትለውን ተስፋ እና መተማመኛን የናደ እንደሆነባት ትናገራለች።
"ዱብ ዕዳ ነው የሆነብን፤ የት እንሄዳለን?"
በስፍራው አስራ ዘጠኝ ዓመት መኖሩን ለቢቢሲ የነገረ ሌላ ነዋሪ በበኩሉ የከተማው አስተዳደር ለገበሬው ካሳ የተከፈለበት ቦታ ላይ የተሠሩ ቤቶችን ነው የማፈርሰው ማለቱን እውነት አይደለም ይላል።
"ይሄ ቤት የተሰራው በ1992 ነው። ማዘጋጃው የተሰራው ከዓመታት በኋላ ነው። የት ሆነው ነው የከፈሉት? ለገበሬው ካሳ የከፈልንበት መሬት ላይ ነው የሰፈራችሁት ነው የሚሉን። እዚህች መሬት ላይ ለአንድም ገበሬ ምንም አልተከፈልም። ግምት ሳይከፍሉ በነፃ ለመውሰድ ነው ለገበሬው ከፍለናል የሚሉት" ይላል።
አንዋር የራሱን ልጆች ዋቢ አድርጎ፥ የከተማው አስተዳደር ተማሪ ሕፃናት የጀመሩትን የትምህርት ዓመት እስኪጠናቀቅ ቢታገሳቸው መልካም እንደነበር ይገልፃል። መንግስት ተፈናቃዮችን ለማቋቋም፥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደግሞ የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለመሰብሰብ እየጣሩ እንዳሉ በሚናገሩበት ሰዓት እርሱ እና ጎረቤቶቹ ቤት አልባ የሆኑበትን እርምጃ ግራ የሚያጋባ ነው ይላል።
"እንደዜግነታችን እንኳ መጠለያ እንኳ አዘጋጅተውልን እዚህ ጋ እንኳ መቀመጥ ትችላለችሁ ባላሉበት ሁኔታ ነው ያፈረሱብን።
ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰብ ደግሞ የአካባቢው አስተዳደር "ለይዞታችን ካርታ እንሰጣችኋለን መረጃ አምጡ በማለት መረጃ ሲሰባሰብ ቆይቷል" በማለት ያስረዳሉ።
አንዳንድ ግለሰቦች እንደሚሉት ቤታቸው እንደሚፈርስ #ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ከ10 ቀን እንደማይበልጥና ይህም ቤት ፈልጎ ለመልቀቅ በቂ ጊዜ እንዳይደለ አስረድተዋል።
"መንግሥት በርቱ #ህጋዊ እናደርገላችኋለን እያለን እስካሁን ለመብራትና ውሃ የከፈልነው ብቻ ከመቶ ሺህ ብር ይበልጣል። ሆኖም ድንገት በሰባት ቀን ውስጥ ቤታችሁን አፍረሱ ተባልን። እኛ ማፍረስ ስላልቻልን መንግሥት እያፈረሰው ነው" ብለዋል።
ሌላኛዉ አስተያት ሰጭ እንደገለጹት ደግሞ "ሚስቴ ከወለደች ሦስት ቀኗ ነዉ። ከቤት ተባርራ ጎዳና ላይ ነች። ቤቱን ሲያፈርሱት እባካችሁ ሚስቴ ከወለደች ሦስት ቀኗ ነዉ ትንሽ ታገሱኝ ስል 'ምን አገባኝ ከእኔ #አልወለደች' ሲል አንደኛው ምላሽ ሰጠኝ። እኔም የሚሰማ መንግሥት ይኖራል ብዬ ለአቤቱታ ትቻት መጣሁ። ሜዳ ላይ በተወጠረ ሸራ ውስጥ ነው ያለችው። ምን እንደሆነች አላውቅም" ሲሉ የተሰማቸውን #ሐዘን ይገልፃሉ።
ትናንት ቤታቸዉ የፈረሰባቸዉ ግለሰቦች ዛሬ ጠዋት ተሰባስበዉ ወደ ኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሮ ቢያመሩም እሳቸዉን ማናገር አትችሉም ተብለው ወደ ክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ መላካቸውን ነግረውናል። ነገር ግን ከክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮም ያገኙት ምላሽ "ቤታችሁ ከመፍረስ አይድንም። ልንተባበራችሁ አንችልም" የሚል መሆኑን ገልጸውልናል።
አቤቱታ አቅራቢዎቹ በመቀጠል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ቢያመሩም "ጉዳያችሁን እዛዉ ጨርሱ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ጉዳይ ጣልቃ አይገቡም" የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸዉ ለቢቢሲ ተናገረዋል።
"መንግሥት ጎዳና የወጡትን #እንሰብስብ ሲል ደስ ብሎን እኛም ገንዘብ እያዋጣን ነበር። ነገር ግን በምትኩ ቤታችን የተቀመጥነውን #ወደጎዳና እያባረርን ነዉ። እቃ እራሱ ማውጣት አልቻልንም ከነቤታችን ነዉ እየፈረሰ ያለው" ብለዋል አስተያየት ሰጭዎቹ።
በዛሬው ዕለትም የማፍረስ ተግባሩ የቀጠለ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰቦች በቤተ ክርስትያንና በመስኪዶች ተጠልለው ማደራቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ ዙሪያ በኦሮሚያ ልዩ ዞን በሚገኙ ከተሞች የህገ ወጥ ግንባታ መስፋፋት እንዳለ በጥናት ማረጋገጡን የኦሮሚያ ክልል የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታወቆ እንደነበር ፋና ብሮድካስቲንግ ዘግቦ ነበር።
በዚህም በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር 67 ነጥብ 2 ሄክታር መሬት እና በቤት ደረጃ ከ12ሺ በላይ ቤቶች በህገወጥ መንገድ መገንባታቸውን መለየታቸውን ተገልጾ ነበር።
ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የለገጣፎ -ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር አረንጓዴ ቦታዎችን፥ የወንዝ ዳርቻዎችን፥ ከፈቃድ ውጭ የተያዙ እና ካሳ ተከፍሎባቸው ግንባታ የተካሄደባቸው ናቸው ያላቸውን ቤቶች እያፈረሰ ነው።
ቤት ማፍረሱ በትናንት ማክሰኞ ዕለት የተጀመረ ሲሆን የከተማው ከንቲባ የሆኑት በ10 ሺህዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ፈርሰው የሕዝብ መናፈሻ ይሆናሉ ማለታቸው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
በዛ ያለ ቁጥር ያላቸው ተጨማሪ ቤቶች እንደሚፈርሱ የሚጠበቅ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎች እርምጃው ዱብ ዕዳ ሆኖብናል ይላሉ።
በ1990ዎቹ መጀመሪያ ከአርሶ አደር መሬት ገዝቶ፤ ጎጆ ቀልሶ በስፍራው መኖር ሲጀምር አካባቢው ከሞላ ጎደል በማሣዎች የተከበበ፣ መሠረት ልማት የናፍቀው እንደነበር የሚገልፀው አንዋር አህመድ ቤቶቻቸው በትናንትናው ዕለት ከፈረሱባቸው አባወራዎች አንዱ ነው።
እኛ ስንገባ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ራሱ አልተዋቀረም ነበር የሚለው አንዋር፤ ለቤቱ ካርታ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ ባይሳካም "ውሃና መብራት አስገብተናል፣ የቤት ቁጥር ተሰጥቶናል፣ የመሬት ግብር እንከፍላለን" ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል።
መንደሩን የሚያቋርጡ መንገዶች በሚቀየሱበት ወቅት ኗሪዎች ሁለት፣ ሦስት ጊዜ ቤቶቻቸውን እና አጥሮቻቸውን አፍረሰው መሥራታቸውን የሚያስታውሰው አንዋር፤ የአሁኑ እርምጃ ፈጣን እንዲሁም የነዋሪዎቹን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ እንደሆነ ይናገራል።
"ይህ የመኖሪያ መንደር እንደሆነ ይታወቃል፤ አረንጓዴ መናፈሻ ይሁን የሚለው አዲስ ማስተር ፕላን እዚያው ቢሮ ቁጭ ብለው የወሰኑት ነገር ነው። ምንም ሳያወያዩን ነው ድንገት ውሳኔ ይዘው የመጡት።"
በወርሃ የካቲት መባቻ የ'ውጡ' ትዕዛዝ እንደደረሰው ለቢቢሲ የገለፀው አንዋር፤ አስር አባላት ያሉትን ቤተሰቡን ይዞ የትም ለመሄድ እንዳልቻለ ይገልፃል።
እንደአንዋር ገለፃ ቤቶቻቸውን ያጡ አንዳንድ ነዋሪዎች በእምነት ተቋማት ተጠልለዋል።
"ያለምንም ቅደም ሁኔታ ነው ያፈረርሱብን። ዕቃችን እስክንሸክፍ እንኳ ጊዜ አልሰጡንም" ሲል ጨምሮ ለቢቢሲ ተናግሯል።
በአካባቢው መሬት ገዝታ መኖር ከጀመረች ስምንት ዓመት እንደሞላት ለቢቢሲ የገለፀች ሌላ ነዋሪ፤ የመኖሪያ ቤቷ ባይፈርስም በስጋት መወጠሯ እንዳልቀረ ታስረዳለች።
"ትናንትና ብዙ ሕፃናት ሜዳ ላይ ሲወድቁ አይቻለሁ" የምትለው ነዋሪ ይህም ያለፈቃድ የሚሠሩ ቤቶችን አስመልክቶ "ሰማይ ላይ ነው እንጅ ምድር ላይ ጨረቃ የለም" በሚል ከመንግሥት ተሰጥቷል የምትለውን ተስፋ እና መተማመኛን የናደ እንደሆነባት ትናገራለች።
"ዱብ ዕዳ ነው የሆነብን፤ የት እንሄዳለን?"
በስፍራው አስራ ዘጠኝ ዓመት መኖሩን ለቢቢሲ የነገረ ሌላ ነዋሪ በበኩሉ የከተማው አስተዳደር ለገበሬው ካሳ የተከፈለበት ቦታ ላይ የተሠሩ ቤቶችን ነው የማፈርሰው ማለቱን እውነት አይደለም ይላል።
"ይሄ ቤት የተሰራው በ1992 ነው። ማዘጋጃው የተሰራው ከዓመታት በኋላ ነው። የት ሆነው ነው የከፈሉት? ለገበሬው ካሳ የከፈልንበት መሬት ላይ ነው የሰፈራችሁት ነው የሚሉን። እዚህች መሬት ላይ ለአንድም ገበሬ ምንም አልተከፈልም። ግምት ሳይከፍሉ በነፃ ለመውሰድ ነው ለገበሬው ከፍለናል የሚሉት" ይላል።
አንዋር የራሱን ልጆች ዋቢ አድርጎ፥ የከተማው አስተዳደር ተማሪ ሕፃናት የጀመሩትን የትምህርት ዓመት እስኪጠናቀቅ ቢታገሳቸው መልካም እንደነበር ይገልፃል። መንግስት ተፈናቃዮችን ለማቋቋም፥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደግሞ የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለመሰብሰብ እየጣሩ እንዳሉ በሚናገሩበት ሰዓት እርሱ እና ጎረቤቶቹ ቤት አልባ የሆኑበትን እርምጃ ግራ የሚያጋባ ነው ይላል።
"እንደዜግነታችን እንኳ መጠለያ እንኳ አዘጋጅተውልን እዚህ ጋ እንኳ መቀመጥ ትችላለችሁ ባላሉበት ሁኔታ ነው ያፈረሱብን።
ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰብ ደግሞ የአካባቢው አስተዳደር "ለይዞታችን ካርታ እንሰጣችኋለን መረጃ አምጡ በማለት መረጃ ሲሰባሰብ ቆይቷል" በማለት ያስረዳሉ።
አንዳንድ ግለሰቦች እንደሚሉት ቤታቸው እንደሚፈርስ #ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ከ10 ቀን እንደማይበልጥና ይህም ቤት ፈልጎ ለመልቀቅ በቂ ጊዜ እንዳይደለ አስረድተዋል።
"መንግሥት በርቱ #ህጋዊ እናደርገላችኋለን እያለን እስካሁን ለመብራትና ውሃ የከፈልነው ብቻ ከመቶ ሺህ ብር ይበልጣል። ሆኖም ድንገት በሰባት ቀን ውስጥ ቤታችሁን አፍረሱ ተባልን። እኛ ማፍረስ ስላልቻልን መንግሥት እያፈረሰው ነው" ብለዋል።
ሌላኛዉ አስተያት ሰጭ እንደገለጹት ደግሞ "ሚስቴ ከወለደች ሦስት ቀኗ ነዉ። ከቤት ተባርራ ጎዳና ላይ ነች። ቤቱን ሲያፈርሱት እባካችሁ ሚስቴ ከወለደች ሦስት ቀኗ ነዉ ትንሽ ታገሱኝ ስል 'ምን አገባኝ ከእኔ #አልወለደች' ሲል አንደኛው ምላሽ ሰጠኝ። እኔም የሚሰማ መንግሥት ይኖራል ብዬ ለአቤቱታ ትቻት መጣሁ። ሜዳ ላይ በተወጠረ ሸራ ውስጥ ነው ያለችው። ምን እንደሆነች አላውቅም" ሲሉ የተሰማቸውን #ሐዘን ይገልፃሉ።
ትናንት ቤታቸዉ የፈረሰባቸዉ ግለሰቦች ዛሬ ጠዋት ተሰባስበዉ ወደ ኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሮ ቢያመሩም እሳቸዉን ማናገር አትችሉም ተብለው ወደ ክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ መላካቸውን ነግረውናል። ነገር ግን ከክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮም ያገኙት ምላሽ "ቤታችሁ ከመፍረስ አይድንም። ልንተባበራችሁ አንችልም" የሚል መሆኑን ገልጸውልናል።
አቤቱታ አቅራቢዎቹ በመቀጠል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ቢያመሩም "ጉዳያችሁን እዛዉ ጨርሱ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ጉዳይ ጣልቃ አይገቡም" የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸዉ ለቢቢሲ ተናገረዋል።
"መንግሥት ጎዳና የወጡትን #እንሰብስብ ሲል ደስ ብሎን እኛም ገንዘብ እያዋጣን ነበር። ነገር ግን በምትኩ ቤታችን የተቀመጥነውን #ወደጎዳና እያባረርን ነዉ። እቃ እራሱ ማውጣት አልቻልንም ከነቤታችን ነዉ እየፈረሰ ያለው" ብለዋል አስተያየት ሰጭዎቹ።
በዛሬው ዕለትም የማፍረስ ተግባሩ የቀጠለ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰቦች በቤተ ክርስትያንና በመስኪዶች ተጠልለው ማደራቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ ዙሪያ በኦሮሚያ ልዩ ዞን በሚገኙ ከተሞች የህገ ወጥ ግንባታ መስፋፋት እንዳለ በጥናት ማረጋገጡን የኦሮሚያ ክልል የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታወቆ እንደነበር ፋና ብሮድካስቲንግ ዘግቦ ነበር።
በዚህም በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር 67 ነጥብ 2 ሄክታር መሬት እና በቤት ደረጃ ከ12ሺ በላይ ቤቶች በህገወጥ መንገድ መገንባታቸውን መለየታቸውን ተገልጾ ነበር።
ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia