በጅግጅጋ በተከሰተ #ግጭት ሁለት ሰዎች ተገደሉ‼️
.
.
ትናንት በሶማሌ ክልል መዲና- ጅግጅጋ የሃይማኖት ክብረ በዓልን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተነገረ።
የከተማዋ ነዋሪዎች የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታይ የሆኑ የጂግጂጋ ከተማ ነዋሪዎች የአስተርዮ ማርያም ክብረ በዓልን ከጂግጂጋ ከተማ 35 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ጉርሱም ወረዳ አክብረው ወደ ከተማው ሲመለሱ በተደራጁ ወጣቶች በድንጋይ መደብደባቸውን ነግረውናል።
በስፍራው የሚገኘው የቢቢሲ ሶማልኛ ጋዜጠኛም ሁለት ሰዎች መገደላቸውን እና አራት ሰዎች ደግሞ ለጉዳት መዳረጋቸውን ዘግቧል።
የበዓሉ ተሳታፊ የነበሩ አንድ የሃይማኖት አባት "ከቤተክርስቲያን መልስ ከተማው መግቢያ ላይ የተደራጁ ወጣቶች ድንጋይ በመወርወር ሰዎች ፈነከቱ፤ መኪኖችንም ሰባበሩ" ብለዋል።
የሃይማኖት አባቱ እንደሚሉት በጥይት ተመትተው የሞቱት ሁለቱ ሰዎች የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች ናቸው፤ ግጭቱን ለመበተን ከመጡ የጸጥታ አስከባሪዎች ጋር በተከሰተ ግጭት ሁለቱ ሰዎች መገደላቸውንም አስረድተዋል።
ሌላው BBC ያነጋገራቸው የጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ መምህር ትናንት ከአዲስ አበባ ወደ ጂግጂጋ እየተመለሱ እንደነበረ በማስታወስ ትናንት አመሻሽ ላይ ሐረር ከተማ ሲደርሱ ወደ ጂግጂጋ ከተማ ዘልቀው መግባት እንደማይችሉ ከተነገራቸው በኋላ ሐረር ከተማ ለማደር መገደዳቸውን ይናገራሉ።
የዩኒቨርሲቲ መምህሩ እንደሚሉት ዛሬ ጠዋት ወደ ጂግጂጋ እንደተመለሱ እና ከተማዋ ላይ የተለመደው ዓይነት እንቅስቃሴ እንደሌለ ይናገራሉ።
የሃይማኖት አባቱ በበኩላቸው በከፊል መንገዶች ዝግ እንደሆኑ እና የመኪና እና የንግድ እንቅስቃሴ በከተማዋ አይታይም ብለዋል።
የግጭቱ መንስኤ እና ጥቃቱ እንዴት እንደተፈጸም እንዲያስረዱን በስልክ የጠየቅናቸው የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አብዱላሂ ሞሃመድ መውሊድ ''ጉዳዩን እያጣራን ስለሆነ አሁን አስተያየት መስጠት አልችልም'' የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ከዚህ ቀደም በጂግጂጋ ተከስቶ ለነበረው ሃይማኖት ተኮር ግጭት መንግሥት 'ሄጎ' ተብሎ የሚጠራውን ቡድን ተጠያቂ አድርጎ ነበር።
ሐምሌ 27፣ 2010 ዓ. ም. ጂግጂጋን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች 96 ሰዎች መሞታቸውን እና ለግድያውም 'ሄጎ' የተባለው ቡድን ተጠያቂ እንደሆነ በወቅቱ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የነበሩት #ዘይኑ_ጀማል ለቢቢሲ ገልጸው ነበር።
የቀድሞ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ሄጎ የሚባለውን ቡድን የፈጠሩትና እቅዱን ያቀነባበሩት የቀድሞ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ናቸው ብለው ነበር።
ምንጭ፦ bbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
ትናንት በሶማሌ ክልል መዲና- ጅግጅጋ የሃይማኖት ክብረ በዓልን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተነገረ።
የከተማዋ ነዋሪዎች የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታይ የሆኑ የጂግጂጋ ከተማ ነዋሪዎች የአስተርዮ ማርያም ክብረ በዓልን ከጂግጂጋ ከተማ 35 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ጉርሱም ወረዳ አክብረው ወደ ከተማው ሲመለሱ በተደራጁ ወጣቶች በድንጋይ መደብደባቸውን ነግረውናል።
በስፍራው የሚገኘው የቢቢሲ ሶማልኛ ጋዜጠኛም ሁለት ሰዎች መገደላቸውን እና አራት ሰዎች ደግሞ ለጉዳት መዳረጋቸውን ዘግቧል።
የበዓሉ ተሳታፊ የነበሩ አንድ የሃይማኖት አባት "ከቤተክርስቲያን መልስ ከተማው መግቢያ ላይ የተደራጁ ወጣቶች ድንጋይ በመወርወር ሰዎች ፈነከቱ፤ መኪኖችንም ሰባበሩ" ብለዋል።
የሃይማኖት አባቱ እንደሚሉት በጥይት ተመትተው የሞቱት ሁለቱ ሰዎች የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች ናቸው፤ ግጭቱን ለመበተን ከመጡ የጸጥታ አስከባሪዎች ጋር በተከሰተ ግጭት ሁለቱ ሰዎች መገደላቸውንም አስረድተዋል።
ሌላው BBC ያነጋገራቸው የጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ መምህር ትናንት ከአዲስ አበባ ወደ ጂግጂጋ እየተመለሱ እንደነበረ በማስታወስ ትናንት አመሻሽ ላይ ሐረር ከተማ ሲደርሱ ወደ ጂግጂጋ ከተማ ዘልቀው መግባት እንደማይችሉ ከተነገራቸው በኋላ ሐረር ከተማ ለማደር መገደዳቸውን ይናገራሉ።
የዩኒቨርሲቲ መምህሩ እንደሚሉት ዛሬ ጠዋት ወደ ጂግጂጋ እንደተመለሱ እና ከተማዋ ላይ የተለመደው ዓይነት እንቅስቃሴ እንደሌለ ይናገራሉ።
የሃይማኖት አባቱ በበኩላቸው በከፊል መንገዶች ዝግ እንደሆኑ እና የመኪና እና የንግድ እንቅስቃሴ በከተማዋ አይታይም ብለዋል።
የግጭቱ መንስኤ እና ጥቃቱ እንዴት እንደተፈጸም እንዲያስረዱን በስልክ የጠየቅናቸው የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አብዱላሂ ሞሃመድ መውሊድ ''ጉዳዩን እያጣራን ስለሆነ አሁን አስተያየት መስጠት አልችልም'' የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ከዚህ ቀደም በጂግጂጋ ተከስቶ ለነበረው ሃይማኖት ተኮር ግጭት መንግሥት 'ሄጎ' ተብሎ የሚጠራውን ቡድን ተጠያቂ አድርጎ ነበር።
ሐምሌ 27፣ 2010 ዓ. ም. ጂግጂጋን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች 96 ሰዎች መሞታቸውን እና ለግድያውም 'ሄጎ' የተባለው ቡድን ተጠያቂ እንደሆነ በወቅቱ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የነበሩት #ዘይኑ_ጀማል ለቢቢሲ ገልጸው ነበር።
የቀድሞ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ሄጎ የሚባለውን ቡድን የፈጠሩትና እቅዱን ያቀነባበሩት የቀድሞ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ናቸው ብለው ነበር።
ምንጭ፦ bbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ለማ እና አቶ ገዱ~ኔዘርላንድ‼️
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ እና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #በኔዘርላንድ የሚገኙ ኩባንያዎችን ጎበኙ፡፡
የሁለቱ ርዕሳነ መስተዳድሮች የጉብኝቱ አላማ በኢትዮጵያ እየተንቀሳቀሱ ከሚገኙ የኔዘርላንድ ኩባንያዎች ጋር ለማስተዋወቅ ነው ተብሏል፡፡
በዚህም በአለም አቀፍ ደረጃ የኢንቨስትመንት ተግዳሮት በሆኑ ጉዳች ዙሪያ ውይይት እንዳካሄዱ ተጠቁሟል፡፡
ኔዘርላንድ በምስራቅ አፍሪካ በተለይ ከኢትዮጰያ ጋር ለረጅም ጊዜ የዘለቀ የኢኮኖሚ እና የልማት ግንኙነት እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
በአሁን ወቅት 100 የሚሆኑ የሀገሪቱ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የተሰማሩ ሲሆን እነዚህም 70 ሺህ ለሚሆኑ ኢትዮጵያውያን የስራ እድል መፍጠራቸው ተነግሯል፡፡
ምቹ የአየር ፀባይ፣ትልቅ የሀገር ውስጥ ገቢያ እና ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ኢትዮጵያ በኔዘርላንድ ኩባንያዎች ተመራጭ እንድትሆን አስችሏታል ተብሏል፡፡
ምንጭ፡- Nederland en Afrika
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ እና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #በኔዘርላንድ የሚገኙ ኩባንያዎችን ጎበኙ፡፡
የሁለቱ ርዕሳነ መስተዳድሮች የጉብኝቱ አላማ በኢትዮጵያ እየተንቀሳቀሱ ከሚገኙ የኔዘርላንድ ኩባንያዎች ጋር ለማስተዋወቅ ነው ተብሏል፡፡
በዚህም በአለም አቀፍ ደረጃ የኢንቨስትመንት ተግዳሮት በሆኑ ጉዳች ዙሪያ ውይይት እንዳካሄዱ ተጠቁሟል፡፡
ኔዘርላንድ በምስራቅ አፍሪካ በተለይ ከኢትዮጰያ ጋር ለረጅም ጊዜ የዘለቀ የኢኮኖሚ እና የልማት ግንኙነት እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
በአሁን ወቅት 100 የሚሆኑ የሀገሪቱ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የተሰማሩ ሲሆን እነዚህም 70 ሺህ ለሚሆኑ ኢትዮጵያውያን የስራ እድል መፍጠራቸው ተነግሯል፡፡
ምቹ የአየር ፀባይ፣ትልቅ የሀገር ውስጥ ገቢያ እና ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ኢትዮጵያ በኔዘርላንድ ኩባንያዎች ተመራጭ እንድትሆን አስችሏታል ተብሏል፡፡
ምንጭ፡- Nederland en Afrika
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ #ጉብኝታቸዉን አጠናቀዉ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ በዝግጅት ላይ ያሉት የጀርመኑ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር የሚበሩበት አዉሮፕላን የቴክኒክ #እክል ገጥሞት መዘግየቱ ተሰምቷል። ሃምሳ አምስት አባላትን ያካተተ የልዑካን ቡድን አባላትን እና ባለንዋዮችን ይዘዉ ወደ ኢትዮጵያ የተጓዙት ፕሬዝዳንት ሽታይንማየር አዉሮፕላናቸዉ እስኪጠገን አዲስ አበባ በሆቴል እንደሚቆዩ ተነግሯል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሞቶ የተገኘውና ወላጆቹ #አልቅሰው የቀበሩት ወጣት ከሳምንታት በኋላ ወደ ወላጆቹ ተመልሷል‼️
.
.
በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ አስተዳደር አንድ ወጣት ማንነታቸው #ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ ይገኛል፡፡ ይህም ከፖሊስ ጆሮ ይደርሳል፡፡
ጉዳዩን የሰማው ፖሊስ የሟችንም ሆነ የገዳይን ማንነት ለማወቅ ያደረገው ጥረት ለጊዜው ሳይሳካለት ይቀራል፡፡ የወንጀሉ መርማሪ ሳጅን አየነው ጎበዜ እንዳሉት ማንነቱ ያልታወቀውን ሟች ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን ወደ ቆቦ ሆስፒታል ይወስዱታል፡፡
ነገር ግን ሐሙስ ሕዳር 20 ቀን 2011ዓ.ም ከሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ 02 ቀበሌ ገረገራ አካባቢ ከምሽቱ 5፡00 አቶ ታረቀ መንግሥቴ የተባሉ ሰው ወደ ፖሊስ በመሄድ ‹‹ሟች የእኔ ልጅ ነው›› በማለት በኮንትራት መኪና አስከሬኑን መውሰዳቸውን ሳጅን አየነው ለአብመድ ተናግረዋል፡፡
አቶ ታረቀ ልጃቸውን ከቀበሩ በኋላ ሕዳር 24 ቀን ወደ ቆቦ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት በመሄድ ክስ መመሥረታቸውንና የልጃቸው ገዳዮች እንዲነግሯቸው መጠየቃቸውንና ፖሊስ በግድያው ዙሪያ የደረሰበትን ለአባት መንገሩን ሳጅን አየነው አስረድተዋል፡፡
አባት አስከሬኑን ሊረከቡ በመጡበት ጊዜ ስለልጃቸው የሚያውቁትን ልዩ ምልክት ተጠይቀው እንደተናገሩና የሟቹን ፎቶግራፍ ሲያዩ በጣም እንዳለቀሱ፤ እንዳጽናኗቸውም መርማሪ ፖሊሱ ተናግረዋል፡፡
የልጃቸውን አስከሬን ከፖሊስ ተቀብለው ሌሊቱን ሲጓዙ ያደሩት አቶ ታረቀ ሕዳር 21 ቀን 2011ዓ.ም ወዳጅ ዘመድ እያስተዛዘናቸው በፍላቂት ገረገራ ደብረ ሃይማኖት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ቀብሩን ያስፈጽማሉ፡፡
‹‹ቆቦ ሰው መሞቱንና የመቄት ሰው ነው መባሉን ስሰማ አጣራሁ፤ ሊቀበር መሆኑን ስሰማም ለማጣራት ሄድኩ፡፡ ደርሼም አስከሬኑን አገላብጨ አየሁ፤ ልጄ ነው፡፡ አምጥቼ ከዘመድ ወዳጅ ጋር ሆኜ ቀበርኩ፡፡ ሥርዓተ ፍትሐቱንም አስፈጸምኩ፤ ሳልስት፣ ሰባት አስቀደስኩለት፡፡ ሰላሳውን ላስቀድስ እየተዘጋጀሁ ሳለ ግን ነገሮች ተቀዬሩ›› ብለዋል አቶ ታረቀ መንግሥቴ ለአብመድ ሲናገሩ፡፡
‹‹ድንገት ስልክ ተደወለ፤ አነሳሁት፡፡ ‹ሞቷል ብላችሁ እንዳለቀሳችሁ ሰምቻለሁ› ብሎ ልጀ ደወለ፡፡ እሱ መሆኑን ስላላመንኩት የተለያዬ ዘመድ እንዲጠራ አደረኩት፤ ተጠራልኝ፡፡ ከዚያም ወደ ቤተሰቡ መጣ›› ብለዋል አባት፡፡
በወቅቱ የሟችን አስከሬን ሲያዩ ከእጁ ጣት ላይና ከጥርሱ ልዩ ምልክትን መሠረት አድርገው ልጃቸው መሆኑን እንዳረጋገጡ የገለጹት አባት ስለተፈጠረው ነገር ተገርመዋል፡፡
‹‹ሞቷል›› ተብሎ የተለቀሰለት አበበ ቤተሰቦቹ ለማመን መቸገራቸውን ገልፆ ‹‹ከሟች ጋር እንዴት እንደተመሳሰልኩ ገርሞኛል፡፡ ለማንኛውም አሁን በወላጆቼ ፊት በመገኜቴና በሕይወት በመሆኔ ደስተኛ ነኝ›› ብሏል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ አስተዳደር አንድ ወጣት ማንነታቸው #ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ ይገኛል፡፡ ይህም ከፖሊስ ጆሮ ይደርሳል፡፡
ጉዳዩን የሰማው ፖሊስ የሟችንም ሆነ የገዳይን ማንነት ለማወቅ ያደረገው ጥረት ለጊዜው ሳይሳካለት ይቀራል፡፡ የወንጀሉ መርማሪ ሳጅን አየነው ጎበዜ እንዳሉት ማንነቱ ያልታወቀውን ሟች ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን ወደ ቆቦ ሆስፒታል ይወስዱታል፡፡
ነገር ግን ሐሙስ ሕዳር 20 ቀን 2011ዓ.ም ከሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ 02 ቀበሌ ገረገራ አካባቢ ከምሽቱ 5፡00 አቶ ታረቀ መንግሥቴ የተባሉ ሰው ወደ ፖሊስ በመሄድ ‹‹ሟች የእኔ ልጅ ነው›› በማለት በኮንትራት መኪና አስከሬኑን መውሰዳቸውን ሳጅን አየነው ለአብመድ ተናግረዋል፡፡
አቶ ታረቀ ልጃቸውን ከቀበሩ በኋላ ሕዳር 24 ቀን ወደ ቆቦ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት በመሄድ ክስ መመሥረታቸውንና የልጃቸው ገዳዮች እንዲነግሯቸው መጠየቃቸውንና ፖሊስ በግድያው ዙሪያ የደረሰበትን ለአባት መንገሩን ሳጅን አየነው አስረድተዋል፡፡
አባት አስከሬኑን ሊረከቡ በመጡበት ጊዜ ስለልጃቸው የሚያውቁትን ልዩ ምልክት ተጠይቀው እንደተናገሩና የሟቹን ፎቶግራፍ ሲያዩ በጣም እንዳለቀሱ፤ እንዳጽናኗቸውም መርማሪ ፖሊሱ ተናግረዋል፡፡
የልጃቸውን አስከሬን ከፖሊስ ተቀብለው ሌሊቱን ሲጓዙ ያደሩት አቶ ታረቀ ሕዳር 21 ቀን 2011ዓ.ም ወዳጅ ዘመድ እያስተዛዘናቸው በፍላቂት ገረገራ ደብረ ሃይማኖት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ቀብሩን ያስፈጽማሉ፡፡
‹‹ቆቦ ሰው መሞቱንና የመቄት ሰው ነው መባሉን ስሰማ አጣራሁ፤ ሊቀበር መሆኑን ስሰማም ለማጣራት ሄድኩ፡፡ ደርሼም አስከሬኑን አገላብጨ አየሁ፤ ልጄ ነው፡፡ አምጥቼ ከዘመድ ወዳጅ ጋር ሆኜ ቀበርኩ፡፡ ሥርዓተ ፍትሐቱንም አስፈጸምኩ፤ ሳልስት፣ ሰባት አስቀደስኩለት፡፡ ሰላሳውን ላስቀድስ እየተዘጋጀሁ ሳለ ግን ነገሮች ተቀዬሩ›› ብለዋል አቶ ታረቀ መንግሥቴ ለአብመድ ሲናገሩ፡፡
‹‹ድንገት ስልክ ተደወለ፤ አነሳሁት፡፡ ‹ሞቷል ብላችሁ እንዳለቀሳችሁ ሰምቻለሁ› ብሎ ልጀ ደወለ፡፡ እሱ መሆኑን ስላላመንኩት የተለያዬ ዘመድ እንዲጠራ አደረኩት፤ ተጠራልኝ፡፡ ከዚያም ወደ ቤተሰቡ መጣ›› ብለዋል አባት፡፡
በወቅቱ የሟችን አስከሬን ሲያዩ ከእጁ ጣት ላይና ከጥርሱ ልዩ ምልክትን መሠረት አድርገው ልጃቸው መሆኑን እንዳረጋገጡ የገለጹት አባት ስለተፈጠረው ነገር ተገርመዋል፡፡
‹‹ሞቷል›› ተብሎ የተለቀሰለት አበበ ቤተሰቦቹ ለማመን መቸገራቸውን ገልፆ ‹‹ከሟች ጋር እንዴት እንደተመሳሰልኩ ገርሞኛል፡፡ ለማንኛውም አሁን በወላጆቼ ፊት በመገኜቴና በሕይወት በመሆኔ ደስተኛ ነኝ›› ብሏል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
11 ሺህ ሊትር ነዳጅ ተያዘ‼️
ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምት በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 11 ሺህ ሊትር ነዳጅ መያዙን የኢሉገላን ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ።
ነዳጁ የተያዘው በኤፍኤስአር የጭነት ተሸከርካሪ ሲጓጓዝ መሆኑን የወረዳው ፖሊስ መምሪያ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር #ዱጋሳ_አሰፋ ገልጸዋል።
ነዳጁ የተያዘው አሽከርካሪው ነዳጁን ለመሸጥ ከገዢዎች ጋር ሲስማማ በነበረበት ወቅት ለፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ነው ተብሏል።
አሽከርካሪው በወቅቱ ለመሰወር ቢሞክርም በህብረተሰቡ ትብብርና በፖሊስ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል።
ምክትል ኢንስፔክተሩ ህብረተሰቡ ህገ ወጥነትንና ወንጀልን ለመከላከል እያደረገ ያለው ጥረት የሚያበረታታ መሆኑን ጠቅሰው፥ ወደፊትም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
ምንጭ፦ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምት በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 11 ሺህ ሊትር ነዳጅ መያዙን የኢሉገላን ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ።
ነዳጁ የተያዘው በኤፍኤስአር የጭነት ተሸከርካሪ ሲጓጓዝ መሆኑን የወረዳው ፖሊስ መምሪያ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር #ዱጋሳ_አሰፋ ገልጸዋል።
ነዳጁ የተያዘው አሽከርካሪው ነዳጁን ለመሸጥ ከገዢዎች ጋር ሲስማማ በነበረበት ወቅት ለፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ነው ተብሏል።
አሽከርካሪው በወቅቱ ለመሰወር ቢሞክርም በህብረተሰቡ ትብብርና በፖሊስ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል።
ምክትል ኢንስፔክተሩ ህብረተሰቡ ህገ ወጥነትንና ወንጀልን ለመከላከል እያደረገ ያለው ጥረት የሚያበረታታ መሆኑን ጠቅሰው፥ ወደፊትም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
ምንጭ፦ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሳይንት ወረዳ‼️
በአማራ ክልል በአምሀራ ሳይንት ወረዳ በአጅባር ከተማ በተቀሰቀሰ #ተቃውሞ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቋረጣቸውን ነዋሪዎች ገለጹ። ትላንት ለተቃውሞ የወጡ ነዋሪዎች ከተማይቱን ከደሴ ከተማ ጋር የሚያገናኛት መንገድን ዛሬም ዘግተው ውለዋል።
ከደሴ በስተምዕራብ 189 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የአጅባር ከተማ በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ አንድ ነዋሪ ዛሬ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ እንደገለጹት የትላንቱን ተቃውሞ ተከትሎ ከተማይቱ ዛሬ “ጸጥ ረጭ” ብላ ውላለች። “ሱቅም ዝግ ነው። መስሪያ ቤቶች ዝግ ናቸው። የትራንስፖርት እንቅስቃሴ የለም” ሲሉ በከተማይቱ ያለውን ሁኔታ የገለጹት ነዋሪው “መንገዶችም በድንጋይ እና በሌሎች ቁሳቁሶች ተዘግተዋል” ብለዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ስር የምትገኘው የአጅባር ከተማ ሰባት ሺህ ገደማ ነዋሪዎች አሏት። ነዋሪዎቿ “አካባቢያችን ከልማት ወደ ኋላ ቀርቷል፤ የክልል እና የዞን ባለስልጣናት ችግራችንን ሊመለከቱልን አልቻሉም” በሚል ትላንት እስከ እኩለ ቀን ድረስ የዘለቀ የአደባባይ ተቃውሞ አድርገው ነበር። ነዋሪዎቹ ጎማዎችን በማቃጠል መንገዶችን ዘግተዋል። በችግሩ ዙሪያ ለመወያየት ከደቡብ ወሎ ዞን የመጡ ባለስልጣናት ከመንገድ ተመልሰዋል መባሉ ነዋሪዎቹን ይበልጥ እንዳስቆጣቸው የዓይን እማኙ ተናግረዋል።
በትላንቱ ሰልፍ ላይ መሳተፋቸውን የሚናገሩት ነዋሪው በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት በሰውም ሆነ በንብረት ላይ ጉዳት አለመድረሱን ይናገራሉ። ነዋሪዎችን አደባባይ ላስወጣቸው የመንገድ እና የሌሎችም የመሰረተ ልማት ችግሮች ከባለስልጣናት በኩል እስካሁን ምንም አይነት መፍትሄ አለመሰጡትንም አስረድተዋል።
የትላንትናው ተቃውሞው ሰላማዊ እንደነበር ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ያረጋገጡት የአምሀራ ሳይንት ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጌ እሸቴ እስካሁንም ድረስ ግን ከተማይቱን ከደሴ ጋር የሚያገናኘውመንገድ አልተከፈተም ብለዋል። ነዋሪዎች ላነሷቸው ጥያቄዎች መፍትሄ ለማበጀት በዛሬው ዕለት ከነዋሪው ጋር ለውይይት መቀመጣቸውን ገልጸዋል።
“አሁን በቀጣይ ሊሆን የሚችለው ከነጋዴው፣ ከአርሶ አደሩም፣ ከመንግስት ሰራተኛም፣ ከአመራርም ጭምር መርጠን የሚመለከታቸው አካላት ጋር ሄደን ምላሽ እናግኝ የሚል ነው” ብለዋል። በከተማይቱ ዘላቂ መፍትሄ እስኪገኝ ድረስ መንገዶቹ ተከፍተው አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ ከነዋሪው ጋር ማምሻውን ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አክለዋል። የተዘጉ መንገዶች ተከፍተው የመኪና እንቅስቃሴ መጀመሩንም የጠቆሙት ኃላፊው ከነገ ጀምሮ የመንግስት መስሪያ ቤቶችም ሆነ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ መደበኛ ስራቸው እንደሚመለሱ ገልጸዋል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአማራ ክልል በአምሀራ ሳይንት ወረዳ በአጅባር ከተማ በተቀሰቀሰ #ተቃውሞ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቋረጣቸውን ነዋሪዎች ገለጹ። ትላንት ለተቃውሞ የወጡ ነዋሪዎች ከተማይቱን ከደሴ ከተማ ጋር የሚያገናኛት መንገድን ዛሬም ዘግተው ውለዋል።
ከደሴ በስተምዕራብ 189 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የአጅባር ከተማ በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ አንድ ነዋሪ ዛሬ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ እንደገለጹት የትላንቱን ተቃውሞ ተከትሎ ከተማይቱ ዛሬ “ጸጥ ረጭ” ብላ ውላለች። “ሱቅም ዝግ ነው። መስሪያ ቤቶች ዝግ ናቸው። የትራንስፖርት እንቅስቃሴ የለም” ሲሉ በከተማይቱ ያለውን ሁኔታ የገለጹት ነዋሪው “መንገዶችም በድንጋይ እና በሌሎች ቁሳቁሶች ተዘግተዋል” ብለዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ስር የምትገኘው የአጅባር ከተማ ሰባት ሺህ ገደማ ነዋሪዎች አሏት። ነዋሪዎቿ “አካባቢያችን ከልማት ወደ ኋላ ቀርቷል፤ የክልል እና የዞን ባለስልጣናት ችግራችንን ሊመለከቱልን አልቻሉም” በሚል ትላንት እስከ እኩለ ቀን ድረስ የዘለቀ የአደባባይ ተቃውሞ አድርገው ነበር። ነዋሪዎቹ ጎማዎችን በማቃጠል መንገዶችን ዘግተዋል። በችግሩ ዙሪያ ለመወያየት ከደቡብ ወሎ ዞን የመጡ ባለስልጣናት ከመንገድ ተመልሰዋል መባሉ ነዋሪዎቹን ይበልጥ እንዳስቆጣቸው የዓይን እማኙ ተናግረዋል።
በትላንቱ ሰልፍ ላይ መሳተፋቸውን የሚናገሩት ነዋሪው በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት በሰውም ሆነ በንብረት ላይ ጉዳት አለመድረሱን ይናገራሉ። ነዋሪዎችን አደባባይ ላስወጣቸው የመንገድ እና የሌሎችም የመሰረተ ልማት ችግሮች ከባለስልጣናት በኩል እስካሁን ምንም አይነት መፍትሄ አለመሰጡትንም አስረድተዋል።
የትላንትናው ተቃውሞው ሰላማዊ እንደነበር ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ያረጋገጡት የአምሀራ ሳይንት ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጌ እሸቴ እስካሁንም ድረስ ግን ከተማይቱን ከደሴ ጋር የሚያገናኘውመንገድ አልተከፈተም ብለዋል። ነዋሪዎች ላነሷቸው ጥያቄዎች መፍትሄ ለማበጀት በዛሬው ዕለት ከነዋሪው ጋር ለውይይት መቀመጣቸውን ገልጸዋል።
“አሁን በቀጣይ ሊሆን የሚችለው ከነጋዴው፣ ከአርሶ አደሩም፣ ከመንግስት ሰራተኛም፣ ከአመራርም ጭምር መርጠን የሚመለከታቸው አካላት ጋር ሄደን ምላሽ እናግኝ የሚል ነው” ብለዋል። በከተማይቱ ዘላቂ መፍትሄ እስኪገኝ ድረስ መንገዶቹ ተከፍተው አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ ከነዋሪው ጋር ማምሻውን ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አክለዋል። የተዘጉ መንገዶች ተከፍተው የመኪና እንቅስቃሴ መጀመሩንም የጠቆሙት ኃላፊው ከነገ ጀምሮ የመንግስት መስሪያ ቤቶችም ሆነ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ መደበኛ ስራቸው እንደሚመለሱ ገልጸዋል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከጥረት ኮርፖሬት የሃብት ምዝበራ ጋር በተያያዘ የአምባሰል ንግድ ስራዎች ስራ አስኪያጅ የነበሩትን አቶ #ምትኩ_በየነን ጨምሮ አምስት ሰዎች ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በህግ ቁጥጥር ስር ዋሉ። የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ከጥረት ኮርፖሬት የሃብት ምዝበራ ጋር በተያያዘ የአምባሰል ንግድ ስራዎች ስራ አስኪያጅ የነበሩትን አቶ ምትኩ በየነን ጨምሮ አምስት ሰዎችን ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በህግ ቁጥጥር ስር አውሏል። ተጠርጣሪዎቹ ነገ በባሕርዳር ከተማና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ🔝ርዕሰ መስተዳድር #ገዱ_አንዳርጋቸው እና ርዕሰ መስተዳድር #ለማ_መገርሳ በኔዘርላንድ በሚገኙ ኩባንያዎች ያደረጉት ጉብኝት።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያና ዩጋንዳ የፖሊስ አመራሮችና አቃቤ ሕጎች የሶስት ቀናት አውደጥናትን ዛሬ #በኤርትራ_አስመራ ተጀምሯል፡፡ አውደጥናቱ የፖሊስ የኮሙኒኬሽን ስርዓትና የሕግ ማዕቀፎች ላይ ትኩረት አድርጎ ውይይት እንደሚያደርግ የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል በቲዊተር ገፃቸው በኩል ገልጸዋል፡፡
Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የነዳጅ ምርቶች ላይ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ተደርጓል‼️
በአለም ላይ ያለውን የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ጭማሪን ግምት ውስጥ በማስገባት እና በህዳር ወር ተደረገው ዋጋ #ማስተካከያ ዝቅተኛ በመሆኑ፥ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ #መጠነኛ_ጭማሪ ማድረጉን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በዚህም መሰረት፡-
•ቤንዚን በሊትር 19 ብር ከ69 ሳንቲም የነበረው 20 ብር ከ19 ሳንቲም
•ነጭ ናፍጣ በሊትር 17 ብር ከ78 ሳንቲም የነበረው 18 ብር ከ03 ሳንቲም
•ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 15 ብር ከ41 ሳንቲም የነበረው 15 ብር ከ66 ሳንቲም
•ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 14 ብር ከ90 ሳንቲም የነበረው 15 ብር ከ15 ሳንቲም
•እንዲሁም የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 20 ብር ከ62 ሳንቲም፣
•ቤኒዚን ኢታኖል ድብልቅ በሊትር 19 ብር ከ89 ሳንቲም እንዲሁም ኬሮሲን በሊትር 18 ብር ከ03 ሳንቲም ሆኗል፡፡
የነዳጅ ችርቻሮ መሸጫ ዋጋው ከነገ ጥር 23 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ማደያዎች ተግባራዊ እንደሚሆንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአለም ላይ ያለውን የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ጭማሪን ግምት ውስጥ በማስገባት እና በህዳር ወር ተደረገው ዋጋ #ማስተካከያ ዝቅተኛ በመሆኑ፥ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ #መጠነኛ_ጭማሪ ማድረጉን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በዚህም መሰረት፡-
•ቤንዚን በሊትር 19 ብር ከ69 ሳንቲም የነበረው 20 ብር ከ19 ሳንቲም
•ነጭ ናፍጣ በሊትር 17 ብር ከ78 ሳንቲም የነበረው 18 ብር ከ03 ሳንቲም
•ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 15 ብር ከ41 ሳንቲም የነበረው 15 ብር ከ66 ሳንቲም
•ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 14 ብር ከ90 ሳንቲም የነበረው 15 ብር ከ15 ሳንቲም
•እንዲሁም የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 20 ብር ከ62 ሳንቲም፣
•ቤኒዚን ኢታኖል ድብልቅ በሊትር 19 ብር ከ89 ሳንቲም እንዲሁም ኬሮሲን በሊትር 18 ብር ከ03 ሳንቲም ሆኗል፡፡
የነዳጅ ችርቻሮ መሸጫ ዋጋው ከነገ ጥር 23 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ማደያዎች ተግባራዊ እንደሚሆንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 22/2011 ዓ.ም.
በሶማሌ ክልል የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ #መሃመድ_ዑመርን ጨምሮ በ47 ግለሰቦች ላይ #ክስ ተመስርቷል።
.
.
ለከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉትን ‹‹ቪ8›› መኪኖች በሌሎች አዳዲስና ወጪ ቆጣቢ ተሽከርካሪዎች የመተካቱ ሂደት በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገልጿል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ ተፈጥሮ በነበረው #አለመረጋጋት እና የተቃውሞ ቀናት ጉዳት ሳይደርስበት በሀሰት ጉዳት የደረሰበት በማስመሰልና ይህንን የሃሰት ፎቶ በማህበራዊ ድረ ገፅ በመልቀቅ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የሞከረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
.
.
በቅርቡ የፀደቀውን የስደተኞች አዋጅ በመቃወም በአዲስ አበባና በጋምቤላ #የተቃውሞ_ሠልፍ ሊደረግ እንደሆነ ተሰምቷል።
.
.
በሶማሌ ክልል ግጭት፣ ግድያና ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ከአራት ወራት በላይ በእስር ላይ የነበረው #ቴዎድሮስ_አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) በ80,000 ብር ዋስ ከእስር እንዲፈታ ፍርድ ቤት ትእዛዝ ሰጥቷል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን "ግዴታዬን እወጣለሁ ፣ መብቴንም እጠይቃለሁ!" በሚል መርህ ቃል የከተማ አቀፍ የታክስ ንቃናቄ መድረክ ተካሂዷል።
.
.
ከኮንሶ ዞን ወደ ሶያማ ቡርጂ ወረዳ ሲጓዝ በነበረ የጭነት መኪና ላይ ባልታወቁ #ታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ በትላንትናው ዕለት የአራት ሰዎች ህይወት አልፏል።
.
.
#በምሥራቅ_ወለጋ_ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች 2ሺህ 380 ዩኒት ደም መለገሳቸውን የነቀምቴ ደም ባንክ አገልግሎት አስታውቋል።
.
.
የመልካም አስተዳደርና የሥራ አጥነት መሠረታዊ ጥያቄዎች በፍጥነት ለመመለስ የሚያግዝ የ60 ቀናት ዕቅድ ተዘጋጅቶ እንቅስቃሴ መጀመሩን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ተናግረዋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ በተፈጠረው ሁከትና ነውጥ #በማራገብ ሂደት #ፖሊስ እና #አድማ_በታኝ አሉበት፤ ይህም በፖሊስ ውስጥ መሠረታዊ ሪፎርም እንደሚያስፈልግ ያመለክታል ተብሏል።
.
.
15ኛው የኢትዮ-ጅቡቲ የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ በዛሬው ዕለት በጂቡቲ ተጀምሯል፡፡
.
.
ትናንት በሶማሌ ክልል መዲና- ጅግጅጋ የሃይማኖት ክብረ በዓልን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።
.
.
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ እና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #በኔዘርላንድ የሚገኙ ኩባንያዎችን ጎብኝተዋል።
.
.
የኢትዮጵያ #ጉብኝታቸዉን አጠናቀዉ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ በዝግጅት ላይ ያሉት የጀርመኑ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር የሚበሩበት አዉሮፕላን የቴክኒክ #እክል ገጥሞት መዘግየቱ ተሰምቷል።
.
.
ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምት በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 11 ሺህ ሊትር ነዳጅ መያዙን የኢሉገላን ወረዳ ፖሊስ አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል በአምሀራ ሳይንት ወረዳ በአጅባር ከተማ በተቀሰቀሰ #ተቃውሞ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቋረጣቸውን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
.
.
ከጥረት ኮርፖሬት የሃብት ምዝበራ ጋር በተያያዘ የአምባሰል ንግድ ስራዎች ስራ አስኪያጅ የነበሩትን አቶ #ምትኩ_በየነን ጨምሮ አምስት ሰዎች ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
.
.
የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያና ዩጋንዳ የፖሊስ አመራሮችና አቃቤ ሕጎች የሶስት ቀናት አውደጥናትን ዛሬ #በኤርትራ_አስመራ ተጀምሯል፡፡
.
.
በአለም ላይ ያለውን የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ጭማሪን ግምት ውስጥ በማስገባት እና በህዳር ወር ተደረገው ዋጋ #ማስተካከያ ዝቅተኛ በመሆኑ፥ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ #መጠነኛ_ጭማሪ ማድረጉን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ምንጭ፦ etv፣ fbc፣ የጀርመን ራድዮ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ ኢዜአ፣ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሶማሌ ክልል የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ #መሃመድ_ዑመርን ጨምሮ በ47 ግለሰቦች ላይ #ክስ ተመስርቷል።
.
.
ለከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉትን ‹‹ቪ8›› መኪኖች በሌሎች አዳዲስና ወጪ ቆጣቢ ተሽከርካሪዎች የመተካቱ ሂደት በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገልጿል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ ተፈጥሮ በነበረው #አለመረጋጋት እና የተቃውሞ ቀናት ጉዳት ሳይደርስበት በሀሰት ጉዳት የደረሰበት በማስመሰልና ይህንን የሃሰት ፎቶ በማህበራዊ ድረ ገፅ በመልቀቅ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የሞከረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
.
.
በቅርቡ የፀደቀውን የስደተኞች አዋጅ በመቃወም በአዲስ አበባና በጋምቤላ #የተቃውሞ_ሠልፍ ሊደረግ እንደሆነ ተሰምቷል።
.
.
በሶማሌ ክልል ግጭት፣ ግድያና ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ከአራት ወራት በላይ በእስር ላይ የነበረው #ቴዎድሮስ_አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) በ80,000 ብር ዋስ ከእስር እንዲፈታ ፍርድ ቤት ትእዛዝ ሰጥቷል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን "ግዴታዬን እወጣለሁ ፣ መብቴንም እጠይቃለሁ!" በሚል መርህ ቃል የከተማ አቀፍ የታክስ ንቃናቄ መድረክ ተካሂዷል።
.
.
ከኮንሶ ዞን ወደ ሶያማ ቡርጂ ወረዳ ሲጓዝ በነበረ የጭነት መኪና ላይ ባልታወቁ #ታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ በትላንትናው ዕለት የአራት ሰዎች ህይወት አልፏል።
.
.
#በምሥራቅ_ወለጋ_ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች 2ሺህ 380 ዩኒት ደም መለገሳቸውን የነቀምቴ ደም ባንክ አገልግሎት አስታውቋል።
.
.
የመልካም አስተዳደርና የሥራ አጥነት መሠረታዊ ጥያቄዎች በፍጥነት ለመመለስ የሚያግዝ የ60 ቀናት ዕቅድ ተዘጋጅቶ እንቅስቃሴ መጀመሩን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ተናግረዋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ በተፈጠረው ሁከትና ነውጥ #በማራገብ ሂደት #ፖሊስ እና #አድማ_በታኝ አሉበት፤ ይህም በፖሊስ ውስጥ መሠረታዊ ሪፎርም እንደሚያስፈልግ ያመለክታል ተብሏል።
.
.
15ኛው የኢትዮ-ጅቡቲ የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ በዛሬው ዕለት በጂቡቲ ተጀምሯል፡፡
.
.
ትናንት በሶማሌ ክልል መዲና- ጅግጅጋ የሃይማኖት ክብረ በዓልን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።
.
.
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ እና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #በኔዘርላንድ የሚገኙ ኩባንያዎችን ጎብኝተዋል።
.
.
የኢትዮጵያ #ጉብኝታቸዉን አጠናቀዉ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ በዝግጅት ላይ ያሉት የጀርመኑ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር የሚበሩበት አዉሮፕላን የቴክኒክ #እክል ገጥሞት መዘግየቱ ተሰምቷል።
.
.
ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምት በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 11 ሺህ ሊትር ነዳጅ መያዙን የኢሉገላን ወረዳ ፖሊስ አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል በአምሀራ ሳይንት ወረዳ በአጅባር ከተማ በተቀሰቀሰ #ተቃውሞ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቋረጣቸውን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
.
.
ከጥረት ኮርፖሬት የሃብት ምዝበራ ጋር በተያያዘ የአምባሰል ንግድ ስራዎች ስራ አስኪያጅ የነበሩትን አቶ #ምትኩ_በየነን ጨምሮ አምስት ሰዎች ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
.
.
የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያና ዩጋንዳ የፖሊስ አመራሮችና አቃቤ ሕጎች የሶስት ቀናት አውደጥናትን ዛሬ #በኤርትራ_አስመራ ተጀምሯል፡፡
.
.
በአለም ላይ ያለውን የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ጭማሪን ግምት ውስጥ በማስገባት እና በህዳር ወር ተደረገው ዋጋ #ማስተካከያ ዝቅተኛ በመሆኑ፥ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ #መጠነኛ_ጭማሪ ማድረጉን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ምንጭ፦ etv፣ fbc፣ የጀርመን ራድዮ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ ኢዜአ፣ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከትራንስፓርት ሚንስቴርና ከሌሎች ሚንስቴር መስሪያ ቤቶች የተወጣጣው የሉኡካን ቡድን የጅቡቲ ወደብን ጎበኘ። በጉብኝቱ ወቅት ስለወደቡ አጠቃላይ እንቅስቃሴ ገለጻ የተደረገ ሲሆን በጂቡቲ ወደብ ላይ የሚያጋጥመውን መጨናነቅ ለመቅረፍ በተለይም የነዳጅ፣ ማዳበሪያና ስንዴን ጨምሮ ሌሎች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች በፍጥነት ማመላለስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መክሯል። የትራንስፖርት ሚንስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የሉኡካን ቡድኑ ወደ ጅቡቲ መምጣት የአገራቱን ግንኙነት ከማጠናከር ባለፈ በቅንጅት ለመስራት የበኩሉን ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia