የትምህርት ቤት መፀዳጃ ቤት #ተደርምሶ የ3 ታዳጊ ተማሪዎች ህይወት ተቀጠፈ።
ዛሬ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የጉሎመኻዳ ወረዳ በሚገኘው " መረታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት " መፀዳጃ ቤት ተደርምሶ 3 ተማሪዎች ወዲያው ህይወታቸው አልፏል።
የመደርመስ አደጋው በእረፍት ጊዜ ከረፋዱ በ4:00 ሰአት የደረሰ ሲሆን የሴቶች የጋራ መፃዳጃ ቤት ሲጠቀሙ ከነበሩ 6 እንስት ተማሪዎች 3ቱ ወድያውኑ ሲሞቱ 3ቱ ቆስለው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።
ትምህርት ቤቱ ፤ ለመፀዳጃ ቤቱ መደርመስ መንስኤው በአከባቢው የዘነበ ከባድ ዝናብ እና መፀዳጃ ቤቱ ለረጅም ጊዜ ማገልገሉ እንደሆነ ገልጿል።
አደጋው በት/ቤቱ ተማሪዎች ፣ መምህራን እና ወላጆች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን መፍጠሩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ያገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
ዛሬ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የጉሎመኻዳ ወረዳ በሚገኘው " መረታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት " መፀዳጃ ቤት ተደርምሶ 3 ተማሪዎች ወዲያው ህይወታቸው አልፏል።
የመደርመስ አደጋው በእረፍት ጊዜ ከረፋዱ በ4:00 ሰአት የደረሰ ሲሆን የሴቶች የጋራ መፃዳጃ ቤት ሲጠቀሙ ከነበሩ 6 እንስት ተማሪዎች 3ቱ ወድያውኑ ሲሞቱ 3ቱ ቆስለው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።
ትምህርት ቤቱ ፤ ለመፀዳጃ ቤቱ መደርመስ መንስኤው በአከባቢው የዘነበ ከባድ ዝናብ እና መፀዳጃ ቤቱ ለረጅም ጊዜ ማገልገሉ እንደሆነ ገልጿል።
አደጋው በት/ቤቱ ተማሪዎች ፣ መምህራን እና ወላጆች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን መፍጠሩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ያገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia