TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢንጂነር #ታከለ_ኡማ⬆️ዛሬ ማለዳ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ዛሬ ማምሻውን የሚደረገውን የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታ ምክንያት በማድረግ የቡና፣ የባህርዳር ከነማ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብን ጨምሮ ከሌሎች ክለቦች ደጋፊ ማህበር ተወካዪች ጋር የሻይ ቡና ቆይታ አድርገዋል። አሳሳቢ እየሆነ ስለመጣው ስፓርታዊ #ጨዋነት ዙሪያም ምክክር አድርገዋል። እግር ኳሱ መዝናኛ መሆኑ መረሳት እንደሌለበትና ከ90 ደቂቃ የመዝናኛ ልዩነት ባለፈ ከምንም አይነት የብሄርና የፖለቲካ ፅንፍ ጋር ሊገናኝ እንደማይገባ እንዲሁም ከተማ አስተዳደሩ እግርኳሱና አጠቃላይ የስፖርቱ ዘርፍ እንዲያድግ ማድረግ ስላለበት እገዛ ተወያይተዋል።

ምንጭ፦ Mayor Office of Addis Ababa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️ጠበቃ #ሄኖክ_አክሊሉ እና አቶ #ሚካኤል_መላእክ ከእስር መፈታታቸውን አቶ በላይ ማናዬ ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ⬆️ለከፍተኛ የመንግስት አመራሮች እየተሰጠ የሚገኘው የ2 ቀን ስልጠና እንደቀጠለ ይገኛል።

ፎቶ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የባለስልጣናት ሀብት⬇️

የፌደራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በመጀመሪያ ዙር የ450 የመንግሥት ባለስልጣናትና ሠራተኞችን ሃብት ለህዝብ -ክፍት ለማድረግ የሶፍትዌር #ሙከራ ላይ መሆኑን አሳውቋል።

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር አቶ አየልኝ ሙሉዓለም እስካሁን የ150 ሺህ ባለስልጣናት እና የመንግስት ሠራተኞች ሃብት በመመዝገብ ለህዝብ ክፍት የማድረጊያ ሶፍትዌር ከህንድ ኩባንያ ጋር በመተባበር ወደ ትግበራ መግባቱን ገልጸዋል።

የሶፍትዌር ትግበራው ለሙስና የመጋለጥ እድላቸው ከፍተኛ የሆኑ ተቋማት ሃላፊዎችንና ሠራተኞችን ሀብት ይፋ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል።

እስካሁን የ80 ግለሰቦች የሀብት መረጃ ወደ ሶፍትዌሩ መመዝገባቸውን የገለጹት ኮሚሽነሩ የማሻሻያ ስራዎች ከተጠናቀቁ በኋላ ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን ተናግረዋል።

ሙከራው ሲጠናቀቅ ማንኛውም ግለሰብ የሚፈልገውን የሀብት ምዝገባ መረጃ በስነምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ቢሮዎች በአካል ቀርቦ መመልከት እንደሚችልም ነው የጠቀሱት።

የሀብት ምዝገባ መረጃው ለህዝብ ክፍት የሚሆንበት ጊዜ ባይጠቀስም በቅርቡ እንደሚጀመር ግን ኮሚሽነር አቶ #አየልኝ ጠቁመዋል።

የሀብት ምዝገባ መረጃዎች እስከዛሬ ለህዝብ ክፍት ያልተደረገው ከስራው ውስብስብነትና በሶፍትዌሩ አለመጠናቀቅ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ኮሚሽኑ ላለፉት ዓመታት በሰው ሃይል እጥረት፣ በስራው ውስብስብነትና አቅም ማነስ ምክንያት የሀብት ማጣራት ስራ እንዳልሰራም ነው ኮሚሽነሩ ያነሱት።

አቶ አየልኝ በዘንድሮው በጀት ዓመት የ80 ግለሰቦች ሀብት እየተጣራ እንደሚገኝ ገልጸው ከዚህም ውስጥ የ23ቱ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport ኢትዮጵያ ቡና የ2011 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል።

ኢትዮጵያ ቡና 4-1 ባህር ዳር ከተማ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኒይዎርክ⬇️

የአሜሪካዋ ኒይዎርክ ከተማ በ25 ዓመት ጊዜ ውስጥ ለመጀመሪያ ግዜ ለአንድ ሳምንት #በተኩስ ሰው #ሳይሞት ማሳለፏ ተገለጸ፡፡

ባለፈው ሳምንት አንድም የተኩስ ሪፖርት ለከተማው ፖሊስ አለመድረሱንና ይህም በሃያ አምስት ዓመት ግዜ ውስጥ ሆኖ እንደማያውቅ የተናገረው የከተማው ፖሊስ ነው፡፡

የኒዎርክ ከተማ ከንቲባ ቢል ዲ ብላሶ በከተማው ምንም አይነት ተኩስ አለመሰማቱና በተኩስ ሰው አለመሞቱ በጣም የሚገርምና አስደናቂ ሲሉ ገልጸውታል፡፡

ስምንት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ሰዎች የሚኖሩባት ከተማ ኒይዎርክ ላይ አንድም የጥይት ተኩስ አለመሰማቱ የከተማው ፖሊስ የስራ ውጤት በመሆኑ ትልቅ ምስጋና ይገበዋል ብለዋል፡፡

የኒዩርክ የንዩፒዲ ፖሊስ የወንጀል መከላከል ዋና ሃላፊ ሎሊፕሎክ እንደተናገሩት በከተማው በጥይት የሚደርስ ግድያ በየግዜው እየቀነሰ የመጣ ሲሆን በመሰከረም ወር ደግሞ በታሪክ ዝቅተኛው ግድያ የተፈጸመበት እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል፡፡

በከተማው ለተገኘው ከፍተኛ ውጤት የማህበረሰብ አቀፍ ፖለስ አገልግሎት ላይ ትኩረት ተደርጎ መሰራቱ መሆኑን የፖሊስ ሃላፊው ተናግረዋል፡፡

ምንጭ ፡-ሲኤንኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሂዩማን ራይትስ ዎች⬇️

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ሂዩማን ራይትስ ዎች ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የአፈና ስልቶችን #እንዲያስቆሙ ጠየቀ። በኢትዮጵያ በቅርቡ የተካሄዱት የጅምላ እስሮች እና "አመለካከትን የመቀየር ስልጠናዎች" ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጀመሯቸውን ፖለቲካዊ #ማሻሻያዎች አደጋ ላይ የሚጥሉ ናቸው ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሃድሶ ስልጠና የሚሰጥባቸውን ካምፖች #እንዲዘጉ እና የዘፈቀደ እስርንም በማስቆም ቁርጠኝነታቸውን እንዲያሳዩም አሳስቧል።

ምንጭ፦ DW የአማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በኤርትራ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር #ሬድዋን_ሁሴን የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳልህ አቅርበዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አትሌት #ፈይሳ_ሌሊሳ ነገ ጥዋት 2:00 ወደ እናት ሀገሩ ይገባል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አቶ #ጌታቸው_ኣሰፋ የትግራይ ክልል ር/መስተዳደር የጸጥታ እና የደህንነት #አማካሪ ሆነው ተሹመዋል።

ምንጭ፦ Getu Temesegen
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አትሌት #ፈይሳ_ሌሊሳ ከ30 ደቂቃ በኋላ ኢትዮጵያ- አዲስ አበባ ይገባል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia