TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች ! " - ሰልፈኞች
በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የፍርድ ቤት እና የትምህርት ቢሮ ወሳኔና ትእዛዝ እንዲተገበር የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በመቐለ ተካሂደዋል።
ሰልፉ የተዘጋጀው በትግራይ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት አማካኝነት ነው።
ምክር ቤቱ ዛሬ " ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ተገኝተው ነበር።
ሰልፈኞቹ ፦
- ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ይመለሱ !
- ህገ-መንግስት ይከበር !
- ፍትህ ለእህቶቻችን ነፃነት ለሁሉ !
- ሂጃብ መልበስ ሃይማኖታዊ መብትና ግዴታ ነው !
- ሂጃቤ መልኬ ነው !
- የፍርድ ቤት ትእዛዝ ይከበር !
- ሰላም እና ፍትህ ለትግራይ !
- መብታችን ይጠበቅልን !
- ከተበዳዮች ጎን እንቁም !
- ፍትህን እንጠይቃለን !
- ከሂጃባችን ጋር ታግለናል፤ ሂጃባችን ለብሰን እንማራለን !
- ሂጃባችን ምርጫችን እና መብታችን ነው !
... የሚሉና እና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
በመቐለ ሮማናት አደባባይ ለተሰባሰቡት ሰልፈኞች መልእክት ያስተላለፉት የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዜዳንት ሸኽ አደም ዓብደልቃድር ፥ " ትግራይ የሃይማኖቶች የመቻቻል የነፃነት ተምሳሌት ነች፤ ይሁን እንጂ ይህንኑ ስልጡንነት ወደ ኋላ በሚመልስ መልኩ ልጆቻችን ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ ከዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና እንዲቀሩ ተደርገዋል " ብለዋል።
ችግሩ ሳይባባስ እንዲፈታ ለሁለት ወራት በላይ የተለያየ ጥረቱ መደረጉ ያወሱት ፕሬዜዳንቱ " ትምህርት ቤቶቹ የክልሉ እና የአገሪቱን ህግ በማክበር የሂጃብ ክልከላውን በአጭር ጊዜ ማንሳት አለባቸው ፤ ጥያቄያችን በአጭር ጊዜ ካልተመለሰ ግን ጥያቄያችን እስከ መጨረሻው ድረስ በሰላማዊ መንገድ እንቀጥላለን " ሲሉ ተናግረዋል።
" የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲሁም ክርስትያን ወንድሞቻችን ችግሩ ክጅምሩ እንዲፈታ ብዙ ጥረት አድርጋችሃል " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ችግሩ በዘላቂነት እስኪፈታ ድረስም የጀመራችሁት ትግል ተጠናክሮ ይቀጥል " በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።
ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች በመዘዋወር የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ሁሉም የሚመለከታቸው መንግስታዊ አካላት ጉዳዩ ወደ ሃይማኖታዊ ግጭት እንዳያመራ የሚያስገነዝብ ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ከትምህርት ገበታቸው የተስተጓጎሉ ሴት ተማሪዎች መካካሻ ትምህርት እንዲያገኙ ያለሙ የሚያወሱ 12 ጥሪዎች እና ልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ መልእክቶች ለክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር በማቅረብ እና በማስተላለፍ ከረፋዱ 4:30 ሰልፉ ተጠናቋል።
ሰላማዊ ሰልፉ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ የከተማዋ የፀጥታ ሃይሎች የተቀናጀ ጥበቃ ያደረጉ ሲሆን በሰላም ተጀምሮ በሰላም መጠናቀቁ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
በሌላ በኩል ፥ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ ክልከላ አድርገዋል የተባሉት በአክሱም ከተማ የሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የጋራ የፅሁፍ ምላሽ ሰጥተዋል።
ት/ቤቶቹ ምን አሉ ?
" 1. የሴት ሙስሊም ተማሪዎች የሂጃብ አጠቃቀም አስመልክቶ በትግራይ ያለው ህግ እና አተገባበሩ ምን ይመስላል ?
ትምህር ቤቶቻችን የትግራይ ትምህርት ቢሮ በ1995 ዓ.ም ያወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ነው እየተጠቀሙ ያሉት ። አዲስ ፖሊሲ ወይም መመሪያ እና ደንብ በትምህርት ሚንስቴር ከወጣ ደግሞ ከትምህርት ቢሮ ጋር ተነጋግሮ ይህንን መመሪያ እና ደንብ ተጠቀሙ ብሎ ይልክልናል ። እኛም ተግባራዊ እናደርጋለን። ይህን ባለልሆነበት ' እህያውን ፈርቶ ዳውላውን ' የሆነ ጥያቄ እና ጫና ግን ግራ የሚያጋባ ነው።
በ1995 ዓ.ም የወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ደግሞ ተማሪዎች መምህራን ወላጆች ተወያይተው ያፀዱቁት ላለፉት 22 ዓመታት እየተጠቀሙት ያለ መመሪያ ደንብ ነው።
በ1995 ዓ.ም የወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ደንብ ደግሞ እንዲታይ በያዝነው ዓመት መጀመሪያ ከወላጅ ተማሪዎች ጥያቄ ተነስቶ ነበር ። የተነሳው ጥያቄ መሰረት በማድረግ በመመሪያ እና ደንቡ ውይይት ተካሂዶ ታህሳስ 6/2017 ዓ.ም በአንድ ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ፀድቀዋል።
በውይይት እና ድምፅ አሰጣጡ የሙስሊም እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ተሳትፈውበት በሙሉ መግባባት መተማመን የተደረሰበት ነው። ታድያ ከአሁን በፊት ታይቶ የማይታወቅ የሂጃብ ክልከላ ጥያቄ ከየት ? እንዴት መጣ ? ትምህርት ቤቶታቻችን ግራ ገብቶዋቸዋል።
2. የትምህርት ቤት ዩኒፎርም አለባበስ ደንብ እና ስነ-ሰርዓት ምን ይመስላል ?
በ1995 ዓ.ም በፀደቀው የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መምሪያ እና ደንብ መሰረት ትምህርት ቤቶቻችን የሚከተለውን የአለባበስ ስርዓት እንዲተገብሩ ያስገድዳል።
የቤተክርስትያን ካህናት እና ዲያቆናት ተማሪዎች ሻሽ መጠምጠምያ ፣ ነጠላ ማድረግ አይፈቀድም። ወንድ ተማሪዎች ባንከር ፣ ፍሪዝ የፀጉር አቆራረጥ አይፈቀድም።
ሴት ተማሪዎችም ነጠላ ፣ መሃረብ ፣ ሻሽ መጠምጠምያ ፣ ጥቁር የሃዘን ሻርፕ ፣ ሂል ጫማ ፣ ሱሪ ፣ የማንኛውም ሃይማኖት አለባበስ የሚያንፀባርቅ ልብስ እንዲለብሱ አይፈቀድም። ይህ የሆነበት ደግሞ በመካከላቸው የሃብት የሃይማኖት ልዩነት ፈጥሮ የመማር የማስተማር ሂደቱ እንዳይታወክ ለማድረግ ያለመ ነው።
ይህ ህግ ደግሞ ክርስትያን ፣ ሙስሊም መምህር የተማሪ ወላጅ ተወያይተው ያፀደቁት እና የሚተዳሩበት ነው። አሁን ታድያ ምን አዲስ ነገር ተፈጥሮ ነው በትምህርት ቤቶቻችን ላይ የሚዘመተው ?
3. ስለ ዘንድሮ 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች መሬት ላይ ያለው መረጃ ምንድነው ?
በአክሱም አራት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሉ። በአራቱ ትምህርት ቤቶች ዘንድሮ ለ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የሚቀርቡት ተማሪዎች 1044 ናቸው።
ከነዚህ 1044 ተማሪዎች 17 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ናቸው። ከነዚህ 17 ሴት ተማሪዎች ለ22 ዓመታት በቆየው የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መመሪያ እና ደንብ በመቀበል 7 ሴት ተማሪዎች ፈተናው ለመውሰድ ፎርም ሞልተዋል።
10 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ደግሞ ከአክሱም ከተማ እስከ ሳውዲ ዓረብያ በተዘረጋ የውጭ ተፅእኖ ፈተና ለመውሰድ የሚያስችላቸው ፎርም አልሞሉም። ሃቁ ይህ ሆኖ እያለ ' 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲስተጓጎሉ ተደረገ ' እየተባለ ነው የሚወራው። 142 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቻችን የሌሉ የፈጠራ ድርሰቶች ናቸው።
የተቀሩት 10 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ቢሆኑ ፎርም መልተው ለመፈተን ፍላጎት አላቸው ፤ ከትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፣ ከመቐለ ፣ ከአዲስ አበባ እስከ ሳውዲ ዓረብያ በየቀኑ እየተደወለ ማስፈራርያ ይደርሳቸዋል። ይህ አካሄድ ደግሞ የቆየውን አብሮነት እና መቻቻል የሚጎዳ ለህዝብ እና አገር የማይጠቅም መወገዝ ያለበት ተግባር ነው። "
... ሲሉ ትምህርት ቤቶቹ በጥምር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በላኩት የፅሁፍ ምላሽ ገልጸዋል።
#UPDATE ትምህርት ቤቶቹ ዘግይተው በላኩት መልዕክት ደግሞ " ሁሉም ተፈታኞች ፎርም ሞልተዋል ለፈተናም ብቁ ናቸው " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaMekelle
#ቲክቫህኢትዮጵያመቐለ
@tikvahethiopia
በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የፍርድ ቤት እና የትምህርት ቢሮ ወሳኔና ትእዛዝ እንዲተገበር የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በመቐለ ተካሂደዋል።
ሰልፉ የተዘጋጀው በትግራይ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት አማካኝነት ነው።
ምክር ቤቱ ዛሬ " ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ተገኝተው ነበር።
ሰልፈኞቹ ፦
- ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ይመለሱ !
- ህገ-መንግስት ይከበር !
- ፍትህ ለእህቶቻችን ነፃነት ለሁሉ !
- ሂጃብ መልበስ ሃይማኖታዊ መብትና ግዴታ ነው !
- ሂጃቤ መልኬ ነው !
- የፍርድ ቤት ትእዛዝ ይከበር !
- ሰላም እና ፍትህ ለትግራይ !
- መብታችን ይጠበቅልን !
- ከተበዳዮች ጎን እንቁም !
- ፍትህን እንጠይቃለን !
- ከሂጃባችን ጋር ታግለናል፤ ሂጃባችን ለብሰን እንማራለን !
- ሂጃባችን ምርጫችን እና መብታችን ነው !
... የሚሉና እና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
በመቐለ ሮማናት አደባባይ ለተሰባሰቡት ሰልፈኞች መልእክት ያስተላለፉት የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዜዳንት ሸኽ አደም ዓብደልቃድር ፥ " ትግራይ የሃይማኖቶች የመቻቻል የነፃነት ተምሳሌት ነች፤ ይሁን እንጂ ይህንኑ ስልጡንነት ወደ ኋላ በሚመልስ መልኩ ልጆቻችን ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ ከዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና እንዲቀሩ ተደርገዋል " ብለዋል።
ችግሩ ሳይባባስ እንዲፈታ ለሁለት ወራት በላይ የተለያየ ጥረቱ መደረጉ ያወሱት ፕሬዜዳንቱ " ትምህርት ቤቶቹ የክልሉ እና የአገሪቱን ህግ በማክበር የሂጃብ ክልከላውን በአጭር ጊዜ ማንሳት አለባቸው ፤ ጥያቄያችን በአጭር ጊዜ ካልተመለሰ ግን ጥያቄያችን እስከ መጨረሻው ድረስ በሰላማዊ መንገድ እንቀጥላለን " ሲሉ ተናግረዋል።
" የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲሁም ክርስትያን ወንድሞቻችን ችግሩ ክጅምሩ እንዲፈታ ብዙ ጥረት አድርጋችሃል " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ችግሩ በዘላቂነት እስኪፈታ ድረስም የጀመራችሁት ትግል ተጠናክሮ ይቀጥል " በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።
ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች በመዘዋወር የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ሁሉም የሚመለከታቸው መንግስታዊ አካላት ጉዳዩ ወደ ሃይማኖታዊ ግጭት እንዳያመራ የሚያስገነዝብ ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ከትምህርት ገበታቸው የተስተጓጎሉ ሴት ተማሪዎች መካካሻ ትምህርት እንዲያገኙ ያለሙ የሚያወሱ 12 ጥሪዎች እና ልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ መልእክቶች ለክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር በማቅረብ እና በማስተላለፍ ከረፋዱ 4:30 ሰልፉ ተጠናቋል።
ሰላማዊ ሰልፉ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ የከተማዋ የፀጥታ ሃይሎች የተቀናጀ ጥበቃ ያደረጉ ሲሆን በሰላም ተጀምሮ በሰላም መጠናቀቁ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
በሌላ በኩል ፥ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ ክልከላ አድርገዋል የተባሉት በአክሱም ከተማ የሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የጋራ የፅሁፍ ምላሽ ሰጥተዋል።
ት/ቤቶቹ ምን አሉ ?
" 1. የሴት ሙስሊም ተማሪዎች የሂጃብ አጠቃቀም አስመልክቶ በትግራይ ያለው ህግ እና አተገባበሩ ምን ይመስላል ?
ትምህር ቤቶቻችን የትግራይ ትምህርት ቢሮ በ1995 ዓ.ም ያወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ነው እየተጠቀሙ ያሉት ። አዲስ ፖሊሲ ወይም መመሪያ እና ደንብ በትምህርት ሚንስቴር ከወጣ ደግሞ ከትምህርት ቢሮ ጋር ተነጋግሮ ይህንን መመሪያ እና ደንብ ተጠቀሙ ብሎ ይልክልናል ። እኛም ተግባራዊ እናደርጋለን። ይህን ባለልሆነበት ' እህያውን ፈርቶ ዳውላውን ' የሆነ ጥያቄ እና ጫና ግን ግራ የሚያጋባ ነው።
በ1995 ዓ.ም የወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ደግሞ ተማሪዎች መምህራን ወላጆች ተወያይተው ያፀዱቁት ላለፉት 22 ዓመታት እየተጠቀሙት ያለ መመሪያ ደንብ ነው።
በ1995 ዓ.ም የወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ደንብ ደግሞ እንዲታይ በያዝነው ዓመት መጀመሪያ ከወላጅ ተማሪዎች ጥያቄ ተነስቶ ነበር ። የተነሳው ጥያቄ መሰረት በማድረግ በመመሪያ እና ደንቡ ውይይት ተካሂዶ ታህሳስ 6/2017 ዓ.ም በአንድ ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ፀድቀዋል።
በውይይት እና ድምፅ አሰጣጡ የሙስሊም እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ተሳትፈውበት በሙሉ መግባባት መተማመን የተደረሰበት ነው። ታድያ ከአሁን በፊት ታይቶ የማይታወቅ የሂጃብ ክልከላ ጥያቄ ከየት ? እንዴት መጣ ? ትምህርት ቤቶታቻችን ግራ ገብቶዋቸዋል።
2. የትምህርት ቤት ዩኒፎርም አለባበስ ደንብ እና ስነ-ሰርዓት ምን ይመስላል ?
በ1995 ዓ.ም በፀደቀው የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መምሪያ እና ደንብ መሰረት ትምህርት ቤቶቻችን የሚከተለውን የአለባበስ ስርዓት እንዲተገብሩ ያስገድዳል።
የቤተክርስትያን ካህናት እና ዲያቆናት ተማሪዎች ሻሽ መጠምጠምያ ፣ ነጠላ ማድረግ አይፈቀድም። ወንድ ተማሪዎች ባንከር ፣ ፍሪዝ የፀጉር አቆራረጥ አይፈቀድም።
ሴት ተማሪዎችም ነጠላ ፣ መሃረብ ፣ ሻሽ መጠምጠምያ ፣ ጥቁር የሃዘን ሻርፕ ፣ ሂል ጫማ ፣ ሱሪ ፣ የማንኛውም ሃይማኖት አለባበስ የሚያንፀባርቅ ልብስ እንዲለብሱ አይፈቀድም። ይህ የሆነበት ደግሞ በመካከላቸው የሃብት የሃይማኖት ልዩነት ፈጥሮ የመማር የማስተማር ሂደቱ እንዳይታወክ ለማድረግ ያለመ ነው።
ይህ ህግ ደግሞ ክርስትያን ፣ ሙስሊም መምህር የተማሪ ወላጅ ተወያይተው ያፀደቁት እና የሚተዳሩበት ነው። አሁን ታድያ ምን አዲስ ነገር ተፈጥሮ ነው በትምህርት ቤቶቻችን ላይ የሚዘመተው ?
3. ስለ ዘንድሮ 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች መሬት ላይ ያለው መረጃ ምንድነው ?
በአክሱም አራት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሉ። በአራቱ ትምህርት ቤቶች ዘንድሮ ለ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የሚቀርቡት ተማሪዎች 1044 ናቸው።
ከነዚህ 1044 ተማሪዎች 17 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ናቸው። ከነዚህ 17 ሴት ተማሪዎች ለ22 ዓመታት በቆየው የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መመሪያ እና ደንብ በመቀበል 7 ሴት ተማሪዎች ፈተናው ለመውሰድ ፎርም ሞልተዋል።
10 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ደግሞ ከአክሱም ከተማ እስከ ሳውዲ ዓረብያ በተዘረጋ የውጭ ተፅእኖ ፈተና ለመውሰድ የሚያስችላቸው ፎርም አልሞሉም። ሃቁ ይህ ሆኖ እያለ ' 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲስተጓጎሉ ተደረገ ' እየተባለ ነው የሚወራው። 142 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቻችን የሌሉ የፈጠራ ድርሰቶች ናቸው።
የተቀሩት 10 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ቢሆኑ ፎርም መልተው ለመፈተን ፍላጎት አላቸው ፤ ከትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፣ ከመቐለ ፣ ከአዲስ አበባ እስከ ሳውዲ ዓረብያ በየቀኑ እየተደወለ ማስፈራርያ ይደርሳቸዋል። ይህ አካሄድ ደግሞ የቆየውን አብሮነት እና መቻቻል የሚጎዳ ለህዝብ እና አገር የማይጠቅም መወገዝ ያለበት ተግባር ነው። "
... ሲሉ ትምህርት ቤቶቹ በጥምር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በላኩት የፅሁፍ ምላሽ ገልጸዋል።
#UPDATE ትምህርት ቤቶቹ ዘግይተው በላኩት መልዕክት ደግሞ " ሁሉም ተፈታኞች ፎርም ሞልተዋል ለፈተናም ብቁ ናቸው " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaMekelle
#ቲክቫህኢትዮጵያመቐለ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የትግራይን ህዝብ አንድነት በሚያጠናክር መልኩ እንዲፈታ ይደረጋል" - አቶ ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ዛሬ " ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን ሰላማዊ ሰልፍ አዘጋጆች መልእክት በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለዋል።
ሰልፉን የጠራው የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ያዘጋጀው መልእክት የተቀበሉት ፕሬዜዳንቱ አቶ ጌታቸው ፥" ከጦርነት ወጥተን በተነፃፃሪ ሰላም በምንገኝበት ጊዜ ሴት ሙስሊም እህቶቻችን በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ሲከለከሉ ማየት በጣም የሚያሳዝን ነው " ብለዋል።
" ችግሩ ገና ከጅምሩ ከትምህርት ቤቶቹ አመራሮች ፣ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ በመነጋገር ለመፍታት ጥረት ሲደረግ ቆይተዋል። እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ ያልነበረት ጉዳይ ነው። አሁንም የትግራይ ህዝብ አንድነት በሚያጠናክር መልኩ እንዲፈታ ይደረጋል " ብለዋል።
" ጉዳዩ ቶሎ መታረም እንዳለበት የሚያግባባን ቢሆንም ፤ ከስሜት በፀዳ አስተዋይነትና ዘላቂነት ባለው መንገድ መሆን እንደሚገባ ሁላችንም መገንዘብ ያስፈልጋል " በማለት አክለዋል።
ችግሩ በፍጥነት እንዲፈታ አስተዳደራቸው ዝግጁ እንደሆነና እንደሚሳራም አመልክተዋል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የተነሳ ጥያቄ አጀንዳ መሆን አልነበረበትም ብሎ እንደሚያምን የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ፤ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተባባሪዎቹ እና ተሳታፊዎቹ ላሳዩት ጭዋ የሆነ ባህሪ ምስጋና አቅርበዋል።
ሰላማዊ ሰልፉ ፍፁም ሰላም በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ሰልፉን በቦታው ሆኖ ሲከታተል የነበረው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
@tikvahethiopia
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ዛሬ " ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን ሰላማዊ ሰልፍ አዘጋጆች መልእክት በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለዋል።
ሰልፉን የጠራው የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ያዘጋጀው መልእክት የተቀበሉት ፕሬዜዳንቱ አቶ ጌታቸው ፥" ከጦርነት ወጥተን በተነፃፃሪ ሰላም በምንገኝበት ጊዜ ሴት ሙስሊም እህቶቻችን በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ሲከለከሉ ማየት በጣም የሚያሳዝን ነው " ብለዋል።
" ችግሩ ገና ከጅምሩ ከትምህርት ቤቶቹ አመራሮች ፣ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ በመነጋገር ለመፍታት ጥረት ሲደረግ ቆይተዋል። እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ ያልነበረት ጉዳይ ነው። አሁንም የትግራይ ህዝብ አንድነት በሚያጠናክር መልኩ እንዲፈታ ይደረጋል " ብለዋል።
" ጉዳዩ ቶሎ መታረም እንዳለበት የሚያግባባን ቢሆንም ፤ ከስሜት በፀዳ አስተዋይነትና ዘላቂነት ባለው መንገድ መሆን እንደሚገባ ሁላችንም መገንዘብ ያስፈልጋል " በማለት አክለዋል።
ችግሩ በፍጥነት እንዲፈታ አስተዳደራቸው ዝግጁ እንደሆነና እንደሚሳራም አመልክተዋል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የተነሳ ጥያቄ አጀንዳ መሆን አልነበረበትም ብሎ እንደሚያምን የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ፤ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተባባሪዎቹ እና ተሳታፊዎቹ ላሳዩት ጭዋ የሆነ ባህሪ ምስጋና አቅርበዋል።
ሰላማዊ ሰልፉ ፍፁም ሰላም በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ሰልፉን በቦታው ሆኖ ሲከታተል የነበረው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
@tikvahethiopia
ዛሬ ጠዋት 1 ሠዓት ከ30 ላይ ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሃን ሲጓዝ የነበረ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ' ጠባሴ ' አካባቢ ሲደርስ መንገድ ስቶ በመውጣቱ የሦስት እግረኞችን ሕይዎት ቀጠፈ፡፡
ከሟቾቹ አንዷ ልጆቿን ወደ ትምህርት ቤት ስትሸኝ የነበረች እናት ናት።
ከሟቾች በተጨማሪም በአደጋው የ1 ዓመት ከ7 ወር ሕጻንን ጨምሮ በ9 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል።
የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር እንደሆነ ጠቁሟል። አደጋውን ያደረሰው አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ ነው ተብሏል።
መረጃው የኤፍኤምሲ ነው።
@tikvahethiopia
ከሟቾቹ አንዷ ልጆቿን ወደ ትምህርት ቤት ስትሸኝ የነበረች እናት ናት።
ከሟቾች በተጨማሪም በአደጋው የ1 ዓመት ከ7 ወር ሕጻንን ጨምሮ በ9 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል።
የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር እንደሆነ ጠቁሟል። አደጋውን ያደረሰው አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ ነው ተብሏል።
መረጃው የኤፍኤምሲ ነው።
@tikvahethiopia
" በቁጥጥር ስር አውለናቸዋል " - የአምቦ ከተማ አስተዳደር
የአምቦ ከተማ አስተዳደር ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር በአንቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪ የነበሩና የሃይማኖት ስም በማጥፋት ወንጀል የተጠረጠሩ 3 ተማሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል።
ተማሪዎቹ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበረው የጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በታቦት እና በሃይማኖቱ ላይ ሲሳለቁ የሚያሳይ ቪዲዮ #ቲክቶክ በተባለው የማህበራዊ ሚዲያ ከለቀቁ በኋላ እጅግ በርካታ ሰዎች ጋር ደርሶ ቁጣን ፈጥሯል።
የአምቦ ከተማ አስተዳደር በድርጊቱ የተሳተፉ እና በማህበራዊ ገጾች ላይ የለጠፉ 3 ተማሪዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ (እንደታሰሩ) ገልጾ የአምቦ ዩኒቨርሲቲም የዲሲፕሊን ቅጣት ለማስተላለፍ አቅጣጫ ማስቀመጡን አስተውቋል።
Via @tikvahethmagazine
የአምቦ ከተማ አስተዳደር ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር በአንቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪ የነበሩና የሃይማኖት ስም በማጥፋት ወንጀል የተጠረጠሩ 3 ተማሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል።
ተማሪዎቹ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበረው የጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በታቦት እና በሃይማኖቱ ላይ ሲሳለቁ የሚያሳይ ቪዲዮ #ቲክቶክ በተባለው የማህበራዊ ሚዲያ ከለቀቁ በኋላ እጅግ በርካታ ሰዎች ጋር ደርሶ ቁጣን ፈጥሯል።
የአምቦ ከተማ አስተዳደር በድርጊቱ የተሳተፉ እና በማህበራዊ ገጾች ላይ የለጠፉ 3 ተማሪዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ (እንደታሰሩ) ገልጾ የአምቦ ዩኒቨርሲቲም የዲሲፕሊን ቅጣት ለማስተላለፍ አቅጣጫ ማስቀመጡን አስተውቋል።
Via @tikvahethmagazine
💥 የኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ECX) ክፍያዎን በቀላሉ በቴሌብር ይፈጽሙ!!
ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ECX) ጋር በተያያዘ የሥልጠና፣ የአባልነት፣ እንዲሁም የቡና፣ ጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች ምዘና ክፍያን ጨምሮ ሌሎች ክፍያዎችን በፈጣኑ ቴሌብር መክፈል ተችሏል፡፡
💡 ከ ECX ሲስተም በሚያገኙት ልዩ የክፍያ ማጣቀሻ ቁጥር በቀላሉ በቴሌብር መክፈል ይችላሉ!
👉 ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ወይም *127# ይጠቀሙ!
ቴሌብር ሱፐርአፕ ➡️ ክፍያ ➡️ ግብር እና የመንግሥት አገልግሎት ➡️ የመንግሥት አገልግሎት ክፍያዎች ➡️ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ECX) ጋር በተያያዘ የሥልጠና፣ የአባልነት፣ እንዲሁም የቡና፣ ጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች ምዘና ክፍያን ጨምሮ ሌሎች ክፍያዎችን በፈጣኑ ቴሌብር መክፈል ተችሏል፡፡
💡 ከ ECX ሲስተም በሚያገኙት ልዩ የክፍያ ማጣቀሻ ቁጥር በቀላሉ በቴሌብር መክፈል ይችላሉ!
👉 ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ወይም *127# ይጠቀሙ!
ቴሌብር ሱፐርአፕ ➡️ ክፍያ ➡️ ግብር እና የመንግሥት አገልግሎት ➡️ የመንግሥት አገልግሎት ክፍያዎች ➡️ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
#AddisAbaba
" አባታችንን አፋልጉን ! "
አባታችን ገብረማርያም መለሰ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ/ም ከሰዓት በኃላ ከቤት እንደወጡ አልተመለሱም።
እድሜያቸው 85 ዓመት ሲሆን መጥፋታቸውን ለፖሊስ አመልክተናል።
በሰዓቱ ለብሰውት የነበረው ጥቁር ጃኬት ነበር። ከዘራም በእጃቸው ይዘዋል።
መጨረሻ ጊዜ የነበሩበት ቦታ ወሰን 02 አካባቢ ነው።
ቤተሰብ ተጨንቋል አባታችንን አፋልጉን፤ መረጃ ለመስጠት 0911452386 ላይ ደውሉልን። " - ፈላጊ ቤተሰቦቻቸው
@tikvahethiopia
" አባታችንን አፋልጉን ! "
አባታችን ገብረማርያም መለሰ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ/ም ከሰዓት በኃላ ከቤት እንደወጡ አልተመለሱም።
እድሜያቸው 85 ዓመት ሲሆን መጥፋታቸውን ለፖሊስ አመልክተናል።
በሰዓቱ ለብሰውት የነበረው ጥቁር ጃኬት ነበር። ከዘራም በእጃቸው ይዘዋል።
መጨረሻ ጊዜ የነበሩበት ቦታ ወሰን 02 አካባቢ ነው።
ቤተሰብ ተጨንቋል አባታችንን አፋልጉን፤ መረጃ ለመስጠት 0911452386 ላይ ደውሉልን። " - ፈላጊ ቤተሰቦቻቸው
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
" የሀጅ ጉዞ ምዝገባ ጥር 15 ይጀምራል የሀጅ ጉዞ ዋጋ አሁን ባለው 625,000 (ስድስት መቶ ሃያ አምስት ሺ) ብር ነው " - ጠቅላይ ምክር ቤቱ
የ1446ኛው የሀጅ እና ዑምራ ጉዞ ምዝገባ ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ የካቲት 21 ብቻ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል።
ምዝገባው ጥር 15/2017 በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር የምዝገባ ጣቢያዎች ይጀመራል።
የሳውዲ ሀጅ ሚኒስቴር ባስቀመጠው አሰራር መሰረት ያለው የምዝገባ ጊዜ አጭር በመሆኑ ሁጃጆች (ተጓዦች) በወቅቱ ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀርቧል።
የዘንድሮ የሀጅ እና ዑምራ የጉዞ ዋጋ 625 ሺህ ብር መሆኑ ተገልጿል።
ምክር ቤቱ " የጉዞው ዋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የታየው የዶላር ጭማሪና በአየር መንገዶች ላይ ያለው የትኬት ዋጋ መናር ዋጋው ከፍ እንዲል አድርጎታል " ብሏል።
" የሀጅ ዋሃ ከዶላር አንፃር የ4,921 ዶላር ቅናሽ እንዲደረግበት ቢደረግም በብር ግን ጭማሪ አሳይቷል " ሲል ገልጿል።
ጠቅላይ ምክር-ቤቱ የአገልግሎት ዋጋን በመቀነስ በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በማጠፍና በሳውዲ የሚቀርበውን አገልግሎት ተመጣጣኝ እንዲሆን በማድረግ 108 ሺህ ብር ቅናሽ እንዲኖረው ማድረጉን አሳውቋል።
የዶላር ዋጋ ከፍ በማለቱ ግን ብሩ መጨመሩ ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት ለአንድ ሀጅ ዋጋ አጠቃላይ ብር 329,000 እንደነበር ይታወሳል።
@tikvahethiopia
" የሀጅ ጉዞ ምዝገባ ጥር 15 ይጀምራል የሀጅ ጉዞ ዋጋ አሁን ባለው 625,000 (ስድስት መቶ ሃያ አምስት ሺ) ብር ነው " - ጠቅላይ ምክር ቤቱ
የ1446ኛው የሀጅ እና ዑምራ ጉዞ ምዝገባ ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ የካቲት 21 ብቻ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል።
ምዝገባው ጥር 15/2017 በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር የምዝገባ ጣቢያዎች ይጀመራል።
የሳውዲ ሀጅ ሚኒስቴር ባስቀመጠው አሰራር መሰረት ያለው የምዝገባ ጊዜ አጭር በመሆኑ ሁጃጆች (ተጓዦች) በወቅቱ ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀርቧል።
የዘንድሮ የሀጅ እና ዑምራ የጉዞ ዋጋ 625 ሺህ ብር መሆኑ ተገልጿል።
ምክር ቤቱ " የጉዞው ዋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የታየው የዶላር ጭማሪና በአየር መንገዶች ላይ ያለው የትኬት ዋጋ መናር ዋጋው ከፍ እንዲል አድርጎታል " ብሏል።
" የሀጅ ዋሃ ከዶላር አንፃር የ4,921 ዶላር ቅናሽ እንዲደረግበት ቢደረግም በብር ግን ጭማሪ አሳይቷል " ሲል ገልጿል።
ጠቅላይ ምክር-ቤቱ የአገልግሎት ዋጋን በመቀነስ በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በማጠፍና በሳውዲ የሚቀርበውን አገልግሎት ተመጣጣኝ እንዲሆን በማድረግ 108 ሺህ ብር ቅናሽ እንዲኖረው ማድረጉን አሳውቋል።
የዶላር ዋጋ ከፍ በማለቱ ግን ብሩ መጨመሩ ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት ለአንድ ሀጅ ዋጋ አጠቃላይ ብር 329,000 እንደነበር ይታወሳል።
@tikvahethiopia
" ዌብሳይቱ ላይ የሚያሳየን ንግድ ፈቃዱ እንደታደሰ ነው ግን ፕሪንት አያደርግም። ... ክፍያውንም እንደ ከፈልን ያሳያል ግን ክፍያ አልከፍልንም ፤ ይሄ ደግሞ የሲስተም ችግር ነው " - ቅሬታ አቅራቢ
የንግድ ፈቃድ ያለ ቅጣት ማደሻ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ/ም ይጠናቀቃል።
የንግድ ስራ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት ከሃምሌ 1 ቀን 2016 ዓ/ም እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ያለ ቅጣት እንዲካሄድ ፕሮግራም ወጥቶ ሲካሄድ ነበር።
በኃላም ተጨማሪ ቀን ተጨምሮ እስከ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ተራዝሟል።
ይህ የተጨመረው ቀን ማለትም ያለ ቅጣት ማደሻ ሊጠናቀቅ 3 ቀን ብቻ ቀርቶታል።
ተገልጋዮች በኦንላይን ፈቃድ ለማሳደስ በስራ ቀናት እስከ ምሽቱ 2:30 ድረስ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ።
የንግድ ፈቃድ በኦንላይን የሚታደሰው በ www.etrade.gov.et ላይ ሲሆን የአገልግሎት ክፍያ ፈጽመው ምስክር ወረቀት በመጠባበቅ ላይ ያሉ ' የምስክር ወረቀት ያትሙ ' (Print Certificate) የሚለውን ቁልፍ በመጫን የምስክር ወረቀታቸውን ማግኘት ይችላሉ።
ከዚሁ ከንግድ ፈቃድ እድሳት ጋር በተያያዘ ግን አንዳንድ ተገልጋዮች እክል ገጠመን ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት ልከዋል።
ከነዚህ ቅሬታ አቅራቢዎች አንደኛው ፦
" ክሊራንስ በታህሳስ 30 ላይ ነበር የጨረስኩት ፤ ከጨረስኩበት ሰዓት ጀምሮ ንግድ ፈቃዱን ለማደስ ክፍያ በምከፍልበት ሰዓት አንደኛ ክፍያው እንደ ተከፈለ ነው የሚያሳየኝ ፤ ሁለተኛ የመክፈያ ቁጥር ተብሎ የተሰጠኝ ቁጥርን ቴሌብር ላይ ስሞክረ ' ይሄ ክፍያ ተከፍላል ' ነው የሚለው።
በሲስተሙ ምክንያት ምንም ነገር መስራት እና ፈቃዱን ማደስ አልቻልኩም። ዌብሳይቱ ላይ የሚያሳየን ንግድ ፈቃዱን ፕሪንት አያደርግም ግን እንደ ታደሰ ያሳያል። ክፍያውንም እንደ ከፈልን ነው የሚያሳየው። ግን ክፍያ አልከፍልንም ይሄ ደግሞ የሲስተም ችግር ስለሆነ ነገ ከነገ ወዲያ ያስጠይቀናል።
ሲስተም እስከሆነ ድረስ ቅጣቱን እና ወለዱን ይዞ ነው። አሁን ባለው እንኳን ቅጣት 2,500 ነው ከዛ የጊዜ ገደብ ተሰጥቶ ካለፈ ወደ 10 ሺህ ከፍ ይላል።
እኛ ባላጠፋነው ፤ በጊዜው ክሊራንስ ጨርሰን ብንገኝም በሲስተም ምክንያት ማደስ አልቻልንም። ለዚህ መፍትሄ እንፈልጋለን " ብለዋል።
በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኮምዩኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድሙ ፍላቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
" ኦንላይን ባሉበት ማራዘም ይችላሉ የሲስተም ችግርም የለም እስከ አሁን ያላደሱ ነጋዴዎች ቅጣት ውስጥ መግባት ይገባቸው ነበር ነገር ግን እስከ ጥር 15 ያለቅጣት እንዲያራዝሙ ተፈቅዶላቸዋል።
ችግርም ካለ የተጠቃሚዎች የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ነው የሚሆነው አሁንም ሲስተሙ እየሰራ ነው ከሦስት ቀን በኃላ ግን ሊያበቃ ይችላል።
አዋጁ የሚለውን ትተን ለንግዱ ማኅበረሰብ በማሰብ ያለቅጣት ከታህሳስ 30 በኋላ ለ15 ቀን እንዲያድሱ ፈቅደናል ሲስተሙ 24 ሰዓት ይሰራል ኤረር (Error) የሚላቸው የአጠቃቀም ችግር ነው በጣም የለማ ሲስተም ነው ያለን።
ለውጤታማነቱም በዚህ አመት በ6 ወር ውስጥ ሁለት ሚሊየን ሃምሳ ሺህ (2,050,000) ሰዎች ንግድ ፈቃድ የማውጣት እና የማደስ አገልግሎት አግኝተዋል።
የሚቀር ነገር አይጠፋም አልፎ አልፎ የሲስተም መቆራረጥ ሊኖር ይችላል ነገር ግን በአብዛኛው አፈጻጸማችን ውጤታማ ነው።
ይህ ሁሉ ሰው ካሳደሰ የሚቀረው ጥቂት ነው በርካታ ሰው ተገልግሏል በነጋዴዎች ችግር ካልሆነ በቀር ከሃምሌ ጀምሮ ማሳደስ ይችሉ ነበር ለምን እስካሁን አረፈዱ በመጨረሻ ሰዓት እንደዚህ አይነት ቅሬታ ማቅረብ ምክንያታዊ ሊሆን አይችልም " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የንግድ ፈቃድ ያለ ቅጣት ማደሻ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ/ም ይጠናቀቃል።
የንግድ ስራ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት ከሃምሌ 1 ቀን 2016 ዓ/ም እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ያለ ቅጣት እንዲካሄድ ፕሮግራም ወጥቶ ሲካሄድ ነበር።
በኃላም ተጨማሪ ቀን ተጨምሮ እስከ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ተራዝሟል።
ይህ የተጨመረው ቀን ማለትም ያለ ቅጣት ማደሻ ሊጠናቀቅ 3 ቀን ብቻ ቀርቶታል።
ተገልጋዮች በኦንላይን ፈቃድ ለማሳደስ በስራ ቀናት እስከ ምሽቱ 2:30 ድረስ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ።
የንግድ ፈቃድ በኦንላይን የሚታደሰው በ www.etrade.gov.et ላይ ሲሆን የአገልግሎት ክፍያ ፈጽመው ምስክር ወረቀት በመጠባበቅ ላይ ያሉ ' የምስክር ወረቀት ያትሙ ' (Print Certificate) የሚለውን ቁልፍ በመጫን የምስክር ወረቀታቸውን ማግኘት ይችላሉ።
ከዚሁ ከንግድ ፈቃድ እድሳት ጋር በተያያዘ ግን አንዳንድ ተገልጋዮች እክል ገጠመን ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት ልከዋል።
ከነዚህ ቅሬታ አቅራቢዎች አንደኛው ፦
" ክሊራንስ በታህሳስ 30 ላይ ነበር የጨረስኩት ፤ ከጨረስኩበት ሰዓት ጀምሮ ንግድ ፈቃዱን ለማደስ ክፍያ በምከፍልበት ሰዓት አንደኛ ክፍያው እንደ ተከፈለ ነው የሚያሳየኝ ፤ ሁለተኛ የመክፈያ ቁጥር ተብሎ የተሰጠኝ ቁጥርን ቴሌብር ላይ ስሞክረ ' ይሄ ክፍያ ተከፍላል ' ነው የሚለው።
በሲስተሙ ምክንያት ምንም ነገር መስራት እና ፈቃዱን ማደስ አልቻልኩም። ዌብሳይቱ ላይ የሚያሳየን ንግድ ፈቃዱን ፕሪንት አያደርግም ግን እንደ ታደሰ ያሳያል። ክፍያውንም እንደ ከፈልን ነው የሚያሳየው። ግን ክፍያ አልከፍልንም ይሄ ደግሞ የሲስተም ችግር ስለሆነ ነገ ከነገ ወዲያ ያስጠይቀናል።
ሲስተም እስከሆነ ድረስ ቅጣቱን እና ወለዱን ይዞ ነው። አሁን ባለው እንኳን ቅጣት 2,500 ነው ከዛ የጊዜ ገደብ ተሰጥቶ ካለፈ ወደ 10 ሺህ ከፍ ይላል።
እኛ ባላጠፋነው ፤ በጊዜው ክሊራንስ ጨርሰን ብንገኝም በሲስተም ምክንያት ማደስ አልቻልንም። ለዚህ መፍትሄ እንፈልጋለን " ብለዋል።
በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኮምዩኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድሙ ፍላቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
" ኦንላይን ባሉበት ማራዘም ይችላሉ የሲስተም ችግርም የለም እስከ አሁን ያላደሱ ነጋዴዎች ቅጣት ውስጥ መግባት ይገባቸው ነበር ነገር ግን እስከ ጥር 15 ያለቅጣት እንዲያራዝሙ ተፈቅዶላቸዋል።
ችግርም ካለ የተጠቃሚዎች የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ነው የሚሆነው አሁንም ሲስተሙ እየሰራ ነው ከሦስት ቀን በኃላ ግን ሊያበቃ ይችላል።
አዋጁ የሚለውን ትተን ለንግዱ ማኅበረሰብ በማሰብ ያለቅጣት ከታህሳስ 30 በኋላ ለ15 ቀን እንዲያድሱ ፈቅደናል ሲስተሙ 24 ሰዓት ይሰራል ኤረር (Error) የሚላቸው የአጠቃቀም ችግር ነው በጣም የለማ ሲስተም ነው ያለን።
ለውጤታማነቱም በዚህ አመት በ6 ወር ውስጥ ሁለት ሚሊየን ሃምሳ ሺህ (2,050,000) ሰዎች ንግድ ፈቃድ የማውጣት እና የማደስ አገልግሎት አግኝተዋል።
የሚቀር ነገር አይጠፋም አልፎ አልፎ የሲስተም መቆራረጥ ሊኖር ይችላል ነገር ግን በአብዛኛው አፈጻጸማችን ውጤታማ ነው።
ይህ ሁሉ ሰው ካሳደሰ የሚቀረው ጥቂት ነው በርካታ ሰው ተገልግሏል በነጋዴዎች ችግር ካልሆነ በቀር ከሃምሌ ጀምሮ ማሳደስ ይችሉ ነበር ለምን እስካሁን አረፈዱ በመጨረሻ ሰዓት እንደዚህ አይነት ቅሬታ ማቅረብ ምክንያታዊ ሊሆን አይችልም " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የትግራይን ህዝብ አንድነት በሚያጠናክር መልኩ እንዲፈታ ይደረጋል" - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ዛሬ " ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን ሰላማዊ ሰልፍ አዘጋጆች መልእክት በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለዋል። ሰልፉን የጠራው የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ያዘጋጀው መልእክት የተቀበሉት ፕሬዜዳንቱ አቶ ጌታቸው…
" ከውጭ የሚመጣ ተሟጋች አያስፈልገንም !! " - አቶ ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በሂጃብ ጉዳይ ምን አሉ ?
" ከውጭ የሚመጣ ተሟጋች አያስፈልገንም። ጉዳዩ በራሳችን ነው የምንጨርሰው። ያለን አንድነት እና መፈቃቀር ሊነካ አይገባም።
የአክሱም ህዝብም በዚህች ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አቋም እንዳለው ነው የማውቀው። አንዳንድ በክፋት የተሰማራ ካልሆነ፥ እያያችሁት እንዳለ ይህ ጉዳይ ያላሳዘነው፣ መፍትሔ መበጀት አለበት ያላለ የለም።
ችግሩ እንደሚፈታ ነው ማምነው፣ ያለን ግንኙነትም የሚያሳየው ይህ ነው። በመዘግየቱ ግን ለሙስሊሙ ማሕበረሰብ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ልጆቹ ወደትምህርት ቤት መላክ የሚፈልግ የትግራይ ህዝብ ሁሉ ይቅርታ መጠየቅ አለብን ብዬ ነው የማምነው። "
Quote - #DW
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በሂጃብ ጉዳይ ምን አሉ ?
" ከውጭ የሚመጣ ተሟጋች አያስፈልገንም። ጉዳዩ በራሳችን ነው የምንጨርሰው። ያለን አንድነት እና መፈቃቀር ሊነካ አይገባም።
የአክሱም ህዝብም በዚህች ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አቋም እንዳለው ነው የማውቀው። አንዳንድ በክፋት የተሰማራ ካልሆነ፥ እያያችሁት እንዳለ ይህ ጉዳይ ያላሳዘነው፣ መፍትሔ መበጀት አለበት ያላለ የለም።
ችግሩ እንደሚፈታ ነው ማምነው፣ ያለን ግንኙነትም የሚያሳየው ይህ ነው። በመዘግየቱ ግን ለሙስሊሙ ማሕበረሰብ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ልጆቹ ወደትምህርት ቤት መላክ የሚፈልግ የትግራይ ህዝብ ሁሉ ይቅርታ መጠየቅ አለብን ብዬ ነው የማምነው። "
Quote - #DW
@tikvahethiopia
" ቢያንስ 20 ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው አልፏል " - IOM
ከጅቡቲ የተነሳች ስደተኞችን የጫነች መርከብ የመን አቅራቢያ በደረሰባት የመስጠም አደጋ ቢያንስ 20 ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው ማለፉን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አሳወቀ።
ከአደጋው 15 ኢትዮጵያውያን እና ሁለት የመናውያን የጀልባዋ ቀዛፊ እና ረዳቱ መትረፋቸውም ተገልጿል።
35 ስደተኞችን አሳፍራ ከጅቡቲ የተነሳችው ጀልባ ዱባብ አቅራቢያ ባጋጠማት ብርቱ ነፋስ ለአደጋው መጋለጧን ተመላክቷል።
በየመናዊ ካፒቴን እና ረዳቱ አማካኝነት ከጅቡቲ የባሕር ጠረፍ ጀልባዋ ስደተኞች አሳፍራ ቅዳሜ ዕለት በምሽት ነበር ጉዞ የጀመረችው።
አደጋው በርካታ ስደተኞች የሚጋፈጡትን አሳዛኝ አደጋ እንደሚያሳይ የገለጸው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለሕገወጥ ስደት መንስኤ ለሆኑ ችግሮች መፍትኄ እንዲፈልጉ ጥሪውን አቅርቧል።
በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሻለ የኑሮ ሁኔታ ፍለጋ በጅቡቲ በኩል ወደ የተለያዩ የአረብ ሃገራት እንደሚሰደዱ በተደጋጋሚ ይነገራል።
ባለፈው ጥቅምት ወርም በተመሳሳይ አደጋ ከጅቡቲ የተነሱ 45 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የተሳፈሩበት ጀልባ በደረሰበት አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።
የየመን ባሕር አካባቢ ለስደተኞች አደገኛ ከሆኑ የባሕር መስመሮች አንዱ መሆኑን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አመልክቷል።
ኢትዮጵያውን ስደተኞች ላይ ስለደረሰው አደጋ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰማ ነገር የለም።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
ከጅቡቲ የተነሳች ስደተኞችን የጫነች መርከብ የመን አቅራቢያ በደረሰባት የመስጠም አደጋ ቢያንስ 20 ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው ማለፉን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አሳወቀ።
ከአደጋው 15 ኢትዮጵያውያን እና ሁለት የመናውያን የጀልባዋ ቀዛፊ እና ረዳቱ መትረፋቸውም ተገልጿል።
35 ስደተኞችን አሳፍራ ከጅቡቲ የተነሳችው ጀልባ ዱባብ አቅራቢያ ባጋጠማት ብርቱ ነፋስ ለአደጋው መጋለጧን ተመላክቷል።
በየመናዊ ካፒቴን እና ረዳቱ አማካኝነት ከጅቡቲ የባሕር ጠረፍ ጀልባዋ ስደተኞች አሳፍራ ቅዳሜ ዕለት በምሽት ነበር ጉዞ የጀመረችው።
አደጋው በርካታ ስደተኞች የሚጋፈጡትን አሳዛኝ አደጋ እንደሚያሳይ የገለጸው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለሕገወጥ ስደት መንስኤ ለሆኑ ችግሮች መፍትኄ እንዲፈልጉ ጥሪውን አቅርቧል።
በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሻለ የኑሮ ሁኔታ ፍለጋ በጅቡቲ በኩል ወደ የተለያዩ የአረብ ሃገራት እንደሚሰደዱ በተደጋጋሚ ይነገራል።
ባለፈው ጥቅምት ወርም በተመሳሳይ አደጋ ከጅቡቲ የተነሱ 45 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የተሳፈሩበት ጀልባ በደረሰበት አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።
የየመን ባሕር አካባቢ ለስደተኞች አደገኛ ከሆኑ የባሕር መስመሮች አንዱ መሆኑን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አመልክቷል።
ኢትዮጵያውን ስደተኞች ላይ ስለደረሰው አደጋ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰማ ነገር የለም።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia